ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ነኝ

ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ነኝ
ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ነኝ

Tuesday, June 14, 2016

=>+*"+<+>††† ወደ ምስራቅ ተመልከቱ †††<+>+"*...

"ወደ ምስራቅ ተመልከቱ ማለት ምን ማለት ነው"??
በኦርቶዶክስ። ተዋህዶ ሀይማኖታችን ቤተ ክርስቲያን
የምታንፀው ምስራቁን አቅጣጫ ጠብቃ ነው እንድሁም
ከቤተ ክርስቲያኑ ጋር አብሮ የሚሰራው ቤተለሄም። በስተ
ምስራቅ በኩል ይደረጋል በፆለት ሰአትም ወደ ምስራቅ
ዙረን ነው የምንፀልየው በስረአተ ቀብር ላይም የሞተ
ሰው ሲቀበርእራሱ ውደ ምዕራብ እግሩ ወደ ምስራቅ።
ሆኖ ይቀበራል።ሌላው ዳቆኑ በስረአተ ቅዳሴው ላይ ወደ
ምስራቅ ተመልከቱ ይላል ለምን??
፩ የአዳም አባታችን ጥንተ ርስተ ገነት በምስራቅ ናት ዘፍ
2*8 ፪÷፰ ይች እርስታችን በአዳም በደል ምክንያት
በክሩቤል ሰይፍ ተዘግታ ስትኖር ሞትን ድል አድርጎ
በደልን ክሶ ጌታችን መዲሀኒታችን እየሱስ ክርስቶስ በሞቱ
ከፈተልን ሉቃ 23*43። ፳፫*፵፫ ወደ ምስራቅ በዞርን
ቁጥርወደ ገነት ለመግባት የተሰጠን ተስፍፋ ትዝ ይለናል
የተከፈተችውም ቤታችን ገነት በእምነት ውለል ብላ
ትታየናለች በክርስቶስ ያገኘነውን ፀጋ እናስባለን
ምድራዊያን አለመሆናችንንም እናስባለን
፪ ጌታ የተውለደው በምስራቅ ነው
ሰበአሰገል ኮኩቡን ያዩት በምስራቅ ሲሄን ያኮከብ
የምህረት እግዝያብሄር ምሳሌ ነው እርሱን ወደ
እግዝያብሄር እንዳደረሳቸው ሁሉ እኛንም ወደ ለመለመው
መስክ ይመራናል ማቴ ፳፪*፲፬ 22*14 ወደ ምስራቅ
በዞርን ቁጥር። የጌታን መውለድነ ያደረገልንን ውለታ
ይታውሰናል የምህረት ኮከብ እየመራን መሆኑን ትዝ
ይለናል
፫ ምስራቅ የእመቤታችን ምሳሌ ነው
ከምስራቅ ጨለማውን የሚገፈው።ፀሀይ እንደሚውጣ
ሁሉ ከእመቤታችን ከድንግል ማርያምም የአለም
የሀጥያት ጨለማ የሚገፍ ፀሀይ ፅድቅ እየሱስ ክርስቴስ
ውጥቷል። ተገኝቷል ለእናንተ ስሜ የምትፈሩ የፅድቅ
ፀሀይ ትወጣላችሁአለች። ሚል ፬*፩ 4*1 ህዝ ፵፬*፩÷፬
44*1-4 ነብዩ ህዝቀየልም እመቤታችንን ያያት በምስራቅ
ነው ስለዚህ ውደ ምስራቅ በዞርን ቁጥር እመቤታችንን
እናስታውሳለን የፅድቅ ፀሀይ ክርስቶስ ስለተውለደልን
በጨለማ አለመሆናችን ትዝ እያለን ከሀጥያት እንርቃለን
፬ የአለም ድህነት የተገኘው በምስራቅ ነው
ጌታ የተስቀለውና አለምን ያዳነው በምስራቅ ነው እየሩስ
አሌም ምስራቃዊት ከተማ ናት በመሆኑ ውደ ምስራቅ
በዞርን ቁጥር የተሰቀለውን ክርስቴስንና የተከፈለልንን ዋጋ
እናስባለን
፭ ክርስትናና ቤተ ክርስቲያን የተመሰረቱት በምስራቅ ነው
የመጅመሪያው ቤተ ክርስቲያን የተመስረተውበ በእየሩስ
አሌም ሲሆንውንጌል የተሰበከው ከዚህ በመነሳቱ ነው
ስለዚህ ውደ ምስራቅ ስንዞር የቤተ ክርስቲያን ጉዞ
የውንጌል መስፋፋትን የህዝብ ና የአለም መዳን ትዝ
ይለናል
፮ ምስራቅ የእግዝያብሄር ክብር መገለጫ ነው
ኢሳ ፳፰*፲፫ 28*13። እግዝያብሄር በምስራቅ
የእስራኤልንም አምላክ የእግዝያብሄርንም ስም በባህር
ደሴቶች አከበሩ ህዝ ፵፫*፪ 43*2 የእስራኤልንም
አምላክ ክብር ከምስራቅ መንገድ ውጣ ።
፯ የጌታ ዳግም ምፅአትም ከምስራቅ ነው
ዘካ ፲፬*፲፬ 14*14
ውስብሀት ለእግዝያብሄር አሜን

=>+*"+<+>††† 7 †††<+>+"*...

#ሰባት_ቁጥር_ምስጢራት
በመጽሐፍ ቅዱስና በስርዓተ ቤተ-ክርስቲያን አስተምህሮ ስባት
ቁጥር ብዙ ምሳሌ እንዳለው ይታወቃል፡፡ በዕብራዊያን
ዘንድም
ሰባት ፍጹም ቁጥር ነው፡፡ ምሳሌ 24፡16 እግዚአብሔር
ከሰኞ
እስከ እሑድ ያሉትን ቀናት በሰባት ቁጥሮች ወስኗል ሕዝበ
እስራኤል ከግብጽ ባርነት ወጥተው በሲና በርሀ ሲጓዙ ይመሩት
የነበሩት በ7 ደመና እንደነበረ ይታወቃል፡፡ ዘዳ 13፡21 ከዚህ
ቀጥለንም ለቤተ-ክርስቲያን አስተምህሮ የ7 ቁጥር
ምስጢራትን
ምሉዕነትን የሚያስረዱ ልዩ ልዩ ማስረጃዎችን በዝርዝር
እንመለከታለን፡፤
ሀ/ ሰባቱ አባቶች
1. ሰማያዊ አባታችን እግዚአብሔር
2. የነፍስ አባት
3. ወላጅ አባት
4. የክርስትና አባት
5. የጡት አባት
6. የቆብ አባት
7. የቀለም አባት
ለ ሰባቱ ዲያቆናት
1. ቅዱስ እስጢፋኖስ
2. ቅዱስ ፊልጶስ
3. ቅዱስ ጵሮክሮስ
4. ቅዱስ ጢሞና
5. ቅዱስ ኒቃሮና
6. ቅዱስ ጳርሜና
7. ቅዱስ ኒቆላዎስ
ሐ ሰባት የጌታ ቃላት /እኔ ነኝ
1. የሕይወት እንጅራ እኔ ነኝ
2. የዓለም ብርሃን እኔ ነኝ
3. እኔ የበጎች በር ነኝ
4. መልካም እረኛ እኔ ነኝ
5. ትነሣዔና ሕይወት እኔ ነኝ
6. እኔ መንገድና ሕይወት ነኝ
7. እውነተኛ የወይን ግንድ እኔ ነኝ
መ ሰባቱ ሰማያት
1. ጽርሐ አርያም
2. መንበረ መንግሥት
3. ሰማይ ውዱድ
4. ኢየሩሳሌም ሰማያዊት
5. ኢዮር
6. ራማ
7. ኤረር
ሠ ሰባቱ ሊቃነ መላእክት
1. ቅዱስ ሚካኤል
2. ቅዱስ ገብርኤል
3. ቅዱስ ሩፋኤል
4. ቅዱስ ራጉኤል
5. ቅዱስ ዑራኤል
6. ቅዱስ ፋኑኤል
7. ቅዱስ ሳቁኤል
ረ ሰባቱ አብያተ ክርስቲያናት
1. የኤፌሶን ቤተ ክርስቲያን
2. የሰርምኔስ ቤተ ክርስቲያን
3. የጴርጋሞን ቤተ ክርስቲያን
4. የትያጥሮስ ቤተ ክርስቲያን
5. የሰርዴስ ቤተ ክርስቲያን
6. የፊልድልፍልያ ቤተ ክርስቲያን
7. የሎዶቅያ ቤተ ክርስቲያን
ሰ ሰባቱ ተዐምራት
ጌታ እኛን ለማዳን በመስቀል ላይ በተሰቀለ ጊዜ የተፈጸሙ
ተዐምራት
1. ፀሐይ ጨልሟል
2. ጨረቃ ደም ሆነ
3. ከዋክብት ረገፉ
4. ዐለቶች ተሠነጠቁ
5. መቃብራት ተከፈቱ
6. ሙታን ተነሡ
7. የቤተ መቅደስም መጋረጃ
ሸ ሰባቱ የመስቀሉ ቃላት
1. አምላኬ አምላኬ ለምን ተውከኝ
2. አባት ሆይ የሚያደርጉትን አያውቁምና ይቅር በላቸው
3. ዛሬ ከእኔ ጋራ በገነት ትሆናለህ
4. እነሆ ልጅሸ እናትህ እነሆት
5. ተጠማሁ
6. ተፈጸመ
7. አባት ሆይ ነፍሴን በእጅህ አደራ እስጥሃለሁ
ቀ ሰባቱ ምሥጢራተ ቤተ ክርስቲያን
1. ምሥጢረ ጥምቀት
2. ምሥጢረ ሜሮን
3. ምሥጢረ ቁርባን
4. ምሥጢረ ክህነት
5. ምሥጢረ ተክሊል
6. ምሥጢረ ንስሐ
7. ምሥጢረ ቀንዲል
በ ሰባቱ ዐበይት አጽዋማት
1. ዐቢይ ጾም
2. የሐዋርያት ጾም
3. የፍልሰታ ጾም
4. ጾመ ነቢያት
5. ጾመ ገሀድ
6. ጾመ ነነዌ
7. ጾመ ድኅነት
ተ ሰባቱ በእግዚአብሔር ዘንድ የተጠሉ ነገሮች
1. ትዕቢተኛ ዓይን ምሳ 16፡6-19
2. ሃሰተኛ ምላስ
3. ንፁህን ደም የምታፈስ እጅ
4. ክፉ ሃሳብን የምታፈልቅ ልብ
5. ለክፋት የምትፈጥን እጅ
6. የሐሰት ምስክርነት
7. በወንድሞች መካከል ጠብን የምታፈራ ምላስ
ቸ ሰባቱ ፀሎት ጊዜያት
1. ነግህ የጠዋት ጸሎት
2. ሠለስት (የ3 ሰዓት ጸሎት)
3. ቀትር (የ6 ሰዓት ጸሎት)
4. ተሰአቱ (የ9 ሰዓት ጸሎት)
5. ሰርክ (የ11 ሰዓት ጸሎት)
6. ነዋም (የምኝታ ጸሎት)
7. መንፈቀ ሌሊት (የሌሊት ጸሎት)
ኀ ሰባቱ ራሶች (2ኛ ነገ. 17፡6)
1. ኢራን
2. ኢራቅ
3. ግሪክ
4. ሚዳን
5. ግብጽ
6. ጣሊያን
7. እስራኤል
ወስብሐት ለእግዚአብሔር ለዘበቅዱሳኒሁ
ይሴባሕ ይእዜኒ ወዘልፈኒ ወለዓለም ዓለም አሜን፡፡ ወአሜን
ለይኩን ለይኩን፡፡

Saturday, June 11, 2016

=>+*"+<+>††† ጻድቁ አባታችን አቡነ ገብረ መንፈስ ቅዱስ †††<+>+"*+

አእምሩ ከመ ተሰብሐ እግዚአብሔር በጻድቁ =>ዘፍ19:3
እግዚአብሐር በጻድቁ እንደተገለጠ እወቁ =>መዝሙረ ዳዊት
4:3 ++++እንኳን ለጻድቁ አባታችን አቡነ ገብረ መንፈስ
ቅዱስ ክብረ በዓል በሰላም አደረሳችሁ አደረሰን የጻድቁ
አባታችን አቡነገብረ መንፈስ ቅዱስ ፀሎት ,ምልጃና እረድሂት
በረከታቸው በሁላችን ላይ ይደርብን አሜን !!!!!!!!
ፃድቁ አባታችን አቡነ ገብረ መንፈስ ቅዱስ በስመ አብ ወወልድ
ወመንፈስ ቅዱስዝክረ ጻድቅ ለዓለም ይሄሉ (የጸድቅ መታሰቢያ
ለዘላለም ይኖራል።) መዝ.111፡6ቅድመ ዓለም ዘሀሎ አለም
ከመፈጠሩ በፊት ለነበረ ለእግዚአብሔር አብ እና የእመቤታችን
የቅድስት ድንግል ማርያም ሥጋን ለለበሰ ለእግዚአብሔር
ወልድ እንዲሁም ከእነሱ ባለመራቅ ለሚኖር ለእግዚአብሔር
መንፈስ ቅዱስም ምስጋና ይገባል፡፡ ስለ ጻድቁ አቡነ ገብረ
መንፈስ ቅዱስ በማብዛት አይደለም በማሳነስ በማስረዘም
አይደለም በማሳጠር እንድጽፍ ያነሳሳኝ እግዚአብሔር ክብርና
ምስጋና ጌትነትና ውዳሴ ይገባዋል አሜን
በእውነት፡፡“እግዚአብሔር ያፈቅሮሙ ለጻድቃን
እግዚአብሔር የዐቅቦሙ ለፈላስያን፡፡“ (እግዚአብሔር
ጻድቃንን ይወድዳል፤ እግዚአብሔር ስደተኞችን
ይጠብቃል፡፡)“” መዝ.፻፵፭፡፰ (145፡ 8)አባታችን አቡነ ገብረ
መንፈስ ቅዱስ ሀጋራቸው ንሂሳ ግብጽ ነው፡፡ አባታቸው ስምዖን
እናታቸው አቅሌስያ፡ ይባላሉ፡፡ ልጅ አጥተው 30 ዘመን
ሲያዝኑ ኖረዋል፡፡ አንድ ቀን አቅሌሲያ ቤተ እግዚአብሔር
ገብታ ከሥዕለ ሥላሴ ሥር ወድቃ ስትማጸን ክብሩ ከሰማይ
ከፍታ የሚበጥ ልጅ እንኪ ተቀበይ የሚል ድምጽ ሰማች፡፡
በዚሁ መሰረት አባታችን መጋቢት 29 ተጸንሰው ታህሳስ 29
ተወለዱ፡፡ ዓይን በገለጹ ጊዜ ከሚታይ ነገር ላይ እንዲያርፍ
እርሳቸውም በተወለዱ ጊዜ አፈፍ ተነስተው “ስብሐት ለአብ
ስብሐት ለወልድ ስብሐት ለመንፈስ ቅዱስ ዘአውጻእከኒ እምጽ
ልመት ውስተ ብረሃን” ብለው በማመስገናቸው ኋላም ምድራዊ
መብል መጠጥ ሳይመገቡ ሳይጠጡ ለምስጋና ተግተው
በመኖራቸው መላዕክትን ይመስላሉ፡፡ሦስት ዓመት ሲሆናቸው
ቅዱስ ገብርኤል ከእመቤታችንና በገነት ካሉ ቅዱሳን ዘንድ
አስባርኮ ገዳማውያን ካሉበት ምኔት ወስዶ ከበሩ አኖራቸው፡፡
አባ ዘመደ ብርሃን አሳድጎ አስተምሮ ከመዓርገ ምንኩስና
አድርሷቸዋል፡፡ ከዚህ በኋላ “ሀብተ ፈውስ” ተሰቷቸዋል፡፡
በአንድ ቀን እልፍ እውራንንና አንካሳን ፈውሷል፡፡ ኋላ ግን
ኤጲስ ቆጶሳቱ ካህናቱ ዝናቸውን ሰምተው እየመቱ ግብር
የሚያስፈቷቸው ቢሆን ቅዱስ ገብርኤል በክንፉ ነጥቆ ከጌታ
ፊት አቀረባቸው፡፡ በገድልህ በትሩፋትህ ከሞተ ነፍስ ከርደተ
ገሃነም የሚድኑ ብዙ ነፍሳት አሉና ከሰው ተለይተህ ወደ ጫካ
ግባ፡፡ ኑሮህም ከ60 አናብስተና ከ60 አናምርት ጋር ይሁን
አላቸው፡፡ ጌታዬ ምን ተመግበው ይኖራሉ? ብለው ጌታን
ጠየቁት፡፡ “ዘኬድከ ጸበለ-እገሪከ ይልህሱ ወበውእቱ ይጸግቡ…”
የረገጥከውን ትቢያ ልሰው ያው ምግብ ሆኗቸው ይኖራሉ፡፡
ብሏቸው ውሳጤ ገዳም ገብተው ከአናብስትና አናምርት ጋር
ይኖሩ ጀመር፡፡ ዳንኤል በአናብስት ጉድጓድ በጣለ ጊዜ አናብርቱ
እንደ ድመት ከእግሩ በታች ሆነው እንደተገኙ የረገጡትን ትቢያ
ይልሱ ይታዘዟቸውም ነበር፡፡ በዚህ መልኩ መልአኩ 30
ዓመት ከቆዩ በኋላ ጌታ ባንድነት በሦስትነት ተገልጾ “ምን
ላድርግልህ ትሻለህ?” አላቸው፡፡ መጀመሪያ ላሉበት መጸለይ
ይገባልና የምድረ ጋቦታን ሰዎች ማርልኝ አሉት፡፡ 3000
ሃጥአንን ከሲኦል አውጥቶ ገነት አግብቶላቸዋል፡፡ “ሑር ምድረ
ኢትዮጵያ ወበህየኒ ሀላውከ ነፍሳት ዘታወጽኦሙ ወደ ኢትዮጵያ
ሂድ” አላቸው፡፡ ቅዱስ ገብርኤል በሰረገላ ነፋስ ጭኖ ምድረ
ከብድ አድርሷቸዋል፡፡ ዳግመኛም ወደ ዝቋላ ደብር ቅዱስ
ወስዷቸው ከዚያ ሆነው በንጽሐ ልቦና የኢትዮጵያን ሕዝብ
ሃጢአት አይተው ከባሕሩ በራሳቸው ቆመው ይጸልዩ ጀመር፡፡
አርባ ቀን ሲሆናቸው መልአኩ መጥቶ “ዘገብረ ተዝካረከ
ወዘጸውዐ ስመከእምሕር ለከ ብሎሀል” አላቸው፡፡ መላ
ኢትዮጵያን ካልማረልኝ አልወጣም ብለው መቶ አመት ሲጸልዩ
ኑረዋል፡፡ ከመቶ አመት በዃላ ጌታ “ተንስእ ወጻእ መሐርኩ ለከ
ኩሎ ኢትዮጵያ ምሬለሃለሁ ውጣ” ብሏቸው ወጥተዋል፡፡ከዚህ
በኋላ ምድረ ከብድ ወርደው ከምድር በላይ ከሰማይ በታች
ሆነው ሰባት ዓመት እንደ ትኩል አምድ ሆነው ዓይናቸውን
ሳይከድኑ ሰባት ዓመት ቆመው ጸልየዋል፡፡ ሰይጣንም
በምቀኝነት ተነሳስቶ ቁራን መስሎ መጥቶ አይናቸውን አንቁሮ
አሳወራቸው፡፡ ሁለት ሱባኤ ሲፈጽሙ ቅዱስ ሚካኤልና ቅዱስ
ገብርኤል መጥተው እፍ ብሏቸው አድነዋቸዋል፡፡ ከዚያ
ተነስተው ወደ ዝቋላ ሲሄዱ ሥላሴን በአምሳለ አረጋውያን
ከጥላ ስር አርፈው አገኟቸው፡፡ በእግዚአብሔር ዙፋን
ተማጽነናል አዝለህ አንድ አንድ ምዕራፍ ሸኘን አሏቸው፡፡
አዝለው ከሸኙአቸው በኋላ በአንድነት በሦስትነት ሆኖ ታያቸው
ደንግጠው ወደቁ፡፡ አንስተው ዝቋላ ወርደህ ጠላቶችህን
ተበቀላቸው አሏቸው፡፡ በዘባነ መብረቅ ደርሰው ሰባቱን ሊቃነ
መላእክት አጋዥ አርድገው እልፍ አዕላፍ አጋንንትን በማጭድ
አጭደዋል፡፡ እንዲህ ለሰሚዕ እፁብ በሆነ ግብር ዓመት
በኢትዮጵያ 262 ኖረው በ562 ዓመታቸው በተስፋቸው
ያመነውን በኪዳናቸው የተማጸነ ጌታ ከመከራ ሥጋ ከመከራ
ነፍስ ሊምርላቸው ተስፋቸውን ተቀብለው በዕለት በዕለተ እሁድ
ዐርፈዋል፡፡መላእክት በአክናፈ እሳት ኢየሩሳሌም ወስደው
በየማነ ምስዋዕ ቀብረዋቸዋል፡፡ሮሜ 12፡12፣ 15፡
30፣ያዕ5፡ 16፣ መዝ.88፡3፣111፡6 ምሳ.10፡7 ማቴ10፡
40-42ወደ ኢትዮጵያ የመጡት በቅዱስ ላሊበላ ዘመነ
መንግስት መሆኑ ስለሚታወቅ ከ9- 14ኛው ም/ዓ ድ/ል/ክ
መሆኑ ነው፡፡ ካለመኖር ወደ መኖር ያመጣኝ፣ ካለማወቅ ወደ
መረዳት ያደረሰኝ አነሳስቶ ላስጀመረኝ አስጀምሮ ላስፈጸመኝ
ጥንት ላሌለው ቀዳማዊ ፍጻሜ ላሌለው ድህራዊ ያልኖረበት
ጊዜ የሌለ የማይኖርበት ጊዜም የማይኖር የዘላለም ንጉስ
ሁሉን ቻይ ፈጣሪ እግዚአብሔርን በራስ ፀጉሬ ቁትር
በአጥንቶቼም ልክ አመሰግናለሁ፡፡በሰማይ ያሉ መላእክት
በምድርም የሚኖሩ የአዳም ዘር ሁሉ የሚያመሰግኗት
በአማላጅነቷ ሁል ጊዜ የማትለየኝ ከፀሐይ ሰባት እጅ የምታበራ
የብርሃን እናት የሁሉ እመቤት የአምላክ እናት ከተመረጡ
የተመረጠች ከተለዩ የተለየች ከተከበሩ የተከበረች እናቴ
እመቤቴ ድንግል ማርያም በቃላት ልገልጸው ከምችለው በላይ
አመሰግናለሁ፡፡ወስብሐት ለእግዚአብሔር ለዘበቅዱሳኒሁ
ይሴባሕ ይእዜኒ ወዘልፈኒ ወለዓለም ዓለም አሜን፡፡ ወአሜን
ለይኩን ለይኩን፡፡
ምንጭ፡- መዝገበ ታሪክ፣ ነገረ ቅዱሳን፣ የወርሃ ጥቅምት
ስንክሳርና ገድላቸው፡፡

Wednesday, June 8, 2016

=>+*"+<+>††† ዕርገት †††<+>+"*+

†† †† ††
#ዕርገት
††
“እግዚአብሔር” በእልልታ ጌታችንም በመለከት ድምጽ ዐረገ
ዘምሩ ለአማላካችን ዘምሩ፤ ዘምሩ ለንጉሳችን ዘምሩ። መዝ
45:5
+
" እግዚአብሔርንም የመምሰል ምሥጢር ያለ ጥርጥር ታላቅ
ነው፤ በሥጋ የተገለጠ፥
በመንፈስ የጸደቀ፥
ለመላእክት የታየ፥
በአሕዛብ የተሰበከ፥
በዓለም የታመነ፥
በክብር ያረገ።"
(1ኛ ወደ ጢሞቴዎስ 3:16)
†† †† ††
እንኩዋን ለጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ዓመታዊ የዕርገት በዓል
በሰላም አደረሳችሁ!!!
†††
ሙሴ አሮንንና ሖርምን ከተማዋን እንዲጠብቁ አድርጎ ኢያሱን
አስከትሎ
ወደ ደብረ ሲና ሔደ። ኢያሱን ከተራራው ግርጌ ትቶ ሙሴ
ብቻውን ወደ
ሲና ወጣ። በሲና ተራራም 40 ቀንና ለሊት ቆየ።
በዚህን ጊዜ እስራኤላዊያን ተስፋ ቆረጡና ማጉረምረም
ዠመሩ።
“ፀሐይ ወጣች ገባች ሙሴ ግን ቀለጠ” አሉ። አመሌ አመሌ
ሲል
በደብረ ሲና ያያት እሳት አቃጠለችው እንዴ? ሐመልማሉንስ
አላቃጠለች
ሙሴን ፈጀችው እንዴ? ይህ ባይሆንም ወደኛ ሲመጣ ባሕረ
ኤርትራን
ሲሻገር ሰጠመ እንዴ? ብለው አጉረመረሙ።
አንገተ ደንዳና የተባሉት እስራኤላዊያን በሬ አላርስ ሲል
አንገቱን
እንደሚያደነድን አንገታቸውን አደንድነው ካህኑ አሮንን ሙሴ
ስለቀረ
አምላክም ስለሌለ ጣኦት ስራልን ብለው ጮኹ። አሮን አሮን
ግበር ለነ
አማልክተ ዘይሐውሩ ቅድሜነ እያሉ ጣኦቱ ይሰራላቸው ዘንድ
ካህኑ
አሮንን አቻኮሉት አጣደፉትም። ይገርማል! እኛም አንዳንዴ
ካህናቱን
የማይገባ ሥራ ስሩ እንደምንላቸው ማለት ነው። ካህናቱን ፣
መነኮሳትን
፣ ጳጳሳትን ፤ ባሕታዊያንን ዓለማዊ ስራ ስሩ እንደምንላቸው
እስራኤላዊያንም ካህኑን ጣዖት ስራ አሉት።
አሮን ልቡ ተከፈለ። ጣኦቱን ቢሰራ ከፈጣሪ ሊጣላ ባይሰራ
እስራኤላዊያን በድንጋይ ሊወግሩት መኾኑን እያሰበ ልቡ
ተከፈለ።
በመጨረሻም ዘዴ መጣለት። አፍቃሬ ንዋይ ናቸውና
ወርቃችሁን አምጡ
ብላቸው ይሰስታሉ ብሎ አሰበ። ይኹን እንጂ በልባቸው ያደረው
ሰይጣን
እጃቸውን ፈቶ ወርቁን በአሮን እግር አስቀመጡ። ካህኑም
መሬት
ተቆፍሮ ቢቀበር ጣኦት ይኾናል አላቸው በዚያው ጠፍቶ
የሚቀር
መስሎት። ግና የተቀበረው ወርቅ በግብረ ሰይጣን አንገቱ
ወርቅ ደረቱ
ብር እግሩ ብረት የኾነ ጥጃ ኾኖ ወጣ።
†††
እስራኤላዊያንም አምላካችን እያሉ መጮኽ ዠመሩ። ቀን
ሲደርስ አንባ
ይፈርስ እንዲሉ ሙሴ ከሲና ተራራ የሚወርድበት ቀን ደረሰ።
ጽላቱን
ከእግዚአብሔር ተቀብሎ 40 ቀን ሙሉ ከሲና ተራራ ግርጌ
የነበረውን
ትዕግስተኛ ኢያሱን አስከትሎ ወደ ሕዝበ እስራኤል መጣ። ነቢዩ
ሙሴ
ከሲና ተራራ ላይ የቃል ኪዳኑን ታቦት ይዞ ሲወርድ
እስራኤላዊያን ጣኦትን
ያመልኩ ነበር፤
ሙሴ ከሲና ተራራ መውረዱ .... ጌታችን ከሰማየ ሰማያት
የመውረዱ
ምሳሌ ነው።
ታቦቱ ከሙሴ እጅ ወድቆ ጣዖታቱን ሰባበረ ...... ይህም ጌታችን
የዲያቢሎስን እራስ እራሱን የመቀጥቀጡ ምሳሌ ነው።
ጌታ ስለ ኃጢአታችን በፈቃዱ ሞቶ ሞትን ድል አድርጎ ተነሣ
“በክብርም
ዐረገ” ይህም ታቦቱ ከእንደገና በእግዚአብሔር ጣት ተጽፎ
ለሙሴ
የመሰጠቱ ምሳሌ ነው!!! ዘፀአት ምዕ. 31-34
ልበአምላክ ዳዊት ለምስጋና አሥሩን ቅኝት ቃኘውና በገናውን
አነሳና
የጌታን ዕርገት በትንቢት መነጽር አየነና እንዲህ አለ፦
“እግዚአብሔር”
በእልልታ ጌታችንም በመለከት ድምጽ ዐረገ ዘምሩ
ለአማላካችን ዘምሩ፤
ዘምሩ ለንጉሳችን ዘምሩ። መዝ 45:5፤ መጽሐፍ አንባቢው
ያስተውል!
ይላል። የዳዊትን መዝሙር ልብ ብለህ ስማው! ልበ አምላክ
ዳዊት
ጌታችን በዐረገ ጊዜ “እግዚአብሔር ዐረገ” ብሎ ተነበየ።
ጌታችን ሞትን
ድል አድርጎ ሲነሣ ደግሞ ምን እንዳለ አስተውል
“እግዚአብሔር
ከእንቅልፍ እንደሚነሳ ተነሣ” መዝ 77:65
አንድም ንዋየ ኅሩይ ሐዋርያው ቅዱስ ጳውሎስ በደሙ ያፀናትን
የእግዚአብሔርን ቤተክርስቲያን ጠብቁ አለ; ደሙን በላዕለ
መስቀል ላይ
ያፈሰሰውን ጌታችንን “እግዚአብሔር” ብሎ ተናገረ
ሐዋ20:28።
††† ††† †††
" #ዕርገት_በደብረዘይት_ተራ ራ"

ጌታችን የዐረገው በደብረዘይት ተራራ ላይ ሲሆን በዚህች ተራራ
ላይ
ብዙ የወይራ ተክል ስለሚገኝ ተራራው ደብረዘይት ተብሏል።
ጌታችን ከትንሳኤ “እስከ ዕርገቱ ለ40 ቀናት” ለሐዋርያቱ
እየተገለጸ
ያስተምራቸው ነበር። [ሐዋ. 1:3] ነገር ግን ምን
እንዳስተማራቸው
አልተጻፈም; በመፅሐፈ ኪዳን ላይ ግን ተፅፏል።
ቤተክርስቲያናችን
አዋልድ መጽሐፍትን የምትጠቀመው በእንዲህ ሁኔታ ነው
ማለት ነው።
“ይህ ወደ ሰማይ ሲያርግ የአያችሁት ኢየሱስ በክብር ወደ ሰማይ
ሲወጣ እንዳያችሁት እንዲሁ በክብር ይመጣል” ሐዋ. 1:11
አምላክ በእልልታ እግዚአብሔር በመለከት ድምጽ
********* ዐረገ ********* መዝ46:5
ከላይ እንዳየነው እንደ ልቤ የተባለለት ዳዊት; ብርሐነ ዓለም
የተባሉት ሐዋርያት እንዲህ ብለው የጻፉትን መናፍቃኑ ሁሌ
ባነበቡት
ቁጥር እስከ ዛሬ ድረስ እንዲሁ አይናቸው እያነበበ ያልፉታል!!
ለነገሩ
ሐዋርያው አስቀድሞ እንዲህ ብሏል፦ “እናንተ የማታስተውሉ
የገላትያ
ሰዎች ሆይ በመስቀል ላይ የተሰቀለውን ክርስቶስን እንዳታዩ
ማን አዚም
አደረገባቹ” ገላትያ 3:1
የጌታችን የኢየሱስ ክርስቶስን አምላክነት ከመጽሐፍ ቅዱስ
ከብዙ
በጥቂቱ ፦
ብሉይ ኪዳን *** አዲስ ኪዳን
መዝ 46:5 *** ሮሜ 9:5
ኢሳያስ 9:6 *** እብራዊያን 1:10
ሚክያስ 5:2 *** ቆላስይስ 1:15
ዘካርያስ 9:9 *** ራዕ 22:12
††† ††† †††
“ #ከዕርገት_በኋላ_10ኛዋ_ ቀን”

እመቤታችን ከሐዋርያቱ ጋር በተዘጋ ደጅ ኾና በፀሎት
ትረዳቸው ነበር፤
በፀሎት ላይ እያሉም ጌታችን ከሞት በተነሣ በ50ኛው በዐረገ
በ10ኛው
ቀን መንፈስ ቅዱስ ለሐዋርያቱ ወረደ። ይህች ቀን ልደታ
ዘቤተክርስቲያን
በመባል ትታወቃለች፤ ምክንያቱም እነ ቅ/ጴጥሮስ በአንድ ቀን
3ሺ
ሰዎችን አጥምቀው አማኞች ስላደረጉ ነው። [የሐዋ.2:41]
በዚህች ቀን
ርደተ መንፈስ ቅዱስ [የመንፈስ ቅዱስ መውረድ ኾኖ
ለሐዋርያቱ
በአውሎ ንፋስና በእሣት አምሳል ተገለፀላቸው። ጌታችን
ለኒቆዲሞስ
መንፈስ ቅዱስ በአውሎ ንፋስ መገለፁን ሲያስረዳው እንዲህ
አለው፦
ሰው ከውኃና ከመንፈስ ካልተወለደ በቀር ወደ እግዚአብሔርን
መንግስት
አይገባም… “ንፋስ ወደሚወደው ይነፍሳል ድምፁንም
ትሰማለህ” ከየት
እንደመጣና ወዴት እንደሚሔድ አታውቅም የተባለውም በዚሁ
ምክንያት
ነው፤ ዮሐ. 3:8።
ከበዓለ ዕርገት ጋር በተያያዘ ጥያቄ ልናነሳ እንችላለን፤ ብዙ
ጊዜ ሰዎች ጌታችን 40 ቀን ብቻ ጾሞ እኛ ለምን 55 ቀናት
እንፆማለን
እያሉ ይጠይቃሉ፤ ለጥያቄያቸው እራሱን የቻለ መልስ
ቢኖረውም ይህን
የሚጠይቁ ሰዎች ግን ከትንሣኤ ጀምሮ ሐዋርያቱ “መንፈስ
ቅዱስ”
እስከተቀበሉበት ቀን ድረስ ለ50 ቀናት ለምንድን ነው
የማንጾመው
ብለው አይጠይቁም፤ ሙሽራው ከሐዋርያቱ ጋር እያለ
አይጾሙም
ስለተባለ በእነዚህ ግዜያት አይፆምም አይሰገድም ለንስኃ ቀኖና
ቢሰጥም ቀኖናው በዚህ ወቅት አይፈጸምም።
[ንስኃ እንገባለን ነገር ግን ቀኖናው እስከ ጾመ ሐዋርያት ድረስ
ይቆያል ]

“ዕርገትና እግዚኦታ” ፦ በእግዚኦታ ላይ ካህኑ ሕብሥቱን
ይበልጥ ከፍ
አድርጎ ይይዘዋል ይህም “የዕርገቱ” ምሳሌ ነው። ከካህኑ ጋር
ሆነን 41
ግዜ እግዚኦ መሐርነ ክርስቶስ እንላለን ፤ ይህም አርባው
እግዚኦታ
አይሁድ ጌታችንን 40 ግዜ እንገርፋለን ብለው እያዛቡ ብዙ ግዜ
የመግረፋቸው ምሳሌ ሲሆን በመጨረሻ ካህኑ ብቻውን
የሚላት
እግዚኦታ ደግሞ የአዳምና የሔዋን የንስሃ ምሳሌ ነው። 12
ግዜ
እግዚኦ መሐርነ ክርስቶስ ስንል ደግሞ ስለስምህ ብለህ ይቅር
በለን
ስንል ነው።
“አብ ወልድ መንፈስ ቅዱስ” የሚለውን እያንዳንዱን ፊደል
ስንቆጥር
12 ይሆናልና!!
Ascend in to haven in glory sit the right hand
of the
father & again wilt come on glory to judge
the quick
and the dead Have mercy up on us.
አቤቱ ሞትህን ልዩ የምትሆን ትንሣኤህንም እናስተምራለን፤
ዕርገትህን
ዳግመኛ መምጣትህን እናምናለን ፤ እናመሰግንሃለን፤
እናምንሃለን ፤
ፈጣሪያችን ሆይ እንማልድሃለን።
+
እግዚአብሔርንም የመምሰል ምሥጢር ያለ ጥርጥር ታላቅ
ነው፤
በሥጋ የተገለጠ፤
በመንፈስ የተረዳ፤
ለመላዕክት የታየ
በአሕዛብ ዘንድ የተሰበከ፤
በዓለም የታመነ፤
በክብር ዐረገ 1ኛ ጢሞ 3:16
*********
እነኾ በዓለ ዕርገትን ይህን የመሳሰሉትን እያሰብን እናከብራለን።
†††
ቤተክርስቲያን ባህረ ጥበባት
አትመረመርም እጅግ ጥልቅ ናት
የሲኦል ደጆች አይችሏትም
ቤተክርስቲያን አትታደስም!
የሐዋርያት ጉባኤ ስለሆነች ስለአንዲት ቅድስት ቤተ ክርስቲያን
ሰላም
እንማልዳለን!
(መጽሐፈ ሚስጢር)
የእግዚአብሔር ቸርነት፣ የድንግል ማርያም አማላጅነት፣
የቅዱሳን መላእክት ተራዳኢነት፣ የጻድቃን፣ የሰማዕታት፣
የቅዱሳን ሐዋርያት፣ የቅዱሳን አበው መነኮሳት፣ የቅዱሳት
አንስት፣ የደናግላንና የቅዱሳን ሁሉ ምልጃና ቃል-ኪዳናቸው
ባለንበት ከሁላችን ጋር ይሁን!!!
†† † ♥ † ††
ለአባ ሕርያቆስ ፤
ለቅዱስ ኤፍሬም ፤
ለቅዱስ ያሬድ ፤
ለአባ ጊዮርጊስ ዘጋስጫ
የተገለጸች እመቤታችን እኛንም በበረከት እና በረድኤት
ትጎብኘን ፤ ከልጅዋ ከወዳጅዋ ከመድኃኔዓለም ዘንድ ታማልደን
፤ አሜን!!!
†† † ♥ † ††
ከዋክብት የሚያመሰግኑት
በስማቸውም የሚጠራቸው:
የፀጋው ብዛት የማይታወቅ
ጌታችን አምላካችንና መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ሆይ
ለሐዋሪያት እንዲሁም ለቀደሙ አባቶቻችን ምሥጢሩን
እንደገለጽክላቸው ለእኛም ግለጽልን። አሜን አሜን አሜን!!!
†† †♥ † ††
ወ ስ ብ ሐ ት ለ እ ግ ዚ አ ብ ሔ ር
ወ ለ ወ ላ ዲ ቱ ድ ን ግ ል
ወ ለ መ ስ ቀ ሉ ክ ቡ ር

Friday, June 3, 2016

=>+*"+<+>††† ግንቦት_27_መድኃኔዓለም †††<+>+"*+

አንድ አምላክ በሚሆን በአብ በወልድ በመንፈስ ቅዱስ ስም
አሜን
#ግንቦት_27_መድኃኔዓለም _ክርስቶስ_ለመባዓ
#ጽዮን_ያደረገለት_ተአምር _ይኽ_ነው፡- ‹‹ተክለማርያም
የተባለ መባዓ ጽዮን የመድኃኔዓለምን በዓል ከሌላ ጋር
አይጨምርም ነበር፡፡ ለመድኃኔዓለም መታሰቢያ የሚሆነውን
ሁሉ ለብቻው ያስቀምጠዋል፡፡ በረሃብ እስኪሞት ድረስ
ከመድኃኔዓለም መታሰቢያ እህል ምንም አይቀምስም፡፡
ያዘጋጀውንም ኅብስትና ጽዋ ለሕዝቡ ይሰጣቸዋል፡፡ የታመሙ
ሰዎችም ለመድኃኔዓለም መታሰቢያ ከተዘጋጀው በበሉ ጊዜ
ከሕመማቸው ሁሉ ይድናሉ፡፡ አባታችን የሚያዘጋጀውን
የመድኃኔዓለምን መታሰቢያ ይበሉ ዘንድ እየተጨናነቁ
ከቅርብም ከሩቅም ሰዎች በእምነት ይመጡ ነበር፡፡ በየወሩ
በዓሉም በቀረበ ጊዜ በጾምና በጸሎት ሰባት ቀን ይማለላል፡፡
ሆዱን ሳያጠግብ ራሱን ሳያስተኛ በፍጹም ልቅሶ መከራውን
ያስባል፡፡ ምድርን እስኪያርስ ድረስ ከዓይኖቹ ዕንባውን
ያፈሳል፡፡ ከልቅሶውም ብዛት የተነሣ እስኪጠፋ ድረስ ዓይኖቹ
ታመሙ፡፡ እመቤታችን ማርያምም ብርሌ የሚመስል ጽዋን
በእጇ ይዛ መጣች፡፡ ‹ወዳጄ ተክለማርያም ሆይ! ስለ ልጄ
ፍቅር ለታመሙ ዓይኖችህ መድኃኒትን እሰጥህ ዘንድ እነሆ
መጣሁ› አለችውና ጣቶቿን ከዚያ ጽዋ ነክራ ዓይኖቹን ቀባችው፤
ከሕመሙም ዳነ፡፡ ከዚያን ጊዜ ጀምሮ ሕመም አላገኘውም፡፡
በተቀደሰች በዓርባ ጾምም የመድኃኔዓለምን ግርፋት እያሰበ
ሰውነቱን በእጅጉ ገረፈ፡፡ ደሙ ከመሬት እስኪወርድ ድረስ
ልቡንም አጥቶ ከምድር ላይ ወደቀ፡፡ የመድኃኔዓለምን
መከራውን አስቦ እንደሞተም ሆነ፡፡ መድኃኔዓለምም ወደ
እርሱ መጣና ‹ተነሥ እኔ ቁስልህን እፈውስሃለሁ› ብሎ
የጀርባውን ቁስል ዳሰሰው፡፡ ምንም ሕማም እንዳላገኘውም
ሆነ፡፡ መድኃኔዓለምም አባታችንን ‹በአንተው እጅ ትገደልን?
እኔ እንኳ የተገደልኩት በአመፀኞች በአይሁድ እጅ ነው› አለው፡፡
በዚያችም ሰዓት ጌታ የመባዓ ጽዮንን ከንፈሮቹን ይዞ አፉን
ከፍቶ ሦስት ጊዜ እፍ አለበት፡፡ ‹የከበረ ትንፋሼም ከትንፋስህ
ጋራ ይጨመር፣ ሥጋህም ከነፍስህ ጋራ የከበረ ይሁን› አለው፡፡
‹አንተ በላዩ እፍ ያልህበትም የተቀደሰና የከበረ ይሁን› አለው፡፡
ብፁዕ ተክለማርያምንም አይቶ ለሰው ፈጽሞ የሚያስደንቅ
ነገርን ነገረው፡፡ ቅድስት ድንግል ማርያምም ስለ ልጇ ስለ
ፍቅሩ ገናንነትም ተደሰተች፡፡ መድኃኔዓለምም አባታችንን ‹ስለ
ሕማሜ ታመሃልና ስለ ክቡር ደሜም ደምህን አፍሰሃልና ስለ
ሞቴም ሞተሃልና እንደወደድኸኝ እኔም እወድሃለሁ፣
ሁልጊዜም ከአንተ አልለይም፡፡ አንተን የወደደ እኔን ወደደ፣
አንተንም የጠላ እኔን ጠላ፣ የላከኝንም ጠላ፣ እኔን እንደጠሉኝ
እንደ አይሁድ ይሁን፡፡ ነፍስህ ከሥጋህ ተለይታ በምትወጣበት
ቀንም ለሌላ አልሰጣትም እኔ እቀበላታለሁ እንጂ› አለው፡፡
‹ወደ አንተ የደረሰ ሁሉ ወደ ቤተክርስቲያንህም የመጣ፣
በአንተም የተማፀነ፣ በእጅህም የተባረከውን ሁሉ
እምርልሃለሁ፡፡ በእኔና በእናቴ ማርያም ስም በማይታበል ቃሌ
ቃልኪዳን ሰጠሁህ፣ መሐላዬንም አላጎድልብህም› አለው፡፡
አባታችንም ይህን ሰምቶ ፈጽሞ ተደሰተ፡፡
‹‹በሌላም ጊዜ ዳግመኛ ጌታችን ደም ግባቱ ያማረ፣ ልብሱም
የመስቀል ምልክት የሆነ ንጹሕ አክሊል በራሱ የተቀዳጀ
ጎልማሳ ሆኖ በፊቱ ቆመ፡፡ ‹ልመናህን እፈጽምልህ ዘንድ እነሆ
ወደ አንተ መጣሁ› አለው፡፡ ‹…እንደ አንተ በዓሌን ያደረገውን
እምረዋለሁ፣ የብርሃን ልብስንም አለብሰዋለሁ…› ብሎ
ቃልኪዳን ከሰጠው በኋላ ሁለመናው በመለኮት ጨውነት
ይጣፍጥ ዘንድ አውራ ጣቱን አጠባው፡፡ ከዚህም በኋላ ከእርሱ
ተሰወረ፡፡ እንዲሁም በሌላ ጊዜ እንዲህ እያለ መለነ፡- ‹ጌታዬ
ፈጣሪዬ ሆይ! በዓልህን አድርግ አንድ አንተ የምትወደውን
ግለጥልኝ› አለ፡፡ ጌታም ‹የሞቴን መታሰቢያ ያደረገ እንደ እኔ
ነፍሳትን ከደይን ያወጣል፣ ‹በእኔ የሚያምን እኔ የምሠራውን
ይሠራል፣ ከዚያም የበለጠ ይሠራል› ብዬ በወንጌሌ
እንደተናገርሁ› አለው፡፡›› ‹‹ክርስቲያኖች ሁሉ የፈጣሪያችንን
የመድኃኔዓለም ክርስቶስን የመታሰቢያ በዓሉን እናድርግ፡፡
የአባቶቻችን የሐዋርያት፣ የጻድቃን፣ የሰማዕታት፣ የመላእክት
መታሰቢያቸው ባረፉበት በተሾሙበት ቀን ይከበራል፡፡ እነርሱን
የፈጠራቸው እርሱ መድኃኔዓለም ነው፣ ያከበራቸው፣ ከፍ ከፍ
ያደረጋቸው፣ ስማቸውን ለጠራ መታሰቢያቸውን ያደረገ
እንደሚድን ቃልኪዳን የሰጣቸው እርሱ ነው፡፡ የመድኃኔዓለምን
የሞቱን መታሰቢያ ያደረገ ግን የተኮነኑ ነፍሳትን ከደይን
ያወጣል፣ በሞቱም ጊዜ ሥቃይን አያያትመ፡፡›› ‹‹ጌታችንም
ለመባዓ ጽዮን እንዲህ አለው፡- ‹መታሰቢያዬንም እንደ አንተ
በየወሩ የሚያደርግ ሁሉ በዓርብ ቀን ብዙ ነፍሳትን ከሲኦል
አወጣለታለሁ፡፡ አንተ ከምታደርገው ከሞቴ መታሰቢያም
ቁራሽ የበላውን፣ ከሩቅም ወሬህን ሰምቶ በልቡ ደስ ያለውና
የወደደውን ከሞቴ መታሰቢያ መድረስ ባይቻለውም እንኳ
እምረዋለሁ፡፡› መባዓ ጽዮንም ስለተሰጠው የምሕረት
ቃልኪዳን እጅግ ደስ ብሎት እንዲህ አለ፡- ‹ያለቸርነቱ በቀር በጎ
ሥራ ለሌለኝ ለእኔ ለኃጢአተኛው ይኽን ሁሉ ስላደረገልኝ
ለእግዚአብሔር ምን እከፍለዋለሁ?› አለ፡፡ ነገር ግን ስሙ
ለዘለዓለም የተባረከ ይሁን አሜን፡፡››
+ + + + + + + + + + + + + + +
ዳግመኛም በዚኽች ዕለት ከሞተ ከ4 ቀን በኋላ ጌታችን
ያስነሣው ቅዱስ አልዓዛር ዓመታዊ መታሰቢያ በዓሉ ነው፡፡
ይኸውም ቅዱስ አልዓዛር የባለ ሽቱዋ የማርያም እንተ
ዕፍረትና የማርታ ወንድም ሲሆን ጌታችን በጣም ይወደው
ስለነበር አልዓዛር መሞቱን ሲሰማ ከእኅቶቹ ጋር
አልቅሶለታል፡፡ ከሞተም ከ4 ቀን በኋላ ከመቃብር
አስተሥቶታል፡፡ ከጌታችን ዕርገት በኋላም አልዓዛርና እኅቶቹ
ቤታቸውን የወንጌል መማርያና የእንግዶች መቀበያ
አድርገውታል፡፡ እርሱ ከሞት በተነሣ በሳምንቱ ጌታችን
ተሰቅሎ በሥጋ ሞተ፡፡ ከትንሣኤውም በኋላ አልዓዛር
ከሐዋርያት ጋር ሆነ፡፡ በ50ኛውም ቀን ከሐዋርያት ጋር
መንፈስ ቅዱስን ተቀብሏል፡፡
አይሁድም ክርስቶስን ያመኑ ክርስቲያኖችን ሲያሳድዱ
አልዓዛርንና እኅቶቹን በቀዳዳ መርከብ ጭነው ወደ ባሕር
ጥለዋቸዋል፡፡ በተአምራት ከሞት ድነው የፈረንሳይ ግዛት
ወደሆነች አንዲት ከተማ ተሰደው በዚያ እየኖሩ የክርስቶስ
ምስክር ሆነዋል፡፡ ሐዋርያት በቆጵሮስ አገር ላይ በአንብሮተ
እጅ ኤጲስ ቆጶስነት ሾሙት፡፡ መንጋውንም በመልካም
አጠባበቅ እየጠበቀ በሹመቱ 40 ዓመት አገልግሏል፡፡
በከተማዋም የመጀመሪያው ጳጳስ በመሆን ወንጌልን እየሰበከ
ሲያገለግል ኖሮ መጋቢት 17 ቀን በሰማዕትነት ዐርፏል፡፡
ቅዱስ አልዓዛር በሰማዕትነት ካረፈ ከብዙ ዘመን በኋላ
ከክርስቲያን ነገሥታት መካከል አንዱ የቅዱስ አልዓዛር ሥጋው
በቆጵሮስ እንዳለ በሰማ ጊዜ ከቆጵሮስ ደሴት ወደ
ቁስጥንጥንያ አፈለሰው፡፡ ሊያፈልሱትም በወደዱ ጊዜ በከበረ
የድንጋይ ሣጥን ውስጥ ሆኖ በምድር ውስጥ ተቀብሮ አገኙት፡፡
በላዩም እንዲህ የሚል ጽሑፍ ነበረ፡- ‹‹ይህ በመቃብር ውስጥ
አራት ቀን ከኖረ በኋላ ከሙታን ለይቶ ላስነሣው ክብር
ይግባውና የጌታችን የኢየሱስ ክርስቶስ ወዳጁ የሆነ የቅዱስ
አልዓዛር ሥጋ ነው፡፡›› ይህንንም ጽሑፍ ባነበቡ ጊዜ ደስ
ተሰኝተው ተሸክመው ወደ ቁስጥንጥንያ አገር ወሰዱት፡፡
ካህናቱም ሁሉ በዝማሬ በክብር ተቀበሉት፡፡ ባማረ ቦታ
አስቀምጠውት ጥቅምት 21 ቀን የፍልሰቱን በዓል
አደረጉለት፡፡ ረድኤት በረከቱ ይደርብን፣ በጸሎቱ ይማረን፡፡
የመድኃኔዓለም ቸርነቱ የመባዓ ጽዮን አማላጅነቱ አይለየን!

=>+*"+<+>††† ግንቦት 26 †††<+>+"*+

<<< በስመ አብ : ወወልድ : ወመንፈስ ቅዱስ : አሐዱ አምላክ . . . አሜን :: >>>
<+> ግንቦት 26 <+>
+*" አቡነ ሃብተ ማርያም ጻድቅ "*+
=>እኒህ ጻድቅ የሃገራችን ኮከበ ገዳም ናቸው:: "ጽድቅና
ትሩፋት እንደ ሃብተ ማርያም" እንዲሉ አበው:: ባሕር ከሆነ
ጣዕመ ሕይወታቸው ጥቂቱን ለበረከት እንካፈል::
+ጻድቁ መካነ ሙላዳቸው ሽዋ (የራውዕይ) ውስጥ ሲሆን
አባታቸው ፍሬ ቡሩክ : እናታቸው ደግሞ ቅድስት ዮስቴና
ትባላለች:: በተለይ ቅድስት ዮስቴና እጅግ ደመ ግቡ : ምጽዋትን
ወዳጅ : ቡርክት ሴት ነበረች:: እንዲያውም ከጻድቁ መወለድ
በፊት መንና ጭው ካለ በርሃ ገብታ ነበር::
+ግን የበቃ ግኁስ አግኝቷት "ከማሕጸንሽ ደግ የሥላሴ ባርያ
አለና ተመለሽ" ብሏት እንደ ገና ተመልሳለች:: ጻድቁን ወልዳ
አሳድጋም እንደ ገና መንና በተጋድሎ ኑራ 7 አክሊላትን ተቀብላ
ዐርፋለች::
+ወደ ጻድቁ ዜና ሕይወት ስንመለስ አቡነ ሃብተ ማርያም ገና
ሕጻን እያሉ ከእናታቸው ጋር ቆመው ሲያስቀድሱ "እግዚኦ
መሐረነ ክርስቶስ" ሲባል ይሰማሉ:: ይሕችን ጸሎት በሕጻን
አንደበታቸው ይዘው ሌሊት ሌሊት እየተነሱ "ማረን እባክህን?"
እያሉ ይሰግዱ ነበር::
+የ5 ዓመት ሕጻን እንዲህ ሲያደርግ ማየቱ በእውነት
ይደንቃል:: ትንሽ ከፍ ብለው በእረኝነት ሳሉም ፍጹም
ተሐራሚና ጸዋሚ ነበሩ:: ጸጋው ስለ በዛላቸውም ልጅ ሆነው
ብዙ ተአምራትን ሰርተዋል:: የፈጣሪውን ስም ያቃለውን አንድ
እረኛም በዓየር ላይ ሰቅለው አውለውታል::
+ከዚያ ግን ለአካለ መጠን ሲደርሱ ወደ ት/ቤት ገብተው :
መጻሕፍትንም አጥንተው መንነዋል:: በአባ መልከ ጼዴቅ እጅ
ከመነኮሱ በሁዋላ የሠሩትን ትሩፋትና የነበራቸውን ተጋድሎ ግን
የኔ ብጤ ደካማ ሰው ሊዘረዝረው አይችልም::
*ባሕር ውስጥ ሰጥመው 500 ጊዜ ይሰግዳሉ::
*በየቀኑ 4ቱን ወንጌልና 150 መዝሙረ ዳዊትን ይጸልያሉ::
(መጽሐፍ ቅዱስን ማንበብ ታላቅ ጸሎት ነው)
*በ40 ቀናት : ቀጥሎም በ80 ቀን አንዴ ብቻ ይመገባሉ::
*ምግባቸው ደግሞ ሣርና ቅጠል ብቻ ነው::
*በየዕለቱ ያለ ማስታጐል ማዕጠንት ያሳርጋሉ:: (ካህን ናቸውና)
*ዘወትር በንጽሕና ቅዱስ ሥጋውን ይበላሉ : ክቡር ደሙን
ይጠጣሉ::
*በፍጹም በልባቸው ውስጥ ቂምን : መከፋትን አላሳደሩም::
+በእነዚህና በሌሎች ትሩፋቶቻቸው ደስ የተሰኘ ጌታም ለጻድቁ
የእሳትና የብርሃን ሠረገላን ሰጥቷቸው በዚያ እየበረሩ
ኢየሩሳሌም ይሔዱ ነበር:: ከብዙ የተጋድሎ ዘመናት በሁዋላም
የክብር ባለቤት መድኃኒታችን ክርስቶስ አዕላፍ መላእክትን
አስከተትሎ መጥቶ አላቸው::
"1.ስለ እኔ ረሃብና ጥምን ስለ ታገስክ:
2.ስለ ምናኔሕ:
3.ስለ ተባረከ ምንኩስናህ:
4.ስለ ንጹሕ ድንግልናህ:
5.ቂምና በቀልን ስላለመያዝህ:
6.ስለ ንጹሕ ክህነትህና ማዕጠንትህ:
7.ቅዱስ ወንጌልን በፍቅር ስለ ማንበብህ 7 አክሊላትን
እሰጥሃለሁ::"
+"በሰማይም ከመጥምቁ ዮሐንስ ጐን : 500 የእንቁ
ምሰሶዎች ያሉበትን አዳራሽ ሰጥቼሃለሁ:: በስምህ የሚለምኑ :
በቃል ኪዳንህ የሚማጸኑትንም ሁሉ እንድምርልህ 'አማንየ!
በርእስየ!' ብዬሃለሁ" አላቸው::
+ቅዱሳን መላእክትም "ሃብተ ማርያም ወንድማችን" ሲሉ
አቀፏቸው:: ጌታ ግን በዚያች ሰዓት አንድም ሦስትም ሆኖ
ታያቸውና አቅፎ 3 ጊዜ ሳማቸው:: ከፍቅሩ ጽናትም የተነሳ
ነፍሳቸው ከሥጋቸው ተለየች:: በዝማሬም ወሰዷት:: {ይህች ቀን
(ግንቦት 26) ለጻድቁ ዕለተ ልደታቸው ናት::}
=>አምላከ አበው ወሰማዕት ጣዕመ ፍቅራቸውን:
ክብራቸውን: ጸጋ በረከታቸውንም ይክፈለን::
=>+"+ እግዚአብሔር ፍርድን ይወድዳልና::
ቅዱሳኑንም አይጥላቸውምና::
ለዘለዓለምም ይጠብቃቸዋል . . .
ጻድቃን ምድርን ይወርሳሉ::
በእርስዋም ለዘላለም ይኖራሉ::
የጻድቅ አፍ ጥበብን ያስተምራል::
አንደበቱም ፍርድን ይናገራል::
የአምላኩ ሕግ በልቡ ውስጥ ነው::
በእርምጃውም አይሰናከልም:: +"+ (መዝ. 36:28-31)
<ወስብሐት ለእግዚአብሔር>

=>+*"+<+>††† ሎሚ 26 ግንቦት እዩ †††<+>+"*+

በሰምኣብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ ኣሃዱ ኣምላክ ኣሜን።
††† ሎሚ 26 ግንቦት እዩ †††
††† #ዓመታዊ_በዓለ_ዕረፍት_ሓ ዋርያ_ቅዱስ #ቶማስ †††
ቶማስ ማለት ጸሓይ ማለት እዩ።ቀዳማይ ስሙ ደዲሞስ እዩ
(ማቴ 10፡30፣ ዮሓ 20፡24 ፣ግብ ሓዋ 1፡13)። ጎይታ ክብ
ምውታት ተፈሊዩ ምስ ተንሰአ ኣብ መበል ሻሙናይ መዓልቱ
ሰንበት መዓልቲ ጎድኒ ጎይታ ዳህሲሱ መለኮት ምስ ኣቃጸሎ
"ጎይታይን ኣምላኸይን "ኢሉ ትንሳኤኡ ኣመነ። ዕርገት ናይ
ኣዴና ቅድስት ድንግል ማርያም ዝርኣየ ድማ ሓዋሪያ ቶማስ
እዩ።ሃገረ ስብከቱ ሕንድኬ (ህንዲ) እዩ። ንሱ ብ 30 ቅርሺ
ተሸይጡ ምስ ናይቲ ሃገር ሃብታም ክልኩዮስ የገልግል ነበረ።
እቲ ሃብታም ካኣ "እንታይ ክትሰርሕ ትክእል ፧"ኢሊ ሓተቶ።
ሓዋሪያ ቶማስ ድማ "ህንጻ ምስራሕ ሓወልቲ ምቅራጽ
ይክእል"በሎ። በዚ ተሰማሚዖም ብዙሕ ገንዘብን ወርቕን
ሃቦ።ኣህዛብ ምኩሓት ስለ ዝኾኑ ካኣ "ጥበብ ዘለዎ ሰብ ረኺበ
"ክብል ናብ ንጉስ ከደ። ቶማስ ድማ ነቲ ገንዘብ ወርቅን
ንድካታትን ነደያትን ሂቡ፣ምሂሩ ኣእመኖም ፣ሰበይቲ ልኩዮስ
፣ምስ ደቃን ኣገልገልታን ኣሚና ተጠምቀት።ልኩዮስ ካብ
መገሽኡ ምስ ተመልሰ "ዝሃነጽካዮ ህንጻ፣ዝቀረጽካዮ ሓወልቲ
ዳኣ ኣበይ ኣሎ፧ ኢሉ ሓተቶ። ሓዋርያ ቶማስ ድማ
"ብገንዘብካን ወርቅካን ዘስራሕካዮም ህንጻታት እዚኦም
እዮም " ኢሉ ነቶም ዝኣመኑ ህዝቢ ኣርኣዮ።ልኪዮስ ድማ
"ተጻዊትለይ "ብምባል ኢዱን እግሩን ኣሲሩ ቆርቦቱ ተቀሊጡ
ክሳዕ ዝግፈፍ ገረፎ።ሑጻ ኣሰኪሙ ውን ካብ ቦታ ናብ ቦታ ኮለል
ከም ዝብል ገበሮ። ሰበይቱ ኣርሰንዋ ነዚ ርእያ ሰንቢዳ ወደቀት
ብኡ ብኡ ድማ ሞተት ። ልክዮስ ካኣ "ሰበይተት ዝሞተት
ብሰንክኽኻ እዩ፣ ስለዚ እንተድኣ ኣሕዊኻያ ኣነ ውን ብኣምላኽካ
ክኣምን እየ በሎ።ጎይታ ንቑስሊ ሓዋርያ ቶማስ ከም ማይ
ኣዝሓሎ። ቅዱስ ቶማስ ካኣ በቲ ዝተገፈ ቆርበቱ ነታ ዝሞተት
ሰበይቲ ተንከያ እሞ ንሳ ካኣ ተንሰአት። ሽዑ ልኪዮስ ብጎይታ
ኣሚኑ ተጠመቐ። ብድሕርዚ ንቆርበቱ ተሰኪሙ ካብ ቦታ ናብ
ቦታ እንዳ ተዘዋውወረ ሕሙማት ፈወሰ፣ሙዉታት
ኣተንስአ፣ንኣህዛብ ኣእሚኑ ከም ዝጥመቑ ገበረ።ሓደ ግዜ
ቀንጣፍያ ትብሃል ዓዲ ምስ በጽሐ ሓደ ሰብኣይ ሸውዓተ ደቁ
ተቀቲሎም ሓዚኑ ረኾቦ እሞ ብቆርበቱ ነቶም ደቂ እቲ ሰብኣይ
ተንኪፉ ኣተስኦም። ኣብ ኢናስም ዝተባህለ ዓዲ ውን ትምህርቱ
ሰሚዖም ተኣምሩ ርእዮም ካብ ንጉስ ክሳብ ገባር ኣሚኖም
ተጠመቁ።ዘራጊ ከሎ ጽሩይ ማይ ዘይስተ ግን ካህናተ ጥዖት
ህዝቢ ብጎይታ እናኣመነ ኽገድፎም ስለ ዝጀመረ ጥቅሞም ስለ
ዝጎደሎም ምስ ንጉስን መኻንንትን ኣባኣስዎ እሞ በዚ ዕለት
ብሰይፈ ሰማዕትነት ተቀበለ ግዚኡ ብ 72 ዓ/ም እዩ።
በረከቱ ጸሎቱ ናይ ሓዋርያ ቅዱስ ቶማስ ምስ ኩሉና ህዝበ
ክርስቲያን ይኩን ።
ኣሜን ኣሜን ኣሜን
ስብሓት ለእግዝኣብሄር
ወለወላዲቱ ድንግል
ወለመስቀሉ ክቡር ይኩን!!!
ኣማኑኤል-ኣርኣያ
ምንጪ ምጽሓፍ መዝገበ ታሪኽ

Thursday, June 2, 2016

ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ነኝ: =>+*"+<+>ግንቦት 25<+>+"*+

ግንቦት 25-
እመቤታችንን በስደቷ ጊዜ አብራት ተሰዳ ድካሟን
የተካፈለቻትና ልጇን መድኃኔዓለምን በጀርባዋ አዝላ ገላውንም
አጥባ ትንከባከበው የነበረችው ቅድስት ሰሎሜ ዕረፍቷ ነው፡፡
+ በዚኽችም ዕለት ጌታችን የደረቁ በትሮችን ያለመለመበት
ዕለት ነው፡፡ ይኸውም የአረገዊ ዮሴፍን በትሮች በአረንጓዴ ቦታ
ላይ ቢተክላቸው ወዲያው ዛፎች ሆኑ፡፡
+ ከበሬዎች ጋር ተጠምደው ሰማዕትነትን የተቀበሉት አቡነ
ሕፃን ሞዐ በዓለ ፅንሰታቸው ነው፡፡
+ ከእንዴና አገር የተገኘው የከበረ ቅዱስ ኮጦሎስ በሰማዕትነት
ዐረፈ፡፡
+ ስብስጣ ከሚባል አገር የተገኘው የከበረ አባ ኄሮዳ
በሰማዕትነት ዐረፈ፡፡
ቅድስት ሰሎሜ፡- ይኽችም ቅድስት የእመቤታችን የአክስት
ልጅ ናት፡፡ እርሷም የማጣት ልጅ፣ የሌዊ ልጅ፣ የሚልኪ ልጅ፣
የካህን አሮን ልጅ ናት፡፡ ማጣትና ሄርሜላ ሶፍያ፣ ማርያምና
ሐና የሚባሉ ሴቶች ልጆችን ወልደዋል፡፡ ቅድስት ሐና ድንግል
ማርያምን ወለደች፣ ድንግል ማርያምም መድኃኔዓለም
ክርስቶስን ወለደች፡፡ ሶፍያ ኤልሳቤጥን ወለደች፣ ኤልሳቤጥም
መጥምቁ ዮሐንስን ወለደች፡፡ ማርያምም ሰሎሜን ወለደች፡፡
እመቤታችን ጌታችንን በወለደችው ጊዜ ቅድስት ሰሎሜ
የእመቤታችን አወላለድ እንደ ሌሎቹ ሴቶች ያለ አወላለድ
መስሏት ነበርና የእመቤታችንን ሆዷን ዳሰሰቻት፡፡ በዚህም
ጊዜ እጇ ተኮማትሮ ተቃጠለ፡፡ ሕፃኑን በዳሠሠችው ጊዜ ግን
እጇ ዳነችላት፡፡ በዚህም እመቤታችን አምላክን እንደወለደች
ዐወቀች፡፡ እመቤታችንን በስደቷ ጊዜ አብራት ተሰዳ ድካሟን
ተካፍላታለች፡፡ ጌታችንንም በጀርባዋ አዝላ፣ በክንዶቿ
ታቅፋዋለች፡፡ ገላውንም የምታጥብበትም ጊዜ ነበር፡፡ ጌታችን
ሰው በሆነበት ወራት ሁሉ ከእርሱ አልተለየችም፡፡
በመከራውም ጊዜ እያለቀሰች ተከትላዋለች፡፡ ከሙታን ተለይቶ
በተነሣም ጊዜ ወደ መቃብሩ ገስግሳ ትንሣኤውን ከሐዋርያት
ቀድማ ያየች ናት፡፡ በ50ኛም ቀን መንፈስ ቅዱስ በወረደ ጊዜ
ከሌሎቹ ሴቶች ጋር ሆና ሰማያዊ ሀብትን ከተቀበለች በኋላ
ቅድስት ሰሎሜ በጌታችንም ስም ወንጌልን አስተራለች፡፡
ብዙዎችንም አሳምና ያስጠመቀች ድንቅ እናት ናት፡፡
ከአይሁድም የሚደርስባት መከራ በጸጋ ተቀብላ ግንቦት 25
ቀን ዐርፋለች፡፡ የቅድስት ሰሎሜ ረድኤት በረከቷ ይደርብን፣
በጸሎቷ ይማረን፡፡
+ + + + + + + + + + + + + + +
ሰማዕቱ ቅዱስ ኮጦሎስ፡- የዚኽም ቅዱስ ወላጆቹ
እግዚአብሔርን የሚፉ ደጋግ ክርስቲያኖች ናቸውና ጌታችንን
ልጅ እንዲሰጣቸው አጥብቀው ከለመኑትና እርሱም የተባረከ
ልጅ ከሰጣቸው በኋላ ልጃቸውን በሃይማኖት በምግባር
አሳደጉት፡፡ አባቱም የእንዴናው ገዥ መኮንን ነው፡፡
ቅዱስ ኮጦሎስም ለራሱ ሥርዓትን በመሥራት በቀን አንድ
መቶ በሌሊትም አንድ መቶ ጸሎታትን ይጸልያል፡፡ ዕድሜውም
በደረሰ ጊዜ ወላጆቹ ሊያጋቡት ሲሹ እርሱ ግን እምቢ አላቸው፡፡
ነገር ግን ወላጆቹ ታናሽ እኅቱ የሆነችውን ሴት ልጃቸውን
ከአርያኖስ ጋር አጋቧት፡፡ አባቱም ከሞት በኋላ ቅዱስ ኮጦሎስ
የስደተኞችና መጻተኞች መቀበያ ቤት ሠርቶ እንግዳን ሁሉ
የሚቀበል ሆነ፡፡ ከዚኽም በኋላ የጥበብ መጻሕፍትን ተምሮ
ሐኪም ሆነ፡፡ ሕሙማንም ወደ እርሱ በመጡ ጊዜ ያለምንም
ዋጋ የሚፈውሳቸው ሆነ፡፡
ከሃዲው ዲዮቅልጥያኖስም ጌታችንን በካደ ጊዜ አርያኖስ
ስለሹመቱ ከንጉሡ ጋር ተስማምቶ ሰማዕታትን የሚያሠቃይ
ሆነ፡፡ በዚኽም ጊዜ ቅዱስ ኮጦሎስ ሰማዕት ይሆን ዘንድ
ተመኝቶ ወደ ሰማዕትነት አደባባይ ወጥቶ አርያኖስን፣ ንጉሡን
ዲዮቅልጥያኖስንና አለቆቹን ሁሉ ስለ ጣዖት አልኮአቸው
ሰደባቸው፣ ጣዖታቱንም ሰደበ፡፡ አርያኖስም ስለ እኅቱ ብሎ
በቅዱስ ኮጦሎስን ከእሥር ፈታው፡፡ ከአርያኖስም በኋላ ሌላ
መኮንን በተሾመ ጊዜ የቅዱስ ኮጦሎስን ዜና እና ገድል ነገሩት፡፡
ጭፍራ ልኮ ወደ እርሱ ካስመጣው በኋላ ለአማልክት
እንዲሰግድ አስገደደው፡፡ ቅዱስ ኮጦሎስም ‹‹ከዕውነተኛው
አምላክ ከክርስቶስ በቀር የሚገዙለት አምላክ የለም፣ ለእርሱ
ብቻ እሰግዳለሁ›› አለው፡፡ በዚኽም ጊዜ መኮንኑ ተቆጥቶ ልዩ
ልዩ በኾኑ ሥቃዮች አሠቃየው፡፡ ነገር ግን የታዘዘ መልአክ
እየመጣ ቅዱስ ኮጦሎስን ከቁስሉ ሁሉ ይፈውሰውና ያጽናናው
ነበር፡፡ ጌታችንም በዚኽ ቅዱስ እጆች ብዙ ድንቅ ድንቅ
ተአምራትን አደረገ፡፡
መኮንኑም ቅዱስ ኮጦሎስን ማሠቃየት በሰለቸው ጊዜ አንገቱን
በሰይፍ ይቆርጡት ዘንድ አዘዘ፡፡ እንደትእዛዙም ሰየፉትና
የሰማዕትነት ፍጻሜው ሆነ፡፡ ከሥጋውም ብዙ ተአምራት
ተገልጠው ታዩ፡፡ የሰማዕቱ የቅዱስ ኮጦሎስ ረድኤት በረከቱ
ይደርብን፣ በጸሎቱ ይማረን፡፡
+ + + + + + + + + + + + + + +
ሰማዕቱ አባ ኄሮዳ፡- ይኽም ቅዱስ አባ ኄሮዳ ከሕጻንነቱ
ጀምሮ በፈሪሃ እግዚአብሔር ያደገ ነው፡፡ በዘመኑም ከሃዲው
ንጉጉሥ ዲዮቅልጥያኖስ ነግሦ ነበርና አባ ኄሮዳ አንድ ቀን
ተኝቶ ሳለ ስለዚኽች ከንቱ አላፊ ዓለም አሰበ፡፡ ጌታችን ‹‹ይኽን
ዓለም ያልካደ ሊያገለግለኝ አይችልም›› ያለውን አስታውሶ
በስሙ ሰማዕት ይኾን ዘንድ ወደደ፡፡ ይኽንንም በልቡ ሲያስብ
ሊቀ መላእክት ቅዱስ ሚካኤል ወደ እርሱ መጥቶ ‹‹የከበርክና
የተመሰገንክ ኄሮዳ ሆይ! ሰላም ለአንተ ይሁን፡፡ እግዚአብሔር
የክብር ዙፋን አዘጋጅቶልሃልና እኔም የመላእክት አለቃ
ሚካኤል ወደ ፍርድ አደባባይ ከአንተ ጋር እሄዳለሁ፣
ከመከራውም አጸናሃለሁና ሰማዕትነትህን በድል ትፈጽማለህ››
ብሎት ወደ ሰማይ ዐረገ፡፡
ከዚኽም በኋላ ቅዱስ አባ ኄሮዳ ወደ ምዕራባዊ ክፍል ወጥቶ
ከጸለየ በኋላ ወደ ፍርድ አደባባይም ሄዶ ‹‹እኔ የክብርን ባለቤት
ክርስቶስን የማመልክ ክርስቲያን ነኝ›› ብሎ በግልጥ ጮኸ፡፡
ከሃዲው መኮንን ሉክያኖስም ይዞ የመጣበትን ጠየቀው፡፡ አባ
ኄሮዳ ከብሕንሳ አውራጃ ስብስጣ ከምትባል አገር እንደሆነና
አስቀድሞም የምድራዊ ንጉሥ ባለሟል እንሆነ ነገረው፡፡
መኮንኑም ‹‹ለአማልክት ሠዋና ብዙ ገንዘብ ሰጥቼህ
ከጭፍሮቼ ሁሉ የበላይ አድርጌ ልሹምህ›› አለው፡፡ አባ ኄሮዳ
ግን ስለ አምኮተ ጣዖቱ ሉክያኖስን ገሠጸው፣ ጣዖታቱንም
ረገመበት፡፡ መኮንኑም እጅግ ተቆጥቶ እሾህ ባላቸው የብረት
ዘንጎች በጽኑ አስደበደበው፣ ከሥቃዩም የተነሣ የቅዱሱ ደሙ
እንደውኃ ፈሰሰ፡፡ ጌታችንም መልአኩን ልኮ ፈወሰውና ፍጹም
ጤነኛ አደረገው፡፡ ዳግመኛም ልዩ ልዩ በሆኑ ሥቃዮችም
አሠቃየው፡፡ ይኽንንም ተአምር ያዩ ሰዎች ‹‹በአባ ኄሮዳ
አምላክ በክርስቶስ አምነናል›› ብለው እየመሰከሩ ሰማዕትነትን
ተቀበሉ፡፡ ቁጥራቸውም ሠላሳ ሺህ አምስት መቶ ሆነ፡፡
መኮንኑም አባ ኄሮዳን ማሠቃየት በሰለቸው ጊዜ ራሱን በሰይፍ
እንዲቆርጡት አዘዘ፡፡ በዚኽም ጊዜ ጌታችን ለአባ ኄሮዳ
ተገለጠለትና ‹‹በችግርና በመከራ ውስጥ ያለ ሰው ቢኖር
በስምህ ቢማጸን ፈጥኖ ከችግሩና ከመከራው ይድናል›› የሚልና
ሌላም ብዙ ታላቅ የምሕረት ቃልኪዳን ገባለት፡፡ ከዚኽም
በኋላ አባ ኄሮዳ ወደ ሕዝቡና ወደ ሰያፊዎቹ ተመልሶ ካረፈ
በኋላ ስለ ሥጋው ነገራቸው፡፡ በታላቅ ደስታም ተመልቶ
ለሰያፊዎቹ ‹‹የታዘዛችሁትን ፈጽሙ›› ብሎ አንገቱን አውጥቶ
ሰጣቸው፡፡ በዚኽችም ዕለት ሰማዕትነቱን በድል ፈጽሞ
አስቀድሞ ጌታችን ቃል የገባለትን የድል አክሊል ተቀዳጀ፡፡ ከ3
ወርም በኋላ ቅዱስ ሥጋውን ወደ አገሩ ወስደው ያማረች ቤተ
ክርስቲያን ሠርተው በውስጧ አኖሩት፡፡ ከሥጋውም ብዙ
ተአምራት ተገልጠው ታዩ፡፡ ለሕሙማንም ፈውስ ሆነ፡፡ የአባ
ኄሮዳ ረድኤት በረከቱ ይደርብን፣ በጸሎቱ ይማረን፡፡
+ + + + + + + + + + + + + + +
አቡነ ሕፃን ሞዐ፡- በአባታቸው አርከሌድስ እናታቸው ትቤ ጽዮን
ይባላሉ፡፡ የተወለዱት ጥር 25 ነው፡፡ አቡነ ሕፃን ሞዐ እና ከእነ
አቡነ ተክለ ሃይማኖት ጋር የሥጋ ዝምድና አላቸው፡፡ ይኸውም
አባታቸው አርከሌድስና ጸጋ ዘአብ ወንድማማቾቸ ናቸው፡፡
አርከሌድስና ጸጋ ዘአብ ሌሎች ሌሎች 4 ወንድሞች አሏቸው፡፡
እነርሱም እንድርያስ፣ ዘርዐ አብርሃም፣ ቀሲስ ዮናስ እና ቀሲስ
ዮሐንስ ናቸው፡፡ አርከሌድስ ሕፃን ሞዐን ይወልዳል፣ ጸጋ ዘአብ
ተክለ ሃይማኖትን ይወልዳል፣ እንድርያስ ሳሙኤል ዘወገግን፣
ዘርዐ አብርሃም ታላቁ አኖሬዎዮስን፣ ቀሲስ ዮናስ
ገላውዲዮስንና የፈጠጋሩን ማትያስን፣ እና ቀሲስ ዮሐንስ
ዜናማርቆስን ይወልዳሉ፡፡ እነዚህ የከበሩ ቅዱሳን አባቶቻችን
በእናታቸውም ወገን ቢሆን እንዲሁ በዝምድና የተቆራኙ
ናቸው፡፡ አቡነ ሕፃን ሞዐ በሌላኛው ስማቸው ሕፃን ዘደብረ
በግዕ ተብለውም ይጠራሉ፡፡ ይኸውም የደብረ በግዕን ገዳም
የመሠረቱት እርሳቸው ስለሆኑ ነው፡፡ ከ47ቱ የሀገራችን
ቀደምት ቅዱሳን ውስጥ አንዱ ናቸው፡፡ በመንዝና በተጉለት
የሚገኙ ታላላቅ ገዳማትን አብዛኞቹን የመሠረቷቸው አቡነ
ሕፃን ሞዐ ናቸው፡፡ ጻድቁ በክፉዎች ወሬና ሴራ ምክንያት ከበሬ
ጋር ተጠምደው ሰማዕትነት የተቀበሉ አባት ናቸው፡፡ ከበሬ ጋር
ሲታረሱ ውለው በእጅጉ ከደከማቸው በኋላ በኃይል የተነፈሱባት
ምድሪቱ ዛሬም ድረስ ልክ እንደሰው የሚሞቅ ትንፋሽ
ታወጣለች፡፡ ያም በጻድቁ እስትንፋስ አምሳል ከመሬት ውስጥ
የሚወጣው እስትንፋስ ለአስም በሽታ መድኃኒት ሆኖ ብዙዎችን
እየፈወ ነው፡፡ ገዳማቸው ከደብረ ብርሃን ከተማ በእግር የ2
ሰዓት መንገድ ርቀት ላይ ይገኛል፡፡ ይኸውም ከወንይዬ ተክለ
ሃይማኖት ገዳም አጠገብ ነው፡፡ ረድኤት በረከታቸው ይደርብን፣
በጸሎታቸው ይማረን፡፡