ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ነኝ

ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ነኝ
ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ነኝ

Tuesday, June 14, 2016

=>+*"+<+>††† ወደ ምስራቅ ተመልከቱ †††<+>+"*...

"ወደ ምስራቅ ተመልከቱ ማለት ምን ማለት ነው"??
በኦርቶዶክስ። ተዋህዶ ሀይማኖታችን ቤተ ክርስቲያን
የምታንፀው ምስራቁን አቅጣጫ ጠብቃ ነው እንድሁም
ከቤተ ክርስቲያኑ ጋር አብሮ የሚሰራው ቤተለሄም። በስተ
ምስራቅ በኩል ይደረጋል በፆለት ሰአትም ወደ ምስራቅ
ዙረን ነው የምንፀልየው በስረአተ ቀብር ላይም የሞተ
ሰው ሲቀበርእራሱ ውደ ምዕራብ እግሩ ወደ ምስራቅ።
ሆኖ ይቀበራል።ሌላው ዳቆኑ በስረአተ ቅዳሴው ላይ ወደ
ምስራቅ ተመልከቱ ይላል ለምን??
፩ የአዳም አባታችን ጥንተ ርስተ ገነት በምስራቅ ናት ዘፍ
2*8 ፪÷፰ ይች እርስታችን በአዳም በደል ምክንያት
በክሩቤል ሰይፍ ተዘግታ ስትኖር ሞትን ድል አድርጎ
በደልን ክሶ ጌታችን መዲሀኒታችን እየሱስ ክርስቶስ በሞቱ
ከፈተልን ሉቃ 23*43። ፳፫*፵፫ ወደ ምስራቅ በዞርን
ቁጥርወደ ገነት ለመግባት የተሰጠን ተስፍፋ ትዝ ይለናል
የተከፈተችውም ቤታችን ገነት በእምነት ውለል ብላ
ትታየናለች በክርስቶስ ያገኘነውን ፀጋ እናስባለን
ምድራዊያን አለመሆናችንንም እናስባለን
፪ ጌታ የተውለደው በምስራቅ ነው
ሰበአሰገል ኮኩቡን ያዩት በምስራቅ ሲሄን ያኮከብ
የምህረት እግዝያብሄር ምሳሌ ነው እርሱን ወደ
እግዝያብሄር እንዳደረሳቸው ሁሉ እኛንም ወደ ለመለመው
መስክ ይመራናል ማቴ ፳፪*፲፬ 22*14 ወደ ምስራቅ
በዞርን ቁጥር። የጌታን መውለድነ ያደረገልንን ውለታ
ይታውሰናል የምህረት ኮከብ እየመራን መሆኑን ትዝ
ይለናል
፫ ምስራቅ የእመቤታችን ምሳሌ ነው
ከምስራቅ ጨለማውን የሚገፈው።ፀሀይ እንደሚውጣ
ሁሉ ከእመቤታችን ከድንግል ማርያምም የአለም
የሀጥያት ጨለማ የሚገፍ ፀሀይ ፅድቅ እየሱስ ክርስቴስ
ውጥቷል። ተገኝቷል ለእናንተ ስሜ የምትፈሩ የፅድቅ
ፀሀይ ትወጣላችሁአለች። ሚል ፬*፩ 4*1 ህዝ ፵፬*፩÷፬
44*1-4 ነብዩ ህዝቀየልም እመቤታችንን ያያት በምስራቅ
ነው ስለዚህ ውደ ምስራቅ በዞርን ቁጥር እመቤታችንን
እናስታውሳለን የፅድቅ ፀሀይ ክርስቶስ ስለተውለደልን
በጨለማ አለመሆናችን ትዝ እያለን ከሀጥያት እንርቃለን
፬ የአለም ድህነት የተገኘው በምስራቅ ነው
ጌታ የተስቀለውና አለምን ያዳነው በምስራቅ ነው እየሩስ
አሌም ምስራቃዊት ከተማ ናት በመሆኑ ውደ ምስራቅ
በዞርን ቁጥር የተሰቀለውን ክርስቴስንና የተከፈለልንን ዋጋ
እናስባለን
፭ ክርስትናና ቤተ ክርስቲያን የተመሰረቱት በምስራቅ ነው
የመጅመሪያው ቤተ ክርስቲያን የተመስረተውበ በእየሩስ
አሌም ሲሆንውንጌል የተሰበከው ከዚህ በመነሳቱ ነው
ስለዚህ ውደ ምስራቅ ስንዞር የቤተ ክርስቲያን ጉዞ
የውንጌል መስፋፋትን የህዝብ ና የአለም መዳን ትዝ
ይለናል
፮ ምስራቅ የእግዝያብሄር ክብር መገለጫ ነው
ኢሳ ፳፰*፲፫ 28*13። እግዝያብሄር በምስራቅ
የእስራኤልንም አምላክ የእግዝያብሄርንም ስም በባህር
ደሴቶች አከበሩ ህዝ ፵፫*፪ 43*2 የእስራኤልንም
አምላክ ክብር ከምስራቅ መንገድ ውጣ ።
፯ የጌታ ዳግም ምፅአትም ከምስራቅ ነው
ዘካ ፲፬*፲፬ 14*14
ውስብሀት ለእግዝያብሄር አሜን

No comments:

Post a Comment