ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ነኝ

ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ነኝ
ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ነኝ

Tuesday, June 14, 2016

=>+*"+<+>††† ወደ ምስራቅ ተመልከቱ †††<+>+"*...

"ወደ ምስራቅ ተመልከቱ ማለት ምን ማለት ነው"??
በኦርቶዶክስ። ተዋህዶ ሀይማኖታችን ቤተ ክርስቲያን
የምታንፀው ምስራቁን አቅጣጫ ጠብቃ ነው እንድሁም
ከቤተ ክርስቲያኑ ጋር አብሮ የሚሰራው ቤተለሄም። በስተ
ምስራቅ በኩል ይደረጋል በፆለት ሰአትም ወደ ምስራቅ
ዙረን ነው የምንፀልየው በስረአተ ቀብር ላይም የሞተ
ሰው ሲቀበርእራሱ ውደ ምዕራብ እግሩ ወደ ምስራቅ።
ሆኖ ይቀበራል።ሌላው ዳቆኑ በስረአተ ቅዳሴው ላይ ወደ
ምስራቅ ተመልከቱ ይላል ለምን??
፩ የአዳም አባታችን ጥንተ ርስተ ገነት በምስራቅ ናት ዘፍ
2*8 ፪÷፰ ይች እርስታችን በአዳም በደል ምክንያት
በክሩቤል ሰይፍ ተዘግታ ስትኖር ሞትን ድል አድርጎ
በደልን ክሶ ጌታችን መዲሀኒታችን እየሱስ ክርስቶስ በሞቱ
ከፈተልን ሉቃ 23*43። ፳፫*፵፫ ወደ ምስራቅ በዞርን
ቁጥርወደ ገነት ለመግባት የተሰጠን ተስፍፋ ትዝ ይለናል
የተከፈተችውም ቤታችን ገነት በእምነት ውለል ብላ
ትታየናለች በክርስቶስ ያገኘነውን ፀጋ እናስባለን
ምድራዊያን አለመሆናችንንም እናስባለን
፪ ጌታ የተውለደው በምስራቅ ነው
ሰበአሰገል ኮኩቡን ያዩት በምስራቅ ሲሄን ያኮከብ
የምህረት እግዝያብሄር ምሳሌ ነው እርሱን ወደ
እግዝያብሄር እንዳደረሳቸው ሁሉ እኛንም ወደ ለመለመው
መስክ ይመራናል ማቴ ፳፪*፲፬ 22*14 ወደ ምስራቅ
በዞርን ቁጥር። የጌታን መውለድነ ያደረገልንን ውለታ
ይታውሰናል የምህረት ኮከብ እየመራን መሆኑን ትዝ
ይለናል
፫ ምስራቅ የእመቤታችን ምሳሌ ነው
ከምስራቅ ጨለማውን የሚገፈው።ፀሀይ እንደሚውጣ
ሁሉ ከእመቤታችን ከድንግል ማርያምም የአለም
የሀጥያት ጨለማ የሚገፍ ፀሀይ ፅድቅ እየሱስ ክርስቴስ
ውጥቷል። ተገኝቷል ለእናንተ ስሜ የምትፈሩ የፅድቅ
ፀሀይ ትወጣላችሁአለች። ሚል ፬*፩ 4*1 ህዝ ፵፬*፩÷፬
44*1-4 ነብዩ ህዝቀየልም እመቤታችንን ያያት በምስራቅ
ነው ስለዚህ ውደ ምስራቅ በዞርን ቁጥር እመቤታችንን
እናስታውሳለን የፅድቅ ፀሀይ ክርስቶስ ስለተውለደልን
በጨለማ አለመሆናችን ትዝ እያለን ከሀጥያት እንርቃለን
፬ የአለም ድህነት የተገኘው በምስራቅ ነው
ጌታ የተስቀለውና አለምን ያዳነው በምስራቅ ነው እየሩስ
አሌም ምስራቃዊት ከተማ ናት በመሆኑ ውደ ምስራቅ
በዞርን ቁጥር የተሰቀለውን ክርስቴስንና የተከፈለልንን ዋጋ
እናስባለን
፭ ክርስትናና ቤተ ክርስቲያን የተመሰረቱት በምስራቅ ነው
የመጅመሪያው ቤተ ክርስቲያን የተመስረተውበ በእየሩስ
አሌም ሲሆንውንጌል የተሰበከው ከዚህ በመነሳቱ ነው
ስለዚህ ውደ ምስራቅ ስንዞር የቤተ ክርስቲያን ጉዞ
የውንጌል መስፋፋትን የህዝብ ና የአለም መዳን ትዝ
ይለናል
፮ ምስራቅ የእግዝያብሄር ክብር መገለጫ ነው
ኢሳ ፳፰*፲፫ 28*13። እግዝያብሄር በምስራቅ
የእስራኤልንም አምላክ የእግዝያብሄርንም ስም በባህር
ደሴቶች አከበሩ ህዝ ፵፫*፪ 43*2 የእስራኤልንም
አምላክ ክብር ከምስራቅ መንገድ ውጣ ።
፯ የጌታ ዳግም ምፅአትም ከምስራቅ ነው
ዘካ ፲፬*፲፬ 14*14
ውስብሀት ለእግዝያብሄር አሜን

=>+*"+<+>††† 7 †††<+>+"*...

#ሰባት_ቁጥር_ምስጢራት
በመጽሐፍ ቅዱስና በስርዓተ ቤተ-ክርስቲያን አስተምህሮ ስባት
ቁጥር ብዙ ምሳሌ እንዳለው ይታወቃል፡፡ በዕብራዊያን
ዘንድም
ሰባት ፍጹም ቁጥር ነው፡፡ ምሳሌ 24፡16 እግዚአብሔር
ከሰኞ
እስከ እሑድ ያሉትን ቀናት በሰባት ቁጥሮች ወስኗል ሕዝበ
እስራኤል ከግብጽ ባርነት ወጥተው በሲና በርሀ ሲጓዙ ይመሩት
የነበሩት በ7 ደመና እንደነበረ ይታወቃል፡፡ ዘዳ 13፡21 ከዚህ
ቀጥለንም ለቤተ-ክርስቲያን አስተምህሮ የ7 ቁጥር
ምስጢራትን
ምሉዕነትን የሚያስረዱ ልዩ ልዩ ማስረጃዎችን በዝርዝር
እንመለከታለን፡፤
ሀ/ ሰባቱ አባቶች
1. ሰማያዊ አባታችን እግዚአብሔር
2. የነፍስ አባት
3. ወላጅ አባት
4. የክርስትና አባት
5. የጡት አባት
6. የቆብ አባት
7. የቀለም አባት
ለ ሰባቱ ዲያቆናት
1. ቅዱስ እስጢፋኖስ
2. ቅዱስ ፊልጶስ
3. ቅዱስ ጵሮክሮስ
4. ቅዱስ ጢሞና
5. ቅዱስ ኒቃሮና
6. ቅዱስ ጳርሜና
7. ቅዱስ ኒቆላዎስ
ሐ ሰባት የጌታ ቃላት /እኔ ነኝ
1. የሕይወት እንጅራ እኔ ነኝ
2. የዓለም ብርሃን እኔ ነኝ
3. እኔ የበጎች በር ነኝ
4. መልካም እረኛ እኔ ነኝ
5. ትነሣዔና ሕይወት እኔ ነኝ
6. እኔ መንገድና ሕይወት ነኝ
7. እውነተኛ የወይን ግንድ እኔ ነኝ
መ ሰባቱ ሰማያት
1. ጽርሐ አርያም
2. መንበረ መንግሥት
3. ሰማይ ውዱድ
4. ኢየሩሳሌም ሰማያዊት
5. ኢዮር
6. ራማ
7. ኤረር
ሠ ሰባቱ ሊቃነ መላእክት
1. ቅዱስ ሚካኤል
2. ቅዱስ ገብርኤል
3. ቅዱስ ሩፋኤል
4. ቅዱስ ራጉኤል
5. ቅዱስ ዑራኤል
6. ቅዱስ ፋኑኤል
7. ቅዱስ ሳቁኤል
ረ ሰባቱ አብያተ ክርስቲያናት
1. የኤፌሶን ቤተ ክርስቲያን
2. የሰርምኔስ ቤተ ክርስቲያን
3. የጴርጋሞን ቤተ ክርስቲያን
4. የትያጥሮስ ቤተ ክርስቲያን
5. የሰርዴስ ቤተ ክርስቲያን
6. የፊልድልፍልያ ቤተ ክርስቲያን
7. የሎዶቅያ ቤተ ክርስቲያን
ሰ ሰባቱ ተዐምራት
ጌታ እኛን ለማዳን በመስቀል ላይ በተሰቀለ ጊዜ የተፈጸሙ
ተዐምራት
1. ፀሐይ ጨልሟል
2. ጨረቃ ደም ሆነ
3. ከዋክብት ረገፉ
4. ዐለቶች ተሠነጠቁ
5. መቃብራት ተከፈቱ
6. ሙታን ተነሡ
7. የቤተ መቅደስም መጋረጃ
ሸ ሰባቱ የመስቀሉ ቃላት
1. አምላኬ አምላኬ ለምን ተውከኝ
2. አባት ሆይ የሚያደርጉትን አያውቁምና ይቅር በላቸው
3. ዛሬ ከእኔ ጋራ በገነት ትሆናለህ
4. እነሆ ልጅሸ እናትህ እነሆት
5. ተጠማሁ
6. ተፈጸመ
7. አባት ሆይ ነፍሴን በእጅህ አደራ እስጥሃለሁ
ቀ ሰባቱ ምሥጢራተ ቤተ ክርስቲያን
1. ምሥጢረ ጥምቀት
2. ምሥጢረ ሜሮን
3. ምሥጢረ ቁርባን
4. ምሥጢረ ክህነት
5. ምሥጢረ ተክሊል
6. ምሥጢረ ንስሐ
7. ምሥጢረ ቀንዲል
በ ሰባቱ ዐበይት አጽዋማት
1. ዐቢይ ጾም
2. የሐዋርያት ጾም
3. የፍልሰታ ጾም
4. ጾመ ነቢያት
5. ጾመ ገሀድ
6. ጾመ ነነዌ
7. ጾመ ድኅነት
ተ ሰባቱ በእግዚአብሔር ዘንድ የተጠሉ ነገሮች
1. ትዕቢተኛ ዓይን ምሳ 16፡6-19
2. ሃሰተኛ ምላስ
3. ንፁህን ደም የምታፈስ እጅ
4. ክፉ ሃሳብን የምታፈልቅ ልብ
5. ለክፋት የምትፈጥን እጅ
6. የሐሰት ምስክርነት
7. በወንድሞች መካከል ጠብን የምታፈራ ምላስ
ቸ ሰባቱ ፀሎት ጊዜያት
1. ነግህ የጠዋት ጸሎት
2. ሠለስት (የ3 ሰዓት ጸሎት)
3. ቀትር (የ6 ሰዓት ጸሎት)
4. ተሰአቱ (የ9 ሰዓት ጸሎት)
5. ሰርክ (የ11 ሰዓት ጸሎት)
6. ነዋም (የምኝታ ጸሎት)
7. መንፈቀ ሌሊት (የሌሊት ጸሎት)
ኀ ሰባቱ ራሶች (2ኛ ነገ. 17፡6)
1. ኢራን
2. ኢራቅ
3. ግሪክ
4. ሚዳን
5. ግብጽ
6. ጣሊያን
7. እስራኤል
ወስብሐት ለእግዚአብሔር ለዘበቅዱሳኒሁ
ይሴባሕ ይእዜኒ ወዘልፈኒ ወለዓለም ዓለም አሜን፡፡ ወአሜን
ለይኩን ለይኩን፡፡