ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ነኝ

ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ነኝ
ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ነኝ

Wednesday, February 22, 2017

ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ነኝ:=>+*"+<+>††7ቱ ኪዳናት+*"+<+>††

በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሃዱ አምላክ አሜን
እንኩዋን ለእመቤታችን ቅድስት #ድንግል_ማርያም
ዓመታዊ "የኪዳን በዓል" በሰላም አደረሳችሁ +"+"+
+*" 7ቱ ኪዳናት "*+
=>"ተካየደ" ማለት "ተስማማ : ተማማለ" እንደ ማለት
ሲሆን "ኪዳን" በቁሙ "ውል : ስምምነት" እንደ ማለት
ነው:: ይኸውም እግዚአብሔር ከሰዎች ጋር: ሰዎችም ከሰዎች
ጋር የሚያደርጉት ሊሆን ይችላል:: ልዩነቱ የእግዚአብሔር
ቃል ኪዳን ቅዱስና የማይለወጥ መሆኑ ነው::
+እግዚአብሔር አምላክ ከሥነ ፍጥረት ጀምሮ በየጊዜው
ከብዙ ወዳጆቹ ጋር ኪዳንን አድርጉዋል:: ቅድስት ቤተ
ክርስቲያንም እነዚህን ኪዳናት ጥቅልል አድርጋ 7 እንደ ሆኑ
ታስተምራለች:: ስለዚህም ዛሬ ፈጣሪ ቢረዳን እነዚሁን 7
ኪዳናት በጥቂቱ እንመለከታለን::
"ኪዳነ ተካየድኩ ምስለ ኅሩያንየ"
"ከመረጥኩዋቸው ጋር ቃል ኪዳንን አደረግሁ" (መዝ. 88:3)
1. +*" ኪዳነ አዳም "*+
=>አዳም ማለት የእግዚአብሔር ድንቅ ፍጥረት: የፍጡራን
አስተዳዳሪ: ነቢይ: ካህንና ንጉሥ ነው:: እግዚአብሔር ከአዳም
ጋር አስቀድሞ በእጸ በለስ አማካኝነት ቃል ኪዳን ነበራቸው::
ነገር ግን አባታችን በዲያብሎስ ሴራ በመረታቱ ኪዳኑ ፈረሰ::
(ዘፍ. 3:1)
+አዳምና ሔዋን ተጸጽተው ቢያለቅሱ ግን አዲስ የኪዳን
ተስፋ: "ከልጅ ልጅህ ተወልጄ አድንሃለሁ" የሚል ኪዳንን
ተቀበሉ:: (ቀሌምንጦስ: ገላ. 4:4)
2. +*" ኪዳነ ኖኅ "*+
=>ከአዳም እስከ ኖኅ ድረስ ባሉት 10 ትውልድ ዓለም
በዓመፃ ተሞላች:: ቅዱስ ኖኅ በደግነቱ መርከብ ሠርቶ
ቤተሰቡን ሲያተርፍ ዓለም በማየ ሥራዌ ጠፋች:: ከመርከቡ
ከወጣ በሁዋላ ኖኅና እግዚአብሔር በቀስተ ደመና ምልክትነት
ቃል ኪዳን ተጋቡ:: "ኢያማስና ለምድር ዳግመ በማየ አይኅ"
እንዲል:: (ዘፍ. 9:12)
3. +*" ኪዳነ መልከ ጼዴቅ "*+
=>መልከ ጼዴቅ የእግዚአብሔር ካህኑ: የክርስቶስም
ምሳሌው የሆነ የሳሌም ንጉሥ ነው:: በ15 ዓመቱ መንኖ:
አጽመ አዳምን ይዞ: በቀራንዮ በሕብስትና በወይን ያስታኩት
ነበር::
+እግዚአብሔር ለመልከ ጼዴቅ: በሐዲስ ኪዳን ለምትሠራው
ክህነትና ምሥጢረ ቁርባን ምሳሌ አድርጐ በቃል ኪዳን
አትሞታል:: በዚህም ተሰውሮ ይኖራል እንጂ ሞትን እስካሁን
አልቀመሰም:: ይህም ካህኑ መልከ ጼዴቅ ከአብርሃም ጋር
በተገናኙበት ጊዜ ተገልጧል:: (ዘፍ. 14:17, ዕብ. 7:1)
4. +*" ኪዳነ አብርሃም "*+
=>ቅዱስ አብርሃም የሕዝብና የአሕዛብ አባት: ሥርወ
ሃይማኖት: የጽድቅም አበጋዝ ነው:: ስለ ፍቅረ እግዚአብሔር
ሲል ከርስቱና ከወገኖቹ ተለይቶ በቅድስና ኑሯልና
እግዚአብሔር "በዘርሕ አሕዛብ ይባረካሉ" አለው:: (ዘፍ.
12:1) የቃል ኪዳን ምልክትም ይሆነው ዘንድ ግዝረትን
ሰጠው:: (ዘፍ. 17:1-14)
5. +*" ኪዳነ ሙሴ "*+
=>ቅዱስ ሙሴ የነቢያት አለቃ: የእሥራኤል እረኛ:
የእግዚአብሔር ሰው እና ፍጹም ትሑት (የዋህ) ሰው ነው::
በፈጣሪው ትዕዛዝ እሥራኤልን ከግብጽ ባርነት አውጥቶ ለ40
ዘመናት በበርሃ ሲመራቸው ከእግዚአብሔር የኪዳንን ጽላትና
አሠርቱን ትዕዛዛት ተቀብሏል:: (ዘጸ. 20:1, 31:18)
6. +*" ኪዳነ ዳዊት "*+
=>ቅዱስ ዳዊት ሥርወ ነገሥት: ጻድቅ: የዋህና ቡሩክ የሆነ
አባት ነው:: እግዚአብሔር ከእረኝነት ጠርቶ ንጉሥ አድርጐ
ሹሞት "ከሆድህ ፍሬ በዙፋንህ ላይ አኖራለሁ" (መዝ.
131:11) ሲል ምሎለታል:: አክሎም ሰፊ ቃል ኪዳን ሰጥቶ
"አልዋሽህም" ብሎ ሲምልለት እንመለከታለን:: (መዝ.
88:35)
7. +*"+ ኪዳነ ምሕረት +"*+
=>በብሉይ ኪዳን የነበሩ 6ቱ ኪዳናት በዘመናቸው ክቡርና
ሕዝቡን ከመቅሰፍት ይታደጉ የነበሩ ቢሆንም ከሲዖል ማዳን
ግን አልቻሉም:: ስለዚህም አንድ ፍጹም ኪዳን ያስፈልግ
ነበር:: ይህን ፍጹም ኪዳን ይፈጽም ዘንድም ከቅድስት ሥላሴ
አንዱ ወልድ ከሰማያት ወርዶ በድንግል ማርያም ማሕጸን
አደረ::
+በፍጹም ተዋሕዶም በሕቱም ድንግልና ተወልዶ: አድጎ:
ተጠምቆ: አስተምሮ: ሙቶ: ተነስቶና ዐርጐ ሥጋ ማርያምን
በዘባነ ኪሩብ አስቀመጠው:: ኪዳነ ምሕረት (የምሕረት
ኪዳን) የምንለው አንዱ ታዲያ ይሔው ነው::
+የጌታችን መጸነሱ: መወለዱ: መሰደዱ: መጠመቁ:
ማስተማሩ: ሥጋውንና ደሙን መስጠቱ: መሰቀሉ: መሞቱና
መነሳቱ: ማረጉና መንፈስ ቅዱስን መላኩ በአንድ ላይ "ኪዳነ
ምሕረት" ይባላል:: ታዲያ ይህ ሁሉ የተደረገው በሥጋ
ማርያም ነውና የኪዳኑ ባለቤት እመቤታችን ቅድስት ድንግል
ማርያም ናት::
+የእርሷ ኪዳን የ6ቱን አበው ኪዳናት ፍጹም በማድረጉ
የኪዳናት ማሕተም ይባላል:: የድንግል ማርያም ኪዳኗ
ከሲዖልና ከገሃነም ሊታደገን አቅሙ አለውና:: መድኃኒታችን
ክርስቶስ ለድንግል እናቱ ቃል ኪዳኑን ያጸናላት ደግሞ ካረገ
ከዓመታት በሁዋላ ጐልጐታ ላይ ነው::
+እመ ብርሃን በዚያ ቁማ ስለ ኃጥአን ስታለቅስ "እናቴ ሆይ!
በስምሽ ያመነውን: በቃል ኪዳንሽ የተማጸነውን
እምርልሻለሁ" ብሎ ደስ አሰኝቷታልና:: ይሔው በእመ ብርሃን
ምልጃና ቃል ኪዳን ምዕመናን ከመቅሰፍትና ከገሃነመ እሳት
ማምለጥ ከጀመሩ 2ሺ ዓመታት ሆኑ:: ዛሬም እኛ ኃጥአን
ልጆቿ ከእሳት እንደምታድነን አምነን በጥላዋ ሥር
እንኖራለን::
+*" ኢትዝክሪ ብነ አበሳነ (ኃጢአተነ : ወጌጋየነ)
ማርያም እሙ ለእግዚእነ:
በኪዳንኪ: ወበስደትኪ ድንግል ተማሕጸነ:: "*+
"ድንግል ሆይ! ኃጢአታችን: አበሳችንና በደላችንን አታስቢብን
ዘንድ በስደትሽና በኪዳንሽ ተማጽነናል::"
=>የአርያም ንግሥት: የሰማያውያንና ምድራውያን ኁሉ
እመቤት: የአምላክ እናት: ቅድስት: ስብሕት: ክብርት:
ልዕልት: ቡርክት: ፍስሕትና ጥዕምት የሆነች ድንግል ማርያም
የድኅነታችን መሠረት: ላመኑባት አንገት የማታስደፋ እውነተኛ
አማላጅ ናት::
+በዚህች ዕለት የካቲት 16 ስለ ወገኖቿ የሰው ልጆች ፍቅር
በእንባ ያቀረበችውን ልመና የባሕርይ አምላክ የሆነ ልጁዋ
ተቀብሎ በማይዋሽ ንጹሕ አንደበቱ ቃል ኪዳን ገብቶላታል::
በስምሽ ያመነ በቃል ኪዳንሽ የተማመነ እሳትን አያይም
ብሏታል::
=>ቸሩ ልጇ ከበረከተ ኪዳኗ አይለየን:: በዓሉንም የሰላም :
የፍቅርና የበረከት ያድርግልን::
=>የካቲት 16 ቀን የሚከበሩ ዓመታዊ የቅዱሳን በዓላት=
1.ኪዳነ ምሕረት (የሰባቱ ኪዳናት ማሕተም)
2.ቅድስት ኤልሳቤጥ (የመጥምቁ ዮሐንስ እናት /
የእመቤታችን አክስት / የሶፍያ ልጅ)
3.ቅዱስ ገብረ ማርያም ጻድቅ ንጉሠ ኢትዮዽያ (የቅ/ላሊበላ
ወንድም)
=>ወርኀዊ በዓላት
1.ቅዱስ አኖሬዎስ ንጉሥ ጻድቅ
2.አባ አቡናፍር ገዳማዊ
3.አባ ዮሐንስ ወንጌሉ ዘወርቅ
4.አባ ዳንኤል ጻድቅ
=>+"+"+ . . . ኤልሳቤጥም የማርያምን ሰላምታ በሰማች
ጊዜ ፅንሱ በማኅፀንዋ ውስጥ ዘለለ:: በኤልሳቤጥም መንፈስ
ቅዱስ ሞላባት:: በታላቅ ድምፅም ጮኻ እንዲህ አለች:-
አንቺ ከሴቶች መካከል የተባረክሽ ነሽ: የማኅፀንሽም ፍሬ
የተባረከ ነው:: የጌታዬ እናት ወደ እኔ ትመጣ ዘንድ እንዴት
ይሆንልኛል? እነሆ የሰላምታሽ ድምፅ በጀሮየ በመጣ ጊዜ
ፅንሱ በማኅፀኔ በደስታ ዘሎአልና:: ከጌታ የተነገረላት ቃል
ይፈፀማልና ያመነች ብፅዕት ናት:: +"+"+ (ሉቃ. 1:39)
<ወስብሐት ለእግዚአብሔር>

ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ነኝ:=>+*"+<+>†† የእመ ቤታችን የቅድስት ኪዳነ ምህረት የንግስ በዓል ††

""የእመ ቤታችን የቅድስት ኪዳነ ምህረት የንግስ
በዓል"!!!
ኪዳነ ምህረት ማለት የምህረት መሐላ ማለት ነው፡፡
ከ" 33"በዓላተ እግዝእትነ ድንግል ማርያም አንዱ ነው፡፡
እመቤታችንም ከጌታችን መቃብር እየሄደች በምትለምንበት
ጊዜ አይሁድ ለምቀኝነት አያርፉምና ምን ልታመጣብን ነው
በማለት ሊጣሏት ሲመጡ ጌታችንም ከዓይናቸው ሰውሯታል
አይሁድም ጠባቂ ቢያቆሙ እመቤታችን ዕለት ዕለት መሄዷን
አላቋረጠችን እመቤታችንም እንዲህ ብላ ስትጸልይ ልጄ
ወዳጄ ሆይ ከስጋዬ ስጋ ከነፍሴ ነፍስ ነስተህ ሰው በመሆንህ
ዘጠኝ ወር ከ5 ቀን በቻለችህ ማሕጸኔ ከአንተ ጋር ሀገር
ለሀገር ስለ መሰደዴ መትተህ ልምናዬን ትሰማኝ ዘንድ
እለምንሃለሁ አለች በዚህ ጊዜ ንውጽውጽውታ ሆነ መቃብራት
ተሰነጣጠቀ ጌታችንም እልፍ ከእልፍ መላዕክቱ ጋር መጥቶ
ሰላም ለኪ ማርያም ምን እንዳደርግልሽ ትለሚኚኛለሽ
አላት፡፡ እርሷም መታሰቢያዬን ያደረገውን ስለ ስሜ ለችግረኛ
የሚራራውን በስሜ ቤተ ክርስቲያን ያነጻውን መባዕ
የሰጠውን ከሃይማኖት ከፍቅር ጽናት ልጁን በስሜ የጠራውን
ሁሉ ማርልኝ ከሞተ ስጋ ከሞተ ነፍስ አድንልኝ አለችው፡፡
ጌታችንም ይህን ሁለ እንዳደርግልሽ መሐልኩ ለኪ በርእስየ
ወበአቡየ ሕያው ወበመንፈስ ቅዱስ ብሎ ቃል ገብቶላት
አርጓል፡፡
ሌላው በላዔ ሰብ በአማርኛ ሰው በላ ማለት ነው፤ ትክክለኛ
ስሙ ግን ስምዖን ይባላል ቅምር በሚባል አገር የሚኖር
እጅግ ባለጸጋ ነበር፤ እንደ አብርሃም እንግዶችን እየተቀበለ
ድሆችን እየመገበ የሚኖር ጻድቅ ነበር፤ ሰይጣን በዚህ ስራው
ቀናበት ሊፈትነውም በሦስት አረጋዊ ሽማግሌዎች ስላሴ ነን
ብሎ ተገለጠለት ልክ እንደ አብርሃም፤ ሐዋርያው ጳውሎስ
ሰይጣን የብርሃን መልአክ መስሎ ይመጣል እንዳለ፤ እርሱም
ሥላሴ መስለውት ተቀበላቸው ተንከባከባቸውም፤ ምግብ
አቀረበላቸው ምግብ አንበላም የምንጠይቅህን ግን
ትፈጽምልን ዘንድ ቃል ግባልን አሉት ቃል ገባላቸው
እንግዲያውስ የምትወደን ከሆነ አንድያ ልጅህን ሰዋልን
አሉት፤ መጀመሪያ ደነገጠ ኃላ አብርሃም ልጁን ሊሰዋ
አልነበረምን እኔንም ሊፈትኑኝ ይሆናል ብሎ ለማረድ
ተዘጋጀ፤ተው የሚለው ድምጽ አልሰማም፤ አረደው
አወራረደው ይዞላቸው ቀረበ፤ መጀመሪያ ቅመስልን አሉት
ቀመሰው ወዲያው እነዚያ ሰዎች ተሰወሩበት እርሱም
አህምሮውን ሳተ ተቅበዘበዘ ከዚያ በኃላ ምግብ አላሰኘውም
የሰው ስጋ እንጂ መጀመሪያ ቤተሰቦቹን በላ ከዚያም ጓደኞቹን
ጦርና የውኃ መንቀል ይዞ ከቤቱ ወጣ ያገኘውን ሰው እየገደለ
ይበላል የበላቸው ሰው ቁጥር 78 ደረሰ፤ በመንገድ ተቀምጦ
የሚለምን በደዌ የተመታ አንድ ደሃ አገኘ ሊበላው ወደ እርሱ
ተጠጋ ግን ቁስሉን አይቶ ተጸየፈው፤ ደሃውም “ስለ
እግዚያብሔር ከያዝከው ውኃ አጠጣኝ” አለው “ዝም በል
ደሃ” ብሎት አለፈ፤ “ኸረ በውኃ ጥም ልሞት ነው ስለ ጻድቃን
ስለ ቅዱሳን” አለው አሁንም ዝም ብሎት ሄደ ለሦስተኛ ጊዜ
“ስለ አዛኝቷ ስለ እምዬ ማርያም” አለው፤ ሰውነቱን አንዳች
ነገር ወረረው “አሁን የጠራከውን ስም እስኪ ድገመው ስለ
ማን አልከኝ” አለው፤ ስለ አዛኝቷ ስለ እመቤቴ ማርያም
አለው፤ ይህቺስ ደግ እንደሆነች በምልጃዋም ከሲኦል
እንደምታወጣ ህጻን እያለው እናትና አባቴ ይነግሩኝ ነበር፤ በል
እንካ አለው እጁን ዘረጋለት ጥርኝ ውኃ ጠብ አደረገለት ወደ
ጉሮሮው አልወረደም የተሰነጠቀ እጁ ውስጥ ገባ እንጂ፤ በለዔ
ሰብ ከዚያች ደቂቃ በኃላ አዕምሮው ተመለሰለት እንዲህም
አለ “በአንድ ዋሻ ውስጥ ገብቼ ስለ ኃጢያቴ አለቅሳለሁ ስጋዬ
ከአጥንቴ እስኪጣበቅ እጾማለሁ ወዮሊኝ ወዮታም አለቢኝ
አለ፤ ወደ ዋሻ ገባ ምግብ ሳይበላ ውኃም ሳይጠጣ 21 ቀን
ኖሮ በርሃብ ሞተ ይላል ተአምረ ማርያም። ጨለማ የለበሱ
ሰይጣናት እያስፈራሩ እያስደነገጡ ነፍሱን ወደ ሲኦል ሊወስዷት
መጡ፤ እመቤታችን ፈጥና በመካከላቸው ተገኘች፤ ልጄ ወዳጄ
ይህችን ነፍስ ማርሊኝ አለችው እናቴ ሆይ 78 ነፍሳትን የበላ
እንዴት ይማራል አላት፤ የካቲት 16 ቀን በጎለጎታ የገባህልኝ
ቃል ኪዳን አስብ ስምሽን የጠራ መታሰቢያሽን ያደረገን
እምርልሻለው ብለኸኝ የለምን አለችው፤ እርሱም እስኪ
ይህቺን ነፍስ በሚዛን አስቀምጧት አለ ቢያስቀምጧት ጥርኝ
ውኃው መዝኖ ተገኘ፤ ስላቺ ስል ምሬታለው ሰባት ቀን
ሲኦልን አስጎብኝታችሁ ወደ ገነት አግቧት አላቸው። ቦታሽ
እዚህ ነበር እያሉ ሲኦልን አስጎብኝተው ወደ ገነት አገቧት።
ልመናዋ ክብሯ የልጇም ቸርነት ከሁላችን ጋር ይሁን።
ተአምረ ማርያም
ድንግል ማርያም በቃል ኪዳኗ አትለየን