ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ነኝ

ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ነኝ
ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ነኝ

Wednesday, April 6, 2016

ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ነኝ:

።።ረቡዕ የሚፀለይ አምላክን የወለደች የእመቤታችን የድንግል
ማርያም ምስጋና።።
፩የምድር ሁለተኛ የሆንሽ ሰማይ ሆይ የሰማያት ሰራዊት
(መላዕክት) ንዕፁ ነሽ ይላሉ ድንግል ማርያም የምስራቅ ደጅ
ናት ሙሽራዋ ንፁህ የሆነ ንፅህት የሰርግ ቤት ናት አብ በሰማይ
አይቶእንዳቺ ያለ አላግኝምና አንድ ልጁን ላከዉ በአንቺም ሰው
ሆነ ቅድስት ሆይ ልምኝልን
፪አምላክን የወለድሽ እመቤታችን ሆይ ትዉልድ ሁሉ አንቺን
ብቻ ያመሰግኑሻል
፫የእግዚአብሄር ሀገር ከተማ ሆይ ነበያት ድንቅ ድንቅ ነገርን
የተናገሩልሽ ደስ የተሰኙ የፅድቃን ማደሪያ ሆነሻል ና የምድር
ንግስታት ሁሉ በብርሀንሽ ይሄዳሉ ማርያም ሆይ ትውልድ ሁሉ
ያመሰግኑሻል ካንቺ ለተውለደውም ይስግዱለታል ያግኑታልም
ቅድስት ሆይ ለምኝልን
፬የዝናብ ዉሀ የታየብሽ የዕውነት ደመና አንቺ ነሽ አብ የልጁ
ምልክት አደረገሽ መንፈስ ቅዱስ አደረብሽ የልዑል ሀይል
ጋርደሽ ማርያም ሆይ ለዘላለም የሚኖር የአብን ልጅ ቃልን
የወለድሽልን መጥቶም ከሀጥያት አዳነን ደስ የተሰኘህ ሆነህ
ምስራችን ይተናገርክ መልአኩ ገብርኤል ሆይ የተሰጠህ ክብር
ታላቅ ንው ወደኛ ይመጣን የጌታን ልደት ንገርከን ልድንግል
ፀጋን የተመላሽ ሆይ እግዚእብሄር ካንቺ ጋርነውና ደስ ይበልሽ
ብለህ አበሰርካት ቅድስት ሆይ ለምኝልኝ
፭ፀጋን አገኘሽመንፈስ ቀዱስ አደረብሽ የልዑል ህይልም ጋረደሽ
(ፀለለብሽ) ማርያም ሆይ በዕውነት ቅዱሱን ወለድሽ ዐለምን
ሁሉ የሚያድን መጥቶአዳነን ቅድስት ሆይ ለምኝልን
፮አንደበታችን የድንግልን ስራ ያመሰግናል ጌታችንና
ምድሃኒታችን ኢይሱስ ክርስቶስ በዳዊት አገር ከእርስዋ
ስለተወለደ አምላክን የወለድች ማርያምን ዛሬ እናመስግናት
አሕዛብ ኑ ማርያምን እናመስግናት እናት እና ድንግል ሁለቱንም
ሁናልችና ርኩሰት የሌሌብሽ እና የአብ ቃል መጥቶ ካንቺ ሰው
ሆነ ንፅሕት ድንግል ሆይ ደስ ይብልሽ ነውር የሌለብሽ
ፍፅመትና ጉድፍ የሌለብሽ ሙዳይ ሆይ ደስ ይበልሽ፡፡ስለቀደመ
ሰው ሰው አዳም ሁለተኛ አዳም የሆነ የክርስቶስ ማደርያው
የምትናገሪ ገነት ሆይ ደስ ይበልሽ፡፡ከአባቱ ያልተለየ አንድ እሱን
የተሸከምሽ ሆይ ደስ ይበልሽ በክብር ጌጥ ሁሉ ያጌጠ እርሱ
መጥቶ ሰው የሆነብሽ ንፅሕት የሰርግ ቤት ሆይ ደስ ይበልሽ
እሳት ባህሪ ያላቃጠለሽ ዕፀ ጳጦስ ደስ ይበልሽ በኪሩቤል ላይ
የሚቀምጥዉ ሰማያዊ መልኮት በስጋ የተሽከምሽ ገረድ እና
እናት ድንግል እና ሰማይ ሆይ ደስ ይበልሽ፡፡ስለዚህ ንፁሀን
ከሆነ መላዕክት ጋር ብፍፁም ደስታ ደስ ተሰኝተን እናመስግን
በሰማይ ለእግዚእብሄር ምስጋና ይሁንብምድርም ዕርቅ ይሁን
እንበልክብርና ምስጋና ጌትንት ያለው እርሱ አንቺን ወድዋልና
ደስ ይበልሽ፡፡
፯ከቅዱሳን ክብር የማርያም ክብር ይበልጣል፣የአብን ቃል
ለመቀበል በተገባ ተገኝታለች እና፡፡መላዕክት የሚፈሩትን
ትጉሆች በሰማይ የሚያምሰግኑትን ድንግል ማርያም
በማህፀንዋ ተሸከመችው ፣ይህቺ ከኪሩቤል ትበልጣልች፤
ክሶስቱ አካል ለአንዱ ማድሪያ ሁናልችና፡፡የንቢያት ሀገራቸው
እየሩሳሌም ይህቺ ናት ፡፡ ለቅዱሳን ሁሉ የደስታቸው ማድርያ
ናት በጨለማ ና በሞት ጥላ ውስጥ ለሚኖሩ ሰዎች ታላቅ
ብርሀን ወጣላቸው፡፡ በቅዱሳን ላይ የሚያድር እግጻብሄር እኛን
ለማዳን ልዩከሆነች ድንግል ሰው ሆኗልና ኑ ይህን ድንቅ እዩ፡፡
ስለተግለጠልን ሚስጥር ምስጋና አቅርቡ፤ሰው የእምይሆን
ሰውሁኗልና፤ቃልተዋህዷልና ፤ጥንት የሌለው ስጋ ጥንታዊ
ቀዳማዊሆነ፡፡ዘመን የማይቆጠርለት መለኮት ዘመን
ተቆጠረለት፡፡የማይታወቅ ተገለጥ፤ የማይታይ ታየ፤የህያው
የእግዚአብሄር ልጅ በእርግጥ ሰው ሆነ፡፡ትላንት የነበረው፣
ዛሬም ያለው ፣መቼምየሚኖረው ኢየሱስ ክርስቶስ
አንሰግድለትና እናመስግነው ዘንድ አንድ ባህሪ ነው ቅድስት ሆይ
ለምኝልን፡፡
፰ ነብዩ ሕዝቀኤል ስለእርስዋ መስከረ፤ድንቅ በሆነ ታላቅ
ቁልፍ የተዘጋች ደጅ በምስራቅአየሁ አለ ከሀያላን ጌታ
በቀርውድ እርስዋ ገብቶ የወጣ የለምቅድስት ሆይ ለምኝልን፡፡
፱ኖሕትም ደጅም መድሀኒታችን የወለደች ደንግል ናት፡፡ እርሱን
ከወለደች በሃላ እንድ ቀድሞው ብድንግልና ኖራልችና፡፡ መጥቶ
ምህረት ከሌለው ጠላት እጅ ያዳነንጌታን የወለድሽ ሆይ ፤
የማህፀንሽ ፍሬ የተባረከ ነው አንቺ ፍፅመትና የተባረከሽ ነሽ
የዕወነት አምላክ በሆነ በክብር ባለቤት ዘንድ ባለሟልነትን
አግኝተሻልና በምድር ላይ ከሚኖር ሁሉ ይልቅ ገናንነትና ክብር
ላንቺ ይገባል፡፡ የአብ ቃል መጥቶ በአንቺ ሰው ሆነ፡፡ከሰውም
ጋር ተመላለሰ፡፡መሀሪ ይቅር ባይ ሰዉን ወዳጅ ነዉና በልዩ
አመጣጡ አዳነን ቅድስት ሆይ ልምኝልን፡፡
(ሼር በማድረግ ያካፍሉ)

ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ነኝ: ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ነኝ: መጋቢት 27

ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ነኝ: ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ነኝ: መጋቢት 27: አንድ አምላክ በሚሆን በአብ በወልድ በመንፈስ ቅዱስ ስም አሜን መጋቢት 27 ለስም አጠራሩ ክብር ምስጋና ይግባውና ቸሩ አምላካችን መድኃኔዓለም ክርስቶስ ያደረገው ድንቅ ተአምር ይህ ነው፡- በዚህች ዕለት ጌታችን በእ...