ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ነኝ

ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ነኝ
ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ነኝ

Friday, April 22, 2016

የሕማማት ጥያቄዎችና መልሶቻቸው

የሕማማት ጥያቄዎችና መልሶቻቸው
የሕማማት ጥያቄዎችና መልሶቻቸው
1 በሕማማት ለምን መስቀል አንሳለምም ወይም
አናማትብም ?
የመስቀል ክብር እና ኃይል የታወቀው ጌታ በመስቀለ ከተሰቀለ
በኋላ ነው በሰሞነ ሕማማት ከሰኞ እስከ አርብ ያሉት ቀናት
የዓመተ ፍዳ መታሰቢያ ናቸው በነዚህ ዘመናት ሰዎች
የመስቀልን አገልገሎት እንዳልጀመሩ ለማሳየት በሰሞነ
ሕማማት በቤተክርስተያን ስርዓት መሰረት መስቀል
መሳለምም
ሆነ የማማተብ ስርዓት የለም
2 በሰሞነ ሕማማት ለምን አንንሳሳምም?
ይሁዳ ጌታውን በመሳም አሳልፎ ሰጥቶአል እኛም እንደ ይሁዳ
ክፋት ካለው መሳሳም መለየታችችንን ለማሰረዳት ከዚሀ
በተጨማሪም ፍፁም ሰላም በዘመነ ፍዳ እንዳልነበረ
ለማሳየት
በሰሞነ ሕማማት እሰከ ምሳሳም የደረሰ ጥብቅ ሰላምታ የለም
3 በሰሞነ ሕማማት የማይፈቀዱ ሌሎቸ ነገሮች ምን ምን
ናቸው ? ማንኛውም ለስጋ የሚያደሉ ተግባሮችን መቀነስ እና
ቢቻለን አበዛኛውን ጊዜአችንን በቤተ እግዚአብሔር የጌታን
መከራ ሕማም በማሰብ በፆም በስግደት በጸሎት ማሳለፍ
በትዳር ያሉ በመኝታ ከመተዋወቅ መታቀብ
ቢቻል አመጋገባችንን ከወትሮው መቀነስ
4 ስለ ሰሞነ ሕማማት በመጽሐፍ ቅዱስ የተጻፈ አለን?
ነብዩ ኢሳይያስ "በእውነት ደዌአችንን ተቀበለ ሕማማችንንም
ተሸክሞአል " ኢሳ53፤4 ይላል ሕማማት የሚለው ቃለ
በቀጥታ
ከመጽሐፍ ቅዱስ ተወሰደ ሲሆን የጌታን መከራ የምናስብበት
ሳምንት ነው የጌታችንን ሞቱን ሕማሙን ማሰብ መዘከር
እንደሚገባ ቅዱስ ጳውሎስ እነዲህ ይላል
" ጌታ እስኪመጣ ድረስ ሞቱን ትናገራላችሁና" 1ቆሮ11፤26
ይህ ሳምንት ለአይሁድና ለመሰሎቻቸው የደስታ ወቅት
ቢሆንም
ለክረስትያኖች በጥልቅ ኅዘን ውስጥ የሚገቡበት ሳምንት ነው
እንዲሀ ተብሎ እንደተጻፈ'' እናንተ ታለቅሳላችሁ ሙሾም
ታወጣላችሁ ዓለም ግን ደስ ይለዋል እናንተም ታዝናላችሁ ነገር
ግን ኃዘናችሁ ወደ ደስታ ይለወጣል'' ዮሐ16፤20
በእርግጥ ኃዘናችን ትንሳኤውን እሰክናይ ለጥቂት ጊዜ ቢሆንም
ግን እናዝናለን በትነሳኤው ደግሞ ደስታውን እንካፈላለን።
ሰኞ አይሁድ እንዴት እንደሚይዙት ለመማከር ክፉ
ጉባኤያቸውን
ጀመሩ
''በዚያን ጊዜ የካህናት አለቆች የሕዝብም ሽማግሎች ቀያፋ
በሚባለው በሊቀ ካህናቱ ግቢ ተሰበሰቡ ጌታ ኢየሱስንም
በተንኮል ሊያስይዙት ሊገሉትም ተማከሩ" ማቴ26፡3_4
ይህንን ጉባዔ ቅዱሰ ዳዊት የከፉዎቸ ጉባዔ እያለ ይጠራዋል
"ብዙ ውሾች ከበውኛልና የክፋተኞች ጉባኤም ያዘኝ"
መዝ21፤16
አይሁድ ሰኞ የጀመሩትን ዕረቡ ውሳኔአቸውን አጠናቀው
በምሴተ
ሐሙስ ከዕራትና ከቁርባን በኋላ ሰይፍና ጎመድ ይዘው መጡ
በፈቃዱ ራሱን አሳልፎ ሰጣቸው ያዙትም እስከ አርብ ስድስት
ሰአት ሲያንገላቱት ቆይተው ከበዙ መከራ በኋላ ሰቀሉት ዘጠኝ
ሰአት ላይ ቅድስት ነፍሱን በፈቃዱ ከቅዱስ ስጋው ለየ ከአሰራ
አንድ ሰአት በፊት ዮሴፍና ኒቆዲሞስ በምስጋና ገንዘው ቀበሩት

ከሕማሙ ከመከራው በረከት ያሳትፈን
ሰላመ እግዚአብሔር ከሁላችን ጋር ይሁን

ሆሳዕና እና ምሳሌነቱ!

ሆሳዕና እና ምሳሌነቱ!
• ጌታችን የታሰሩ አህዮች ለምን መረጠ?
• ሃዋርያት ለምን ልብሳቸው አነጠፉለት ?
• ጌታ ለምን በፈረስ ላይ አልተቀመጠም?
• ዝንባባ የምን ምሳሌ ነው?
• በሆሣዕና በእጃችን እደ ቀለበት ማሰራችን የምን ምሳሌ
ነው?
ቤተ ፋጌ የድሆች መንደር ናት፡- ጌታ የድሆች መንደር ወደደ፡፡
እኛ ድሆቹን ባለ ፀጋ ሊያደርገን ስለኛ ብሎ ራሱን ድሃ ያደረገ
አምላክ ነውና፡፡ቤተ ፋጌ ለእየሩሳሌም በጣም ቅርብ ናት፡፡
እኛም ለቤተ ክርስትያን ቅርብ መሆን አለብን፡፡
እየሩ ሳሌም ቤተ ክርስትያን ናት እንቅረባት ፡፡እየሩ ሳሌም
እመቤታችን ናት እንቅረባት ፡፡ጌታ ቤተሳጌ በደረሰ ጊዜ
የተመሳቀለ መንገድ ቁሞ ሁለቱን ደቀ መዛሙርቱ ላከ *ሁሩ
ሃገረ ቅድመክሙ* ወደ ፊታችሁ ላለው ሃገር ሂዱ ወደ
መንደሪቱ ግቡ አላቸው፡፡
በተመሳቀለ ቦታ መቆሙ፡- ወደ ፊት በመስቀል ላይ
እሰቀላለሁ ሲል ነው፡፡
ሁለቱ ደቀ መዛሙርቱ ሲልካቸው በፊታችሁ ላለው ሃገር ሂዱ
ያን ጊዜ አህያ ከውርንጭላዋ ጋር ታስራ ታገኛላችሁ ፈታችሁ
አምጡልኝ አላቸው፡፡
ጌታችን ብዙ ያልታሰሩ አህዮች እያሉ ለምን የታሰሩትን መረጠ?
አህዮቹ የታሰሩት ሌባ ሰርቆ ነው ያሰራቸው፡፡ ወንበዴ ሰርቆ
ነው ያሰራቸው
አህዮቹ ለጌታ ውለታ ሰርተዋል፡፡ ጌታ ሲወለድ
አሙቀውታልና፡፡ ለጌታ ውለታ ልንመልስ ያልቻልነው እኛ
ሰዎች ብቻ ነን፡፡
የታሰሩት እዲፈቱ የመረጠበት ሚስጥር፡-እኔ ከሃጥአታችሁ
ልፈታችሁ የመጣሁ ነኝ ሲል ነው፡፡
ወንበዴው አህዮቹን ሰርቆ በመንደር እንዳሰራቸው
ዲያብሎስም ለሰው ልጅ በሃጥአት ሰንሰለት ከሲኦል መንደር
አስራቸው ነበርና፡፡
ሃዋርያቱ ሲልካቸው ምን ታደርጋላችሁ የሚላችሁ ሰው ቢኖር
ጌታቸው ይሻቸዋል በልዋቸው አላቸው፡፡ የፈጠራቸው እሱ
ነውና፡፡
ከአህያዋ ጀርባ ሃዋርያት ልብሳቸው አነጠፉለት ለምን?
ለምንስ ኮርቻ አላደረጉለትም? ለምንስ ልብሳቸው መረጡ?
ለስላሳ ህግ የሰራህልን አንተ አባት ነህ ሲሉ ነው፡፡ለስላሳ ህግ
የተባለው ወንጌል ነው
ወንጌል ፍቅር ናት የሚረግማችሁ መርቁ ትላለችና፡፡ልብስ
የሰውነት ነውር ይሸፍናል፡፡ ነውረ ሃጥአታችን የምትሸፍንልን
አምላክ ነህ ሲሉ ነው፡፡ እሱ ልብሳችን ነውና፡፡ ነውራችን
የሚሸፍንልን እሱ ነውና፡፡ችግሩ ግን ነውረ ሃጥአታችን
የሚሸፍንልን ልብስ እርሱ መሆኑን አለማወቃችን ነው፡፡
አብሮን እንዳለ አለማስተዋላችን ነው፡፡ስለዚ እንደ ሃዋርያት
ሃጥአታችንን አስቀድመህም የሸፈንክልን ዛሬም የምትሸፍንልን
ወደፊትም የምትሸፍንልን አምላክ አንተ ነህ ልንለው ይገባል፡፡
ጌታችን በሁለቱ አህያዎች በጥበብ ተቀመጠ፡- በሰው የማይቻል
በእግዚአብሔር ዘንድ ግን የሚቻል መሆኑ ጥበበኛ አባት ሁሉን
የሚችል አባት መሆኑ የሚገልጽ ነው፡፡ አንድም ወንጌልን
ኦሪትና ሃዲስን ሁለቱ አስታርቆ አስማምቶ አንዱን አንዱን
እየመገበ የሚሄድ መሆኑ የሚያመለክት ነው፡፡
ጌታ ለምን በፈረስ ላይ አልተቀመጠም?
ትንቢትና ምሳሌውን ለመፈጸም ነው፡፡ ት.ዘካ9፡9 ” አንቺ
የጽዮን ልጅ ሆይ፥ እጅግ ደስ ይበልሽ፤ አንቺ የኢየሩሳሌም ልጅ
ሆይ፥ እልል በዪ፤ እነሆ፥ ንጉሥሽ ጻድቅና አዳኝ ነው፤ ትሑትም
ሆኖ በአህያም፥ በአህያይቱ ግልገል በውርጫይቱ ላይ ተቀምጦ
ወደ አንቺ ይመጣል።”
በአህያ መቀመጡ
•ትህትናን ለማስተማር
•የሰላም ዘመን ነው ሲል
•ለፈለጉኝ ሁሉ የቅርብ አምላክ ነኝ ሲል በንጽህና በየዋህነት
ለሚኖሩ መእመናን አድሬባቸው እኖራለሁ ሲል፡፡
•አህያዎች ትሁታን ናቸው ረጋ ብለው ነው የሚሄዱት፤በቀላሉ
ትወጣበታለህ፤በቀላሉ ትይዘዋለህ፤እንደፈለክም ታዝዋለህ፤እኛ
በትእቢት ተይዘን ነው እንጂ በየዋህነት ብንመላለስ እሱ
ያድርብን ነበር፡፡ እኛ የእግዚአብሔር ማደርያ ነንና፡፡
ትልቅዋ አህያ የኦሪት ምሳሌ ነው
1.ትልቅዋ አህያ ሸክም የለመደች ናት ህገ ኦሪትም የተለመደች
ህግ ናትና፡፡
2.የእስራኤል ምሳሌ ነው፡-ትልቅዋ አህያ ሸክም እንደለመደች
ሁሉ እስራኤልም ህግ ለመፈጸም በህግ ለመራመድ የለመዱ
ናቸው፡፡
3.የአዳም ምሳሌ ነው፡- አዳም ሸክም የበዛበት ነበርና
ውርጭላዋ
1.በህገ ወንጌል ትመሰላለች፡-ምክንያቱም ወንጌል ኢየሱስ
ክርስቶስ የመሰረታት የሰራት አዲስዋ ህግ ናትና፡፡
2.በአህዛብ ትመሰላለች፡-ትንሽዋ አህያ ሸክም የለመደች
አይደለችም እንዲሁም አህዛብም ህግህን የመቀበል የለመደ
አይደሉም፡፡ ለህግህ አዲስ ናቸውና፡፡
3.የእመቤታችን ምሳሌ ናት፡- የዓለም ሸክም አቅልላለችና
በእመቤታችን ትመሰለላለች፡፡ እመቤታችን ድህነተ
ምክንያታችን ጌታን የተሸከመች ንጽህት እንከን የሌላት እናት
ናትና፡፡
ህዝቡም ልብሳቸው እያወለቁ በጎዳና አነጡፉለት ለምን?
እንኳን አንተ የተቀመጥክባት አህያም ክብር ይገባታል ብለው
ነው፡፡እስራኤላውያን ጌታ የተቀመጠባት አህያ አከበሩ፡፡ ይህ
ትውልድ ግን ጌታ የተቀመጠባት እመቤታችን ማክበር
ተሳናቸው፡፡ልብሳቸው ማንጠፋቸው፡- ለክብሩ መግለጫ ነው፡፡
ሌሎችም ቅጠል አነጠፉለት፡ ሰስት አይነት ቅጠል አነጠፉለት
ዝንባባ፤የቴመር ዛፍ፤የወይራ ዛፍ አነጠፉለት፡፡
ዝንባባ
1.ዝንባባ፡- ይስሃቅ በተወለደ ጊዜ ደስ ብሎት አብርሃምን
ዝንባባ ይዞ እግዚአብሔር አመስግነዋል፡፡
2.ዝንባባ ደርቆ እንደገና ሂወት ይዘራል፡- የደረቀ ሂወታችን
የምታለመልም አምላክ ነህ ሲሉ ነው፡፡
3.ዝንባባ የሰላም ምልክት ነው፡- የሰላም አምላክ ነህ ሲሉ
ነው
4.ዝንባባ የደስታ መግለጫ ነው፡- አንተ ደስ የምታሰኝ
ሃዘናችንም የምታርቅልን አምላክ ነህ ሲሉ ነው፡፡
5.ዝንባባ እሾሃማ ነው፡- አንተ ህያው አሸናፊ አምላክ ነህ ሲሉ
ነው፡፡
6.ዝንባባ እሳት አይበላውም ለብልቦ ይተወዋል እንጂ፡፡ ጌታም
አንተ ባህሪህን የማይመረመር ነው ሲሉ ነው፡፡
ሆሣዕና በእጃችን እደ ቀለበት ማሰራችን የምን ምሳሌ ነው?
1.ጌታ ለአዳም የሰጠው ቃል ኪዳን ለማስታወስ፡-ከልጅ ልጅህ
ተወልጄ አድነሃለሁ ያለውን የተስፋ ቃል ለማስታወስ፡፡
2.ጌታ ለእመቤታችን የገባላትን ቃል ኪዳን ተምሳሌት ነው
3.ጌታ ለእስራኤላውያን የሰጣቸው ቃል ኪዳን ተምሳሌት ነው
4.ጌታ ለአዳም ከሰይጣን ግዛት ነጻ እንዳወጣው ሁሉ እኛም
ከሰይጣን ግዛት ከመከራ ስጋ ከመከራ ነፍስ ከክፋት ከሃጥአት
አውጣን ማረን ለንስሃ ሞት አብቃን ከቤትህ አትለየን እንደ
ቸርነትህ ይቅር በላን ስንል ከጌታ ደግመን ላናጠፋ ቃል
የምንገባበት ነው፡፡
ስለዚ እንደ ታሰሩ አህዮች መፈታት አለብን፡፡ ሁላችን ታስረናልና
ቤተ ክርስትያን በመሄድ እንድንፈታ እናድርግ፡፡ የታሰሩት ሁሉ
በካህናት አባቶቻችን አማካኝነት እዲፈቱ ልናድርግ ይገባናል፡፡
ለምን ቢባል አምላካችን ይፈልገናል አባታችን አማላካችን
ንጉሳችን ኢየሱስ ክርስቶስ ይፈልገናል፡፡ ጌታ ጸጋውን አብዝቶ
ለዘላለሙ ከቤቱ አይለየን የነጻነት አባት ካለን ሱስና ልማድ ሁሉ
ነጻ አድርጎ ለሱ እንድንገዛ እርሱ ይርዳን
አሜን ተባረኩ መልካም በዓል፡፡

ሆሣዕና

።።።።።።ሆሳዕና።።።።። ።።
«ሆሳዕና» ቃሉ ከሁለት አረማይክ ቃላት የተሰራ ሲሆን
ትርጉም
«እባክህ እርዳ፣ አሁን አድን» ማለት ነው። እብራይስጡም
ይህንኑ ቃል ወርሶ « הושענא » ሆሻአና ሲል ይገኛል። አዎ
«አሁን አድን፣ እባክህ እርዳን» ብሎ የአዳም ዘር ያጣውን
ልጅነትና የደረሰበትን ሞት ለመላቀቅ የሚያሰማው የጩኸት
ድምጽ ነው፣ «ሆሳዕና»!!!
ዳዊት ነቢይ በመንፈስ ቅዱስ ተመልክቶ ማዳኑን ሲጣራና አሁን
ናልን ሲል ከዘመናት በፊት አድምጠነዋል። የውስጥ ዓይኖቹ
ሩቅ አይተዋል። ማዳኑንም ሽተው እንዲህ ሲል ዘምሮለታል።
«አቤቱ፥ እባክህ፥ አሁን አድን አቤቱ፥ እባክህ፥ አሁን አቅና»
መዝ ፻፲፰፣፳፭
ያ ማለት ደግሞ « אָנָּ֣א יְ֭הוָה הֹושִׁ֘יעָ֥ה נָּ֑א אָֽנָּ֥א
יְ֝הוָ֗ה הַצְלִ֘יחָ֥ה נָּֽא » አና ያኽዌ ሆሳአና አና ያኽዌ
ሆስሊኻ ና» የሚለው የእብራይስጡ ቃል ነው።
ሆሳዕና እና ምሳሌነቱ!
• ጌታችን የታሰሩ አህዮች ለምን መረጠ?
• ሃዋርያት ለምን ልብሳቸው አነጠፉለት ?
• ጌታ ለምን በፈረስ ላይ አልተቀመጠም?
• ዝንባባ የምን ምሳሌ ነው?
• በሆሣዕና በእጃችን እደ ቀለበት ማሰራችን የምን ምሳሌ
ነው?
ቤተ ፋጌ የድሆች መንደር ናት፡- ጌታ የድሆች መንደር ወደደ፡፡
እኛ ድሆቹን ባለ ፀጋ ሊያደርገን ስለኛ ብሎ ራሱን ድሃ ያደረገ
አምላክ ነውና፡፡ቤተ ፋጌ ለእየሩሳሌም በጣም ቅርብ ናት፡፡
እኛም
ለቤተ ክርስትያን ቅርብ መሆን አለብን፡፡
እየሩ ሳሌም ቤተ ክርስትያን ናት እንቅረባት ፡፡እየሩ ሳሌም
እመቤታችን ናት እንቅረባት ፡፡ጌታ ቤተሳጌ በደረሰ ጊዜ
የተመሳቀለ መንገድ ቁሞ ሁለቱን ደቀ መዛሙርቱ ላከ *ሁሩ
ሃገረ ቅድመክሙ* ወደ ፊታችሁ ላለው ሃገር ሂዱ ወደ
መንደሪቱ ግቡ አላቸው፡፡
በተመሳቀለ ቦታ መቆሙ፡- ወደ ፊት በመስቀል ላይ
እሰቀላለሁ ሲል ነው፡፡
ሁለቱ ደቀ መዛሙርቱ ሲልካቸው በፊታችሁ ላለው ሃገር ሂዱ
ያን ጊዜ አህያ ከውርንጭላዋ ጋር ታስራ ታገኛላችሁ ፈታችሁ
አምጡልኝ አላቸው፡፡
ጌታችን ብዙ ያልታሰሩ አህዮች እያሉ ለምን የታሰሩትን መረጠ?
አህዮቹ የታሰሩት ሌባ ሰርቆ ነው ያሰራቸው፡፡ ወንበዴ ሰርቆ
ነው ያሰራቸው
አህዮቹ ለጌታ ውለታ ሰርተዋል፡፡ ጌታ ሲወለድ
አሙቀውታልና፡፡
ለጌታ ውለታ ልንመልስ ያልቻልነው እኛ ሰዎች ብቻ ነን፡፡
የታሰሩት እዲፈቱ የመረጠበት ሚስጥር፡-እኔ ከሃጥአታችሁ
ልፈታችሁ የመጣሁ ነኝ ሲል ነው፡፡
ወንበዴው አህዮቹን ሰርቆ በመንደር እንዳሰራቸው
ዲያብሎስም ለሰው ልጅ በሃጥአት ሰንሰለት ከሲኦል መንደር
አስራቸው
ነበርና፡፡
ሃዋርያቱ ሲልካቸው ምን ታደርጋላችሁ የሚላችሁ ሰው ቢኖር
ጌታቸው ይሻቸዋል በልዋቸው አላቸው፡፡ የፈጠራቸው እሱ
ነውና፡፡
ከአህያዋ ጀርባ ሃዋርያት ልብሳቸው አነጠፉለት ለምን?
ለምንስ ኮርቻ አላደረጉለትም? ለምንስ ልብሳቸው መረጡ?
ለስላሳ ህግ የሰራህልን አንተ አባት ነህ ሲሉ ነው፡፡ለስላሳ ህግ
የተባለው ወንጌል ነው
ወንጌል ፍቅር ናት የሚረግማችሁ መርቁ ትላለችና፡፡ ልብስ
የሰውነት ነውር ይሸፍናል፡፡ ነውረ ሃጥአታችን የምትሸፍንልን
አምላክ ነህ ሲሉ ነው፡፡ እሱ ልብሳችን ነውና፡፡ ነውራችን
የሚሸፍንልን እሱ ነውና፡፡ችግሩ ግን ነውረ ሃጥአታችን
የሚሸፍንልን ልብስ እርሱ መሆኑን አለማወቃችን ነው፡፡
አብሮን
እንዳለ አለማስተዋላችን ነው፡፡ስለዚ እንደ ሃዋርያት
ሃጥአታችንን አስቀድመህም የሸፈንክልን ዛሬም የምትሸፍንልን
ወደፊትም
የምትሸፍንልን አምላክ አንተ ነህ ልንለው ይገባል፡፡ጌታችን
በሁለቱ አህያዎች በጥበብ ተቀመጠ፡- በሰው የማይቻል
በእግዚአብሔር ዘንድ ግን የሚቻል መሆኑ ጥበበኛ አባት ሁሉን
የሚችል አባት መሆኑ የሚገልጽ ነው፡፡ አንድም ወንጌልን
ኦሪትና
ሃዲስን ሁለቱ አስታርቆ አስማምቶ አንዱን አንዱን እየመገበ
የሚሄድ መሆኑ የሚያመለክት ነው፡፡
ጌታ ለምን በፈረስ ላይ አልተቀመጠም?
ትንቢትና ምሳሌውን ለመፈጸም ነው፡፡ ት.ዘካ9፡9 ” አንቺ
የጽዮን ልጅ ሆይ፥ እጅግ ደስ ይበልሽ፤ አንቺ የኢየሩሳሌም ልጅ
ሆይ፥
እልል በዪ፤ እነሆ፥ ንጉሥሽ ጻድቅና አዳኝ ነው፤ ትሑትም ሆኖ
በአህያም፥ በአህያይቱ ግልገል በውርጫይቱ ላይ ተቀምጦ ወደ
አንቺ ይመጣል።”
በአህያ መቀመጡ
•ትህትናን ለማስተማር
•የሰላም ዘመን ነው ሲል
•ለፈለጉኝ ሁሉ የቅርብ አምላክ ነኝ ሲል በንጽህና በየዋህነት
ለሚኖሩ መእመናን አድሬባቸው እኖራለሁ ሲል፡፡
•አህያዎች ትሁታን ናቸው ረጋ ብለው ነው የሚሄዱት፤በቀላሉ
ትወጣበታለህ፤በቀላሉ ትይዘዋለህ፤እንደፈለክም ታዝዋለህ፤እኛ
በትእቢት ተይዘን ነው እንጂ በየዋህነት ብንመላለስ እሱ
ያድርብን ነበር፡፡ እኛ የእግዚአብሔር ማደርያ ነንና፡፡
ትልቅዋ አህያ የኦሪት ምሳሌ ነው
1.ትልቅዋ አህያ ሸክም የለመደች ናት ህገ ኦሪትም የተለመደች
ህግ ናትና፡፡
2.የእስራኤል ምሳሌ ነው፡-ትልቅዋ አህያ ሸክም እንደለመደች
ሁሉ እስራኤልም ህግ ለመፈጸም በህግ ለመራመድ የለመዱ
ናቸው፡፡
3.የአዳም ምሳሌ ነው፡- አዳም ሸክም የበዛበት ነበርና
ውርጭላዋ
1.በህገ ወንጌል ትመሰላለች፡-ምክንያቱም ወንጌል ኢየሱስ
ክርስቶስ የመሰረታት የሰራት አዲስዋ ህግ ናትና፡፡
2.በአህዛብ ትመሰላለች፡-ትንሽዋ አህያ ሸክም የለመደች
አይደለችም እንዲሁም አህዛብም ህግህን የመቀበል የለመደ
አይደሉም፡፡ ለህግህ አዲስ ናቸውና፡፡
3.የእመቤታችን ምሳሌ ናት፡- የዓለም ሸክም አቅልላለችና
በእመቤታችን ትመሰለላለች፡፡ እመቤታችን ድህነተ
ምክንያታችን ጌታን የተሸከመች ንጽህት እንከን የሌላት እናት
ናትና፡፡
ህዝቡም ልብሳቸው እያወለቁ በጎዳና አነጡፉለት ለምን?
እንኳን አንተ የተቀመጥክባት አህያም ክብር ይገባታል ብለው
ነው፡፡ እስራኤላውያን ጌታ የተቀመጠባት አህያ አከበሩ፡፡ ይህ
ትውልድ ግን ጌታ የተቀመጠባት እመቤታችን ማክበር
ተሳናቸው፡፡ ልብሳቸው ማንጠፋቸው፡- ለክብሩ መግለጫ ነው፡፡
ሌሎችም ቅጠል አነጠፉለት፡ ሰስት አይነት ቅጠል አነጠፉለት
ዘንባባ፤የቴመር ዛፍ፤የወይራ ዛፍ አነጠፉለት፡፡
ዘንባባ
1.ዘንባባ፡- ይስሃቅ በተወለደ ጊዜ ደስ ብሎት አብርሃምን
ዝንባባ ይዞ እግዚአብሔር አመስግነዋል፡፡
2.ዝንባባ ደርቆ እንደገና ሂወት ይዘራል፡- የደረቀ ሂወታችን
የምታለመልም አምላክ ነህ ሲሉ ነው፡፡
3.ዝንባባ የሰላም ምልክት ነው፡- የሰላም አምላክ ነህ ሲሉ
ነው
4.ዝንባባ የደስታ መግለጫ ነው፡- አንተ ደስ የምታሰኝ
ሃዘናችንም የምታርቅልን አምላክ ነህ ሲሉ ነው፡፡
5.ዝንባባ እሾሃማ ነው፡- አንተ ህያው አሸናፊ አምላክ ነህ ሲሉ
ነው፡፡
6.ዝንባባ እሳት አይበላውም ለብልቦ ይተወዋል እንጂ፡፡ ጌታም
አንተ ባህሪህን የማይመረመር ነው ሲሉ ነው፡፡
ሆሣዕና በእጃችን እደ ቀለበት ማሰራችን የምን ምሳሌ ነው?
1.ጌታ ለአዳም የሰጠው ቃል ኪዳን ለማስታወስ፡-ከልጅ ልጅህ
ተወልጄ አድነሃለሁ ያለውን የተስፋ ቃል ለማስታወስ፡፡
2.ጌታ ለእመቤታችን የገባላትን ቃል ኪዳን ተምሳሌት ነው
3.ጌታ ለእስራኤላውያን የሰጣቸው ቃል ኪዳን ተምሳሌት ነው
4.ጌታ ለአዳም ከሰይጣን ግዛት ነጻ እንዳወጣው ሁሉ እኛም
ከሰይጣን ግዛት ከመከራ ስጋ ከመከራ ነፍስ ከክፋት ከሃጥአት
አውጣን ማረን ለንስሃ ሞት አብቃን ከቤትህ አትለየን እንደ
ቸርነትህ ይቅር በላን ስንል ከጌታ ደግመን ላናጠፋ ቃል
የምንገባበት ነው፡፡
ስለዚ እንደ ታሰሩ አህዮች መፈታት አለብን፡፡ ሁላችን ታስረናልና
ቤተ ክርስትያን በመሄድ እንድንፈታ እናድርግ፡፡ የታሰሩት ሁሉ
በካህናት አባቶቻችን አማካኝነት እዲፈቱ ልናድርግ ይገባናል፡፡
ለምን ቢባል አምላካችን ይፈልገናል አባታችን አማላካችን
ንጉሳችን ኢየሱስ ክርስቶስ ይፈልገናል፡፡ ጌታ ጸጋውን አብዝቶ
ለዘላለሙ ከቤቱ አይለየን የነጻነት አባት ካለን ሱስና ልማድ ሁሉ
ነጻ አድርጎ ለሱ እንድንገዛ የእግዚአብሔር ቸርነት የድንግል
ማርያም አማላጅነት የቅዱሳን አበው ጥበቃ ይርዳን።

የዐቢይ ጾም 8ኛ ሳምንት ሆሣዕና

ሆሣዕና (የዐቢይ ጾም 8ኛ ሳምንት)
ሆሣዕና ከስምንቱ የዐቢይ ጾም እሑዶች አንዱና የመጨረሻው
ሳምንት ተብሎ የሚጠራው ከትንሣኤ ቀድሞ የሚገኝ
የሕማማት መገቢያ ዋዜማ ነው። ሆሣዕና አስቀድሞ ካለው
ረቡዕ ጀምሮ የሚታሰብ ታላቅ የቤተክርስቲያን የበዓል ቀን
እንደሆነ ይታወቃል። ይህን ስም በዚሁ ሰንበትና በዋዜማዎቹ
ዕለታት የሚዘመረው ጾመ ድጓ ‘ሆሣዕና በአርያም’’ ‘ሆሣዕና
ለወልደ ዳዊት’’ ‘ዕለተ ሆሣዕናሁ አርዓየ… ‘ ወዘተ. በማለት
ሆሣዕና የሚለውን ቃል ቅዱስ ያሬድና ሌሎችም አባቶች
በየቦታው እየጠቀሱና እየተዘመረለት በአህያ ውርንጭላ ላይ
ተቀምጦ ኢየሩሳሌም የገባበትን ሁኔታ እየተረከ ስለሚዘምር
ይህ ሰንበት በጌትነትና በክብር በውዳሴና ቅዳሴ ሆሣዕና
በአርአያም እየተባለ በሽማግሌዎችና በሕፃናት አንደበት
በድንጋዮችም ልሳን ሳይቀር እየተመሰገነ ወደ ቅድስት ሀገር
ኢየሩሳሌም በከብር ሲገባ ለሰጣቸው ለተቀደሰ ሰላሙና ፍቅሩ
መታሰቢያ ሆኖ የተሰጠ ነው።
አስቀድሞም በነቢየ እግዚአብሔር ዘካሪያስ እንደተነገረው
‘አንቺ የጽዮን ልጅ ሆይ እጅግ ደስ ይበለሽ ፣አንቺ የኢየሩሳሌም
ልጅ ሆይ እልል በይ እነሆ ንጉሥሽ ጻድቅና አዳኝ ነው ትሑትም
ሆኖ በአህያም በአህያያቱም ግልገል በውርንጫይቱ ላይ
ተቀምጦ ወደ አንቺ ይመጣል… ሰላምን ይናገራል’’ ዘካ.9፣9።
በማለት እንደሚመጣና የሠላምንም ብሥራት እንደሚያበሥር
ተናገሮ ነበር። ሲመጣም ‘ሁሉም ፈጥነው ልብሳቸውን ወሰዱ
በሰገነቱም መሰላል እርከን ላይ ከእግሩ በታች አነጠፉት።’’
በማለት ሊደረግለት የሚገባውን ገልጿል። 2ኛ ነገ. 9፣13 ።
የሆሣዕና በዓል በቤተክርስቲያን ጌታ ወደ ቤተመቅደስ ሲገባ
ሕዝቡ ፀበርት ወይም ዘንባባ በመያዝ ‘ቡርክ ዘይመጽእ በስመ
እግዚአብሔር - በእግዚአብሔር ስም የሚመጣ የተባረክ
ነው።’’ መዝ.117፣26 በማለት ስለተቀበሉት ይህን በማሰብና
በማድረግ ቤተክርስቲያናችን ዘንባባ ለሕዝበ ክርስቲያኑ
ይታደላል። በቤተክርስቲያን በአራቱም ማዕዘናት ይህን በዓል
የሚመለከቱ የቅዱስ ማቴዎስ (ማቴ. 21፣1-17)፤ የቅዱስ
ማርቆስ፣(ማር.11፣1-1 0)፤ የቅዱስ ሉቃስና
(ሉቃ.19፣29-38)፤ የቅዱስ ዮሐንስ (ዮሐ.12፣12-15)
ወንጌላት ይነበባሉ ። ታዲያ አኛ ይህን ዐቢይ በዓል
የምናከብረው እንዴት ነው? በነቢያቱ ከላይ እንደተገለጠው
በወንጌላቱም አንደተፈጸመው እርሱ ወደ እኛ የሚመጣበት ጊዜ
መቼ ነው? ሲመጣስ ምን እናድርግ? የእግዚአብሔርን
መምጫ ጊዜ ማሰብና መዘጋጀት ያለብን እንዴት ነው?
ምክንያቱም በዓሉ ከምንም በላይ የሚጠቅመን ለእኛ ነውና ።
ስለዚህ ይህን በዓል ስናከብር ሰላምንና ፍቅርን የእርሱን የክብር
አመጣጥ እያሰብን ልንተገብረው ይገባል።
ለጌታ የማያስፈልግ ፍጥረት የለም ይልቁንም የክብር ዘውድ
አድረጎ በመልኩ የፈጠረው ሰው ያስፈልገዋል።ያለ
እግዚአብሔር ፈቃድ የተፈጠረ ማንም የለም።እያንዳንዳችን
በእግዚአብሔር ዓላማና ዐቅድ የተፈጠርን እንደመሆናችን
መጠን እግዚአብሔር የሚከብርበትን ሥራ ልንሠራ
ይገባል።አህያ በሰው ሰውኛ ሲታይ የንቀትና የውርደት ሲመስል
ይችላል ።የአህያን ታሪክ በመጽሐፍ ቅዱስ ስንመለከት ግን
1. በለዓም በሥጋዊ ገንዘብ መንፈሳዊ ዓይኑ ታውሮ
እግዚአብሔር ያልረገማቸውን እስራኤላውያንን ሊራገም ሲሄድ
እስራኤላውያንን እንዳይራገም ለመንገር ከእግዚአብሔር ዘንድ
የተላከው መልአክ በሚሄድበት መንገድ ላይ ቆሞ ሳለ ከበለዓም
ይልቅ ያየችው የበለዓም አህያ ነበረች ። አህያይቱም መልአኩን
አክብራ መንገዱን እንደለቀቀችለት ቅዱስ መጽሐፍ
ይነግረናል። ዘኅ.22፣23።
2. በትንቢተ ኢሳያስ 1፣3 ‘ሰማይ ስሚ ምድርም አድምጪ በሬ
የገዢውን አህያም የጌታውን ጋጣ አወቀ እሥራኤል ግን
አላወቀም’’ እንደተባለው ጌታ በተወለደ ጊዜ ትንቢቱን
ምሳሌውን የሚያውቁ እሥራኤላውያን ባላወቁ ባለተቀበሉ
ሰዓት በዚያ በብርድ ወራት እናቱ የምታለብሰው ልብስ አጥታ
ቅጠል አልብሳው በነበረ ጊዜ ለጌታ ሙቀት የገበሩለት
እረኞቻቸውን ተከትለው የመጡ ከበቶች ላሞችና አህዮች
ናቸው። ‘ወአስተማወቅዎ አድግ ወላህም’’ እንዲል አባ
ሕርያቆስ በቅዳሴ ማርያም።።
3. በሆሣዕና ዕለት ከሌሎች እንስሳት ይለቅ ጌታን ለመሸከም
ለከብር የተሸከመችው አህያ ናት። ጌታን የተሸከመችው አህያ
ከዚያ በፊት ያላየችውና ያልተደረገላት ክብር ተደርጉላታል።
አህያ ከዚህ በፊት ለኛ እህል ተሸክማ ስትሄድ ሂጂ እያልን በዱላ
እንደበድባት ነበር፡ ነውም። ነገር ግን በሆሣዕና ዕለት እንኳን
በዱላ ልትደበደብ ቀርቶ ሰዎች በእርሷ ላይ ለተቀመጠው ጌታ
ሲሉ ልብሳቸውን ሁሉ እያነጠፉላት በንጣፍ ላይ ተራምዳለች ።
ስለዚህ ክርስቶስ በአህያይቱ ላይ እንዲቀመጥባት ልብስም አንደ
ተጎዘጎዘላት እኛም ጌታ በፀጋውና በረድኤቱ እንዲያድርብን
ልባችንን ከኃጢአትና ከተንኮል አንጽተን ፍቅርንና ትሕትና
ልንጎዘጎዝ ይገባል።ጌታ በኛ ላይ በፀጋው ሲያድር በእርሱና
በቅዱሳኑ ዘንድ ያለን ክብርና ፀጋ ታላቅ ነው። በነገር ሁሉ
መከናወን ይሆንልናል።ክርስቶስን በመሸከሟ የአህያይቱ ታሪክ
እንደተለወጠ ሁሉ በክርስቶስ ማደሪያነታችን ያለፈው መጥፎ
ታሪካችን ይለወጣል።እንግዲህ በእለተ ሆሣዕና ወደ
ኢየሩሳሌም ሲሄድ ሕዝቡ ሁሉ በደስታ በዝማሬ እንደ ንጉሰ
እንደተቀበሉት እኛም ሀሴትን አድርገን ‘ሆሣዕና እምርት እንተ
አቡነ ዳዊት…’’ በማለት እናመሰግናለን። ከበዓሉ ረድኤት
በረከት ያሳትፈን።አሜን።
የዕለተ ሰንበት መዝሙር (ከጾመ ድጓ)
ወእንዘ ሰሙን በዓለ ፋሲካ ቀርቡ አርዳኢሁ ለአምላከ ጽድቅ
ኀበ ደብረ ዘይት ሙራደ ዓቀብ ሀገረ እግዚአብሔር ወተቀበልዎ
ሕዝብ ብዙኃን አዕሩግ ወሕፃናት ነሢኦሙ አዕፁቀ በቀልት
እንዘ ይብሉ ሆሣዕና በአርያም ተፅዒኖ ዲበ ዕዋል ቦአ ሀገረ
ኢየሩሳሌም በትፍሥሕት ወበሐሴት ይሁቦሙ ኃይለ
ወሥልጣነ፡፡
ትርጉም: “በፋሲካ በዓል ሰሞን የእውነት አምላክ ደቀ
መዛሙርት ወደ ደብረ ዘይት ቀረቡ፤ በሀገረ እግዚአብሔር
(ኢየሩሳሌም) አቀበቱ ላይ ብዙ አረጋውያንና ሕፃናት የዘንባባ
ቅጠል ይዘው ሆሣዕና በአርያም እያሉ ተቀበሉት፣ በአህያ
ውርንጫ ላይ ተጭኖ በፍጹም ደስታ ወደ ኢየሩሳሌም ገባ።
ለእነዚህ ኃይልና ሥልጣንን ይሰጣቸዋል።

የዐቢይ ጾም 7ኛ ሳምንት ኒቆዲሞስ

ኒቆዲሞስ (የዐቢይ ጾም 7ኛ ሳምንት)
ዮሐ. 3÷1-11 ከፈሪሳውያንም ወገን የአይሁድ አለቃ የሆነ
ኒቆዲሞስ የሚባል አንድ ሰው ነበረ፤ እርሱም በሌሊት ወደ
ኢየሱስ መጥቶ። መምህር ሆይ፥ እግዚአብሔር ከእርሱ ጋር
ከሆነ በቀር አንተ የምታደርጋቸውን እነዚህን ምልክቶች
ሊያደርግ የሚችል የለምና መምህር ሆነህ ከእግዚአብሔር
ዘንድ እንደ መጣህ እናውቃለን አለው። ኢየሱስም መልሶ።
እውነት እውነት እልሃለሁ፥ ሰው ዳግመኛ ካልተወለደ በቀር
የእግዚአብሔርን መንግሥት ሊያይ አይችልም አለው።
ኒቆዲሞስም። ሰው ከሸመገለ በኋላ እንዴት ሊወለድ ይችላል?
ሁለተኛ ወደ እናቱ ማኅፀን ገብቶ ይወለድ ዘንድ ይችላልን?
አለው። ኢየሱስም መለሰ፥ እንዲህ ሲል። እውነት እውነት
እልሃለሁ፥ ሰው ከውኃና ከመንፈስ ካልተወለደ በቀር ወደ
እግዚአብሔር መንግሥት ሊገባ አይችልም። ከሥጋ የተወለደ
ሥጋ ነው፥ ከመንፈስም የተወለደ መንፈስ ነው። ዳግመኛ
ልትወለዱ ያስፈልጋችኋል ስላልሁህ አታድንቅ። ነፋስ
ወደሚወደው ይነፍሳል፥ ድምፁንም ትሰማለህ፥ ነገር ግን
ከወዴት እንደ መጣ ወዴትም እንዲሄድ አታውቅም፤ ከመንፈስ
የተወለደ ሁሉ እንዲሁ ነው። ኒቆዲሞስ መልሶ። ይህ እንዴት
ሊሆን ይችላል? አለው። ኢየሱስም መልሶ እንዲህ አለው።
አንተ የእስራኤል መምህር ስትሆን ይህን አታውቅምን?
እውነት እውነት እልሃለሁ፥ የምናውቀውን እንናገራለን
ያየነውንም እንመሰክራለን፥ ምስክራችንንም አትቀበሉትም።
ስለ ምድራዊ ነገር በነገርኋችሁ ጊዜ ካላመናችሁ፥ ስለ ሰማያዊ
ነገር ብነግራችሁ እንዴት ታምናላችሁ? ከሰማይም ከወረደ
በቀር ወደ ሰማይ የወጣ ማንም የለም፥ እርሱም በሰማይ
የሚኖረው የሰው ልጅ ነው።
የዕለተ ሰንበት መዝሙር (ከጾመ ድጓ)
ሖረ ኀቤሁ ዘስሙ ኒቆዲሞስ ወይቤሎ ለኢየሱስ ረቢ ሊቅ ንሕነ
ነአምን ብከ ከመ እምኀበ አብ መጻእከ ከመ ትኩን መምህረ፤
ዕጓለ አንበሳ ሰከብከ ወኖምከ አንሥአኒ በትንሣኤከ፡፡
ትርጉም: ስሙ ኒቆዲሞስ የተባለው ሰው ወደ ጌታችን ኢየሱስ
ሄደ፤ መምሕር ሆይ ልታስተምር ከእግዚአብሔር አብ ዘንድ
እንደመጣህ እናምንብሃለን አለው። የአንበሳ ደቦል ተኛህ፣
አንቀላፋህም፤ በትንሣኤህ አንሣኝ።
እውነት እውነት እልሃለሁ፡- ሰው ዳግመኛ ከውኃና ከመንፈስ
ካልተወለደ የእግዚአብሔርን መንግሥት አያይም፡፡ ጌታችንና
መድኀኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ይህንን የተናገረው ለኒቆዲሞስ
ነው፡፡
ኒቆዲሞስ የሃይማኖት ሊቅ ነው፡፡ ብዙ የተማረ ብዙ ያወቀ
ሰው ነው፡፡ ከዚህም የተነሣ ሊቅ - ምሁር - አለቃ ተብሎ
ተጠርቶአል፡፡ በጊዜው ከነበሩ ሰዎች ከፍ ያለና የላቀ ዕውቀት
የነበረው ሰው ነበር፡፡ በሌሊት ወደ ጌታ እየመጣ ይማር ነበር፡፡
የማታ ተማሪ ነበር፡፡ ቀን - ቀን የምኩራብ አስተማሪ ሆኖ ብዙ
ሰዎችን ያስተምር ስለ ነበረና እርሱ የሚያስተምራቸው አይሁድ
ጌታን ስላልተቀበሉ ቀን ለቀን መጥቶ የሚማርበት አመቺ ጊዜ
አልነበረውም፡፡
በአይሁድ ሕግ ጌታን የሚከተልና የሚቀበል ሰው ከምኲራብ
የሚባረር ስለሆነ እነርሱን ላላማስቀየም ማታ ነበር
የሚማረው፡፡ ኒቆዲሞስ ለጌታ ከሰው ችሎታ በላይ የሆኑ
ተአምራትን ስለምትሠራ እኛን ለማስተማርና ለመምከር
ከእግዚአብሔር ዘንድ ተልከህ የመጣህ ነህ ብሎ
መስክሮለታል፡፡ ጌታም ለእናንተ ተልኬ የመጣሁ ከሆነና
እናንተን ለማስተማር እንደ መጣሁ ከተረዳህ ሰው ዳግመኛ
ከውኃና ከመንፈስ ካልተወለደ ወደ እግዚአብሔር መንግሥት
አይገባም አለው፡፡
ኒቆዲሞስ ስላልገባው እኔ አርጅቼአለሁ፤ እንዴት ነው ወደ እናቴ
ማኅጸን ተመልሼ የምገባውና ዳግም የምወለደው? ብሎ
ኢየሱስ ክርስቶስን ጠየቀው፡፡ ጌታም፡- ሰው ከሰው ከተወለደ
ሥጋዊ ነው፤ የሰው ልጅ ነው፡፡ የእግዚአብሔር ልጅ ለመሆን
በመንፈስ መወለድ አለበት፡፡ ከእግዚአብሔር መወለድ ነፋስ
ከየት ተነሥቶ ወዴት እንደሚነፍስ እንደማይታወቅ ያለ ረቂቅ
ምሥጢር ነው አለው፡፡ አሁንም ያ ሊቅ፤ ያ አዋቂ አልገባኝም
አለ፡፡ ኢየሱስ ክርስቶስም፡- አንተ የእስራኤል ሊቅና አዋቂ
ሆነህ እንዴት ይህን አታውቅም አለው፡፡ ከሰማይ ከወረደው
በቀር ወደ ሰማይ የሚወጣ የለም፤ የምናውቀውንም
እንናገራለን ካለው በኋላ ጥያቄውን በዚህ ገታ፡፡
ኒቆዲሞስ ወደ ጌታችን ወደ ኢየሱስ ክርስቶስ መጥቶ መማሩ
የምያስመሰግነው ተግባር ነው፡፡ አይሁድ ወገኖቹ ጌታን
ሳይከተሉት እርሱ ጌታን መውደዱ የሚያስደንቅ ነው፡፡
ኒቆዲሞስ የሚያመሸው ከጌታ ጋር ነበር፡፡ ባለችው ትርፍ
ጊዜው ሁሉ ወደ ፈጣሪው ይሔድ ነበር፡፡ ይህ ታላቅ ዕድል
ነው፡፡ ቀን ሲያስተምርና ሲደክም ስለሚውል ማታ - ማታ
ማረፍ ይገባው ነበር፡፡ ኒቆዲሞስ ግን ቤቴ ገብቼ ልረፍ
አላለም፡፡ ባለ ሥልጣንና ባለጸጋ ስለ ነበር ደጅ የሚጠናው
ሕዝብና መሰል ባልንጀሮቹ ይፈልጉት ነበር፡፡ ይሁን እንጂ
ከእነርሱ ጋር አላመሸም፡፡
ከዚህ አባት ታላቅ ትምህርት ልንማር ያስፈልጋል፡፡ እኛ ዛሬ
የምናመሸው የት ነው? የምናመሸውስ ከማን ጋር ነው? ምን
ስናደርግ ነው የምናመሸው? ኒቆዲሞስ ቤቱ አልነበረም
የሚያመሸው፤ ከእውነተኛው መምህር ጋር እንጂ፡፡ ኒቆዲሞስ
ጽድቁንና በረከቱን እየያዘ ነበር ወደ ቤቱ ይገባ የነበረው፡፡ እኛ
ወደ ቤታችን የምንገባው እየከበርን ነው ወይ? ጸድቀን ነው
የምንገባው ወይስ ጎስቁለን?
የዛሬው ሰው እየሰከረ፣ እየጨፈረ፣ እየደማ፣ እየቆሰለ አብዶ
ነው የሚመለሰው፡፡ በቤት ያሉትም እንቅፋት ያገኘው ይሆን?
ይሞት ይሁን? እያሉ እየተሳቀቁ ነው የሚያመሹት፡፡
የሚሞትም አለ፡፡ ማምሸት እንደ ኒቆዲሞስ ከጌታ ጋር ነው
እንጂ! ኒቆዲሞስ ከጌታ ጋር በማምሸቱ ፈጣሪውን አወቀ፡፡
ጌታን ማወቅ ብቻ ደግሞ አይበቃም፡፡ ማወቅማ አጋንንትም
ያውቁታል፡፡ ከመንፈስ መወለድ መወለድ ያስፈልጋል፡፡
ሰው ዕፀ በለስን በበላ ጊዜ የእግዚአብሔር ልጅነቱን ተነጥቆ
ነበር፡፡ ጌታ መጥቶ ዳግም ሰው እስከሚያደርገን ድረስ
የሰይጣል ልጆች ሆነን ነበር፡፡ ከዚያም በአርባና በሰማኒያ ቀን
ከአብራከ መንፈስ ቅዱስና ከማኅፀነ ዮርዳኖስ ተወልደናል፡፡
አባታችን የምንለው ለዚህ ነው፡፡ ከእርሱ ከተወለድንና ልጅነትን
ካገኘን እንደገና ልጅነታችንን ካገኘን እንደገና ልጅነታችንን
እንዳናጣ አክብረን እንያዘው፡፡ መጀመሪያም አላወቅንበትም
ነበር፡፡ አዳም ከገነት የሚወጣ አልመሰለውም ነበር፡፡ ሰይጣን
አታሎታል፡፡ እኛም እንደገና እንዳንታለል ልጅነታችን
እንዳይሰረዝ እንጠንቀቅ፡፡
የብዙዎቻችን ልጅነት ዛሬ እየተወሰደ ነው፡፡ ልጅነታችንን
እያስነጠቅነው ነው፡፡ እነ ኤሳው እየነጠቁን ነው፡፡ ብዙዎች
እንደ ያዕቆብ ልጅነታችንን ሊወስዱብን አሰፍስፈዋል፡፡ ሰይጣን
እንደ አዳም ሊነጥቀን አሰፍስፏል፡፡ ዛሬ በጣም አርጅተናል፡፡
ኒቆዲሞስ አርጅቶ ነበር፡፡ በጥምቀትና በንስሓ ግን አዲስ
ሕይወት አግኝቶአል፤ ታድሷል፡፡ ያረጀው ሕይወቱ ለመለመ፡፡
ያረጀው ሰውነታችንን በሥጋውና በደሙ በንስሓ እናድሰው፡፡ ይህ
ከሆነ ነው የእግዚአብሔርን መንግሥት የምንወርሰው፡፡
ወስብሐት ለእግዚአብሔር