ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ነኝ

ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ነኝ
ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ነኝ

Friday, May 13, 2016

=>+*"ሥርዓተ ቤተክርስቲያን"*+

**ሥርዓተ ቤተክርስቲያን***=======Share
1. ጫማ አድርጐ ወደ ቤተመቅደስ መግባት ክልክል
ነው፡፡ ዘጸ 3፡5 የሐዋ 7፡39 2ኛ ዜና7፡14
2. ለሃጩን የማዝረክረክ ነውር /ልጋግ/ ያለበት ሰው
ቤተክርስቲያን አይገባም
3. በቤተክርስቲያን አጸድ ግብዣ ማድረግ አይገባም፡፡ ፍት.ነገ.
አንቀጽ 1 ክርስቶስ ሥጋና ደም
ከሚሰዋበት ምዕመናን ሥጋወደሙን ከሚቀበሉበት
ከቤተክርስቲያን ራቅ ብሎ በደጀ ሰላም አቅራቢያ
በቤተ ምርፋቅ ካልሆነ በቀር በቤተመቅደስ ውስጥና
በዓውደ ምሕረት ላይ ሥጋዊ መብል መጠጥ
ማቅረብ መብላት መጠጣት አይገባም፡፡ 4. የቤተክርስቲያን
መገልገያ ንዋያተ ቅዱሳትን ለግል
አገልግሎት ማዋል አይገባም፡፡ ዳን 5፡35-31 ፍት.
ነገ. አን.1 ረስጣ 28
5. በቅጽረ ቤተክርስቲያን ገበያ መገበያየት አይገባም
ዮሐ2፡14-17 ፍት.ነገ. አን. 1
6. በቤተመቅደስ በማኅበር ጸሎት ወቅት የግል ጸሎት
ማድረግ
ክልክል ነው፡፡
7. በቤተመቅደስ በቅዳሴ ሰዓት አቋርጦ መውጣት
ክልክል ነው፡፡ ማቴ 26፡26 ዕንባ2፡2ዐ
8. ሴት ልጅ በወር አበባ ወቅት ወደ ቤተመቅደስ
መግባት አይፈቀድላትም፡፡ ዘሌዋ 15፡18-30 ፍት.
ነገ. 14፡583 9. ወንድ ልጅ ሕልመ ሌሊት /ዝንየት/
ከመታው
በዕለቱ ወደ ቤተመቅደስ አይገባም፡፡ ዘሌዋ 15፡
2-18
10. የሌሊት ልብስ /የአረማውያን ልብስ/ ለብሶ ወደ
ቤተመቅደስ መግባት ክልክል ነው፡፡ 1ኛ ቆሮ 11፡
5-14 11. ባልና ሚስት ከተራክቦ በኋላ ዕለቱን ወደ
ቤተመቅደስ ለመግባት አይፈቀድላቸውም፡፡
«ጋብቻ ቅዱስ መኝታውም ንጹሕ ቢሆንም
በቤተክርስቲያን ሥርዓት መሠረት ከተራክብ በኋላ
ዕለቱኑ ወደ መቅደስ መግባት አይቻልም፡፡ ቅዱስ
ጳውሎስ «ለጸሎት በመፈቃቀድ ካልሆነ በስተቀር ባልና ሚስት
አይከላከሉ» እንዳለው ባልና ሚስት
ከተራክቦ የሚርቁት በበዓላት፣ በአጽዋማት፣
ለጸሎትና ለቅዳሴ በሚዘጋጁበት ዕለታት በሰንበት
ነው፡፡ ስለዚህ ጠዋት ለቅዳሴ በሚዘጋጁበት ጊዜ
ራሳቸውን ሊጠብቁ ይገባል፡፡ 1ኛ ቆሮ 7፡5 ኩፋሌ
34፡12 ዘጸ19፡15 12. በቤተ መቅደስ ውስጥ መሳቅ፣
መሳለቅ፣
ዋዛፈዛዛ
ነገር መነጋገር ክልክል ነው፡፡ ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ
«በምድራዊ ንጉሥ ፊት በቆምክ ጊዜ በምንም
ምክንያት ቢሆን ለመሳቅ አትደፋፈርም ታዲያ
በሰማያዊ ንጉሠ ነገሥት ፊት ትስቃለህን? ብሏል፡፡
ተግሣጽ ዘዮሐንስ አፈወርቅ አንቀጽ 6 «በቅዳሴ ሰዓት /ጊዜ/
የሚስቅ ዓለማዊ ቢሆን ወደ ውጭ
ያውጡት ከቅዱስ ምሥጢር /ከቁርባኑ/ አያቀብሉት
ተብሏል፡፡ ቀኖና ባስሌዎስ አንቀጽ 79
13. አብዝቶ ጠጥቶና ሰክሮ መግባት ክልክል ነው፡፡
«እንዳትሞቱ ወደ መገናኛው ድንኳን ስትገቡ አንተና
ልጆችህ የወይን ጠጅና የሚያሰክር ነገር ሁሉ አትጠጡ» ዘሌዋ
1ዐ፡8-10 ሉቃስ 21፡34 ምሳሌ
23፡29-35 ይሁንና ይህን ወይን አትጠጣ ቀምሰህ
ፈጣሪህን ለማመስገን ያህል ብቻ ይሁን እንጂ እንደ
ጢሞቴዎስ ብትታመም ከገድል ጽናት የተነሳ በድኑ
ደዌ ብትያዝ ግን ከወይን ጥቂት ጠጣ እርሱ ለሥጋ
ሕይወት ይሆንልሃልና፡፡ 1ኛ ጢሞ 5፡23 ሃይማኖተ አበው
ዘሠልስቱ ምዕት 21፡17-18
14. በቂም በቀል ሰውን አስቀይሞ የሰውን ገንዘብ
በማጭበርበር ወስዶ ወደ ቤተክርስቲያን መጥቶ
መጸለይ ክልክል ነው፡፡ ማቴ 5፡23-24 ማር 11፡25
ሉቃስ 18፡9-14
15. «ወደ እግዚአብሔር ቤት በገባህ ጊዜ እግርህን ጠብቅ . . .
» (ከተቀደሰ ስፍራ እንደቆምክ
አስተውል፡፡) መክ 5፡1 ወስብሐት ለእግዚአብሔር