ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ነኝ

ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ነኝ
ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ነኝ

Friday, June 3, 2016

=>+*"+<+>††† ግንቦት_27_መድኃኔዓለም †††<+>+"*+

አንድ አምላክ በሚሆን በአብ በወልድ በመንፈስ ቅዱስ ስም
አሜን
#ግንቦት_27_መድኃኔዓለም _ክርስቶስ_ለመባዓ
#ጽዮን_ያደረገለት_ተአምር _ይኽ_ነው፡- ‹‹ተክለማርያም
የተባለ መባዓ ጽዮን የመድኃኔዓለምን በዓል ከሌላ ጋር
አይጨምርም ነበር፡፡ ለመድኃኔዓለም መታሰቢያ የሚሆነውን
ሁሉ ለብቻው ያስቀምጠዋል፡፡ በረሃብ እስኪሞት ድረስ
ከመድኃኔዓለም መታሰቢያ እህል ምንም አይቀምስም፡፡
ያዘጋጀውንም ኅብስትና ጽዋ ለሕዝቡ ይሰጣቸዋል፡፡ የታመሙ
ሰዎችም ለመድኃኔዓለም መታሰቢያ ከተዘጋጀው በበሉ ጊዜ
ከሕመማቸው ሁሉ ይድናሉ፡፡ አባታችን የሚያዘጋጀውን
የመድኃኔዓለምን መታሰቢያ ይበሉ ዘንድ እየተጨናነቁ
ከቅርብም ከሩቅም ሰዎች በእምነት ይመጡ ነበር፡፡ በየወሩ
በዓሉም በቀረበ ጊዜ በጾምና በጸሎት ሰባት ቀን ይማለላል፡፡
ሆዱን ሳያጠግብ ራሱን ሳያስተኛ በፍጹም ልቅሶ መከራውን
ያስባል፡፡ ምድርን እስኪያርስ ድረስ ከዓይኖቹ ዕንባውን
ያፈሳል፡፡ ከልቅሶውም ብዛት የተነሣ እስኪጠፋ ድረስ ዓይኖቹ
ታመሙ፡፡ እመቤታችን ማርያምም ብርሌ የሚመስል ጽዋን
በእጇ ይዛ መጣች፡፡ ‹ወዳጄ ተክለማርያም ሆይ! ስለ ልጄ
ፍቅር ለታመሙ ዓይኖችህ መድኃኒትን እሰጥህ ዘንድ እነሆ
መጣሁ› አለችውና ጣቶቿን ከዚያ ጽዋ ነክራ ዓይኖቹን ቀባችው፤
ከሕመሙም ዳነ፡፡ ከዚያን ጊዜ ጀምሮ ሕመም አላገኘውም፡፡
በተቀደሰች በዓርባ ጾምም የመድኃኔዓለምን ግርፋት እያሰበ
ሰውነቱን በእጅጉ ገረፈ፡፡ ደሙ ከመሬት እስኪወርድ ድረስ
ልቡንም አጥቶ ከምድር ላይ ወደቀ፡፡ የመድኃኔዓለምን
መከራውን አስቦ እንደሞተም ሆነ፡፡ መድኃኔዓለምም ወደ
እርሱ መጣና ‹ተነሥ እኔ ቁስልህን እፈውስሃለሁ› ብሎ
የጀርባውን ቁስል ዳሰሰው፡፡ ምንም ሕማም እንዳላገኘውም
ሆነ፡፡ መድኃኔዓለምም አባታችንን ‹በአንተው እጅ ትገደልን?
እኔ እንኳ የተገደልኩት በአመፀኞች በአይሁድ እጅ ነው› አለው፡፡
በዚያችም ሰዓት ጌታ የመባዓ ጽዮንን ከንፈሮቹን ይዞ አፉን
ከፍቶ ሦስት ጊዜ እፍ አለበት፡፡ ‹የከበረ ትንፋሼም ከትንፋስህ
ጋራ ይጨመር፣ ሥጋህም ከነፍስህ ጋራ የከበረ ይሁን› አለው፡፡
‹አንተ በላዩ እፍ ያልህበትም የተቀደሰና የከበረ ይሁን› አለው፡፡
ብፁዕ ተክለማርያምንም አይቶ ለሰው ፈጽሞ የሚያስደንቅ
ነገርን ነገረው፡፡ ቅድስት ድንግል ማርያምም ስለ ልጇ ስለ
ፍቅሩ ገናንነትም ተደሰተች፡፡ መድኃኔዓለምም አባታችንን ‹ስለ
ሕማሜ ታመሃልና ስለ ክቡር ደሜም ደምህን አፍሰሃልና ስለ
ሞቴም ሞተሃልና እንደወደድኸኝ እኔም እወድሃለሁ፣
ሁልጊዜም ከአንተ አልለይም፡፡ አንተን የወደደ እኔን ወደደ፣
አንተንም የጠላ እኔን ጠላ፣ የላከኝንም ጠላ፣ እኔን እንደጠሉኝ
እንደ አይሁድ ይሁን፡፡ ነፍስህ ከሥጋህ ተለይታ በምትወጣበት
ቀንም ለሌላ አልሰጣትም እኔ እቀበላታለሁ እንጂ› አለው፡፡
‹ወደ አንተ የደረሰ ሁሉ ወደ ቤተክርስቲያንህም የመጣ፣
በአንተም የተማፀነ፣ በእጅህም የተባረከውን ሁሉ
እምርልሃለሁ፡፡ በእኔና በእናቴ ማርያም ስም በማይታበል ቃሌ
ቃልኪዳን ሰጠሁህ፣ መሐላዬንም አላጎድልብህም› አለው፡፡
አባታችንም ይህን ሰምቶ ፈጽሞ ተደሰተ፡፡
‹‹በሌላም ጊዜ ዳግመኛ ጌታችን ደም ግባቱ ያማረ፣ ልብሱም
የመስቀል ምልክት የሆነ ንጹሕ አክሊል በራሱ የተቀዳጀ
ጎልማሳ ሆኖ በፊቱ ቆመ፡፡ ‹ልመናህን እፈጽምልህ ዘንድ እነሆ
ወደ አንተ መጣሁ› አለው፡፡ ‹…እንደ አንተ በዓሌን ያደረገውን
እምረዋለሁ፣ የብርሃን ልብስንም አለብሰዋለሁ…› ብሎ
ቃልኪዳን ከሰጠው በኋላ ሁለመናው በመለኮት ጨውነት
ይጣፍጥ ዘንድ አውራ ጣቱን አጠባው፡፡ ከዚህም በኋላ ከእርሱ
ተሰወረ፡፡ እንዲሁም በሌላ ጊዜ እንዲህ እያለ መለነ፡- ‹ጌታዬ
ፈጣሪዬ ሆይ! በዓልህን አድርግ አንድ አንተ የምትወደውን
ግለጥልኝ› አለ፡፡ ጌታም ‹የሞቴን መታሰቢያ ያደረገ እንደ እኔ
ነፍሳትን ከደይን ያወጣል፣ ‹በእኔ የሚያምን እኔ የምሠራውን
ይሠራል፣ ከዚያም የበለጠ ይሠራል› ብዬ በወንጌሌ
እንደተናገርሁ› አለው፡፡›› ‹‹ክርስቲያኖች ሁሉ የፈጣሪያችንን
የመድኃኔዓለም ክርስቶስን የመታሰቢያ በዓሉን እናድርግ፡፡
የአባቶቻችን የሐዋርያት፣ የጻድቃን፣ የሰማዕታት፣ የመላእክት
መታሰቢያቸው ባረፉበት በተሾሙበት ቀን ይከበራል፡፡ እነርሱን
የፈጠራቸው እርሱ መድኃኔዓለም ነው፣ ያከበራቸው፣ ከፍ ከፍ
ያደረጋቸው፣ ስማቸውን ለጠራ መታሰቢያቸውን ያደረገ
እንደሚድን ቃልኪዳን የሰጣቸው እርሱ ነው፡፡ የመድኃኔዓለምን
የሞቱን መታሰቢያ ያደረገ ግን የተኮነኑ ነፍሳትን ከደይን
ያወጣል፣ በሞቱም ጊዜ ሥቃይን አያያትመ፡፡›› ‹‹ጌታችንም
ለመባዓ ጽዮን እንዲህ አለው፡- ‹መታሰቢያዬንም እንደ አንተ
በየወሩ የሚያደርግ ሁሉ በዓርብ ቀን ብዙ ነፍሳትን ከሲኦል
አወጣለታለሁ፡፡ አንተ ከምታደርገው ከሞቴ መታሰቢያም
ቁራሽ የበላውን፣ ከሩቅም ወሬህን ሰምቶ በልቡ ደስ ያለውና
የወደደውን ከሞቴ መታሰቢያ መድረስ ባይቻለውም እንኳ
እምረዋለሁ፡፡› መባዓ ጽዮንም ስለተሰጠው የምሕረት
ቃልኪዳን እጅግ ደስ ብሎት እንዲህ አለ፡- ‹ያለቸርነቱ በቀር በጎ
ሥራ ለሌለኝ ለእኔ ለኃጢአተኛው ይኽን ሁሉ ስላደረገልኝ
ለእግዚአብሔር ምን እከፍለዋለሁ?› አለ፡፡ ነገር ግን ስሙ
ለዘለዓለም የተባረከ ይሁን አሜን፡፡››
+ + + + + + + + + + + + + + +
ዳግመኛም በዚኽች ዕለት ከሞተ ከ4 ቀን በኋላ ጌታችን
ያስነሣው ቅዱስ አልዓዛር ዓመታዊ መታሰቢያ በዓሉ ነው፡፡
ይኸውም ቅዱስ አልዓዛር የባለ ሽቱዋ የማርያም እንተ
ዕፍረትና የማርታ ወንድም ሲሆን ጌታችን በጣም ይወደው
ስለነበር አልዓዛር መሞቱን ሲሰማ ከእኅቶቹ ጋር
አልቅሶለታል፡፡ ከሞተም ከ4 ቀን በኋላ ከመቃብር
አስተሥቶታል፡፡ ከጌታችን ዕርገት በኋላም አልዓዛርና እኅቶቹ
ቤታቸውን የወንጌል መማርያና የእንግዶች መቀበያ
አድርገውታል፡፡ እርሱ ከሞት በተነሣ በሳምንቱ ጌታችን
ተሰቅሎ በሥጋ ሞተ፡፡ ከትንሣኤውም በኋላ አልዓዛር
ከሐዋርያት ጋር ሆነ፡፡ በ50ኛውም ቀን ከሐዋርያት ጋር
መንፈስ ቅዱስን ተቀብሏል፡፡
አይሁድም ክርስቶስን ያመኑ ክርስቲያኖችን ሲያሳድዱ
አልዓዛርንና እኅቶቹን በቀዳዳ መርከብ ጭነው ወደ ባሕር
ጥለዋቸዋል፡፡ በተአምራት ከሞት ድነው የፈረንሳይ ግዛት
ወደሆነች አንዲት ከተማ ተሰደው በዚያ እየኖሩ የክርስቶስ
ምስክር ሆነዋል፡፡ ሐዋርያት በቆጵሮስ አገር ላይ በአንብሮተ
እጅ ኤጲስ ቆጶስነት ሾሙት፡፡ መንጋውንም በመልካም
አጠባበቅ እየጠበቀ በሹመቱ 40 ዓመት አገልግሏል፡፡
በከተማዋም የመጀመሪያው ጳጳስ በመሆን ወንጌልን እየሰበከ
ሲያገለግል ኖሮ መጋቢት 17 ቀን በሰማዕትነት ዐርፏል፡፡
ቅዱስ አልዓዛር በሰማዕትነት ካረፈ ከብዙ ዘመን በኋላ
ከክርስቲያን ነገሥታት መካከል አንዱ የቅዱስ አልዓዛር ሥጋው
በቆጵሮስ እንዳለ በሰማ ጊዜ ከቆጵሮስ ደሴት ወደ
ቁስጥንጥንያ አፈለሰው፡፡ ሊያፈልሱትም በወደዱ ጊዜ በከበረ
የድንጋይ ሣጥን ውስጥ ሆኖ በምድር ውስጥ ተቀብሮ አገኙት፡፡
በላዩም እንዲህ የሚል ጽሑፍ ነበረ፡- ‹‹ይህ በመቃብር ውስጥ
አራት ቀን ከኖረ በኋላ ከሙታን ለይቶ ላስነሣው ክብር
ይግባውና የጌታችን የኢየሱስ ክርስቶስ ወዳጁ የሆነ የቅዱስ
አልዓዛር ሥጋ ነው፡፡›› ይህንንም ጽሑፍ ባነበቡ ጊዜ ደስ
ተሰኝተው ተሸክመው ወደ ቁስጥንጥንያ አገር ወሰዱት፡፡
ካህናቱም ሁሉ በዝማሬ በክብር ተቀበሉት፡፡ ባማረ ቦታ
አስቀምጠውት ጥቅምት 21 ቀን የፍልሰቱን በዓል
አደረጉለት፡፡ ረድኤት በረከቱ ይደርብን፣ በጸሎቱ ይማረን፡፡
የመድኃኔዓለም ቸርነቱ የመባዓ ጽዮን አማላጅነቱ አይለየን!

=>+*"+<+>††† ግንቦት 26 †††<+>+"*+

<<< በስመ አብ : ወወልድ : ወመንፈስ ቅዱስ : አሐዱ አምላክ . . . አሜን :: >>>
<+> ግንቦት 26 <+>
+*" አቡነ ሃብተ ማርያም ጻድቅ "*+
=>እኒህ ጻድቅ የሃገራችን ኮከበ ገዳም ናቸው:: "ጽድቅና
ትሩፋት እንደ ሃብተ ማርያም" እንዲሉ አበው:: ባሕር ከሆነ
ጣዕመ ሕይወታቸው ጥቂቱን ለበረከት እንካፈል::
+ጻድቁ መካነ ሙላዳቸው ሽዋ (የራውዕይ) ውስጥ ሲሆን
አባታቸው ፍሬ ቡሩክ : እናታቸው ደግሞ ቅድስት ዮስቴና
ትባላለች:: በተለይ ቅድስት ዮስቴና እጅግ ደመ ግቡ : ምጽዋትን
ወዳጅ : ቡርክት ሴት ነበረች:: እንዲያውም ከጻድቁ መወለድ
በፊት መንና ጭው ካለ በርሃ ገብታ ነበር::
+ግን የበቃ ግኁስ አግኝቷት "ከማሕጸንሽ ደግ የሥላሴ ባርያ
አለና ተመለሽ" ብሏት እንደ ገና ተመልሳለች:: ጻድቁን ወልዳ
አሳድጋም እንደ ገና መንና በተጋድሎ ኑራ 7 አክሊላትን ተቀብላ
ዐርፋለች::
+ወደ ጻድቁ ዜና ሕይወት ስንመለስ አቡነ ሃብተ ማርያም ገና
ሕጻን እያሉ ከእናታቸው ጋር ቆመው ሲያስቀድሱ "እግዚኦ
መሐረነ ክርስቶስ" ሲባል ይሰማሉ:: ይሕችን ጸሎት በሕጻን
አንደበታቸው ይዘው ሌሊት ሌሊት እየተነሱ "ማረን እባክህን?"
እያሉ ይሰግዱ ነበር::
+የ5 ዓመት ሕጻን እንዲህ ሲያደርግ ማየቱ በእውነት
ይደንቃል:: ትንሽ ከፍ ብለው በእረኝነት ሳሉም ፍጹም
ተሐራሚና ጸዋሚ ነበሩ:: ጸጋው ስለ በዛላቸውም ልጅ ሆነው
ብዙ ተአምራትን ሰርተዋል:: የፈጣሪውን ስም ያቃለውን አንድ
እረኛም በዓየር ላይ ሰቅለው አውለውታል::
+ከዚያ ግን ለአካለ መጠን ሲደርሱ ወደ ት/ቤት ገብተው :
መጻሕፍትንም አጥንተው መንነዋል:: በአባ መልከ ጼዴቅ እጅ
ከመነኮሱ በሁዋላ የሠሩትን ትሩፋትና የነበራቸውን ተጋድሎ ግን
የኔ ብጤ ደካማ ሰው ሊዘረዝረው አይችልም::
*ባሕር ውስጥ ሰጥመው 500 ጊዜ ይሰግዳሉ::
*በየቀኑ 4ቱን ወንጌልና 150 መዝሙረ ዳዊትን ይጸልያሉ::
(መጽሐፍ ቅዱስን ማንበብ ታላቅ ጸሎት ነው)
*በ40 ቀናት : ቀጥሎም በ80 ቀን አንዴ ብቻ ይመገባሉ::
*ምግባቸው ደግሞ ሣርና ቅጠል ብቻ ነው::
*በየዕለቱ ያለ ማስታጐል ማዕጠንት ያሳርጋሉ:: (ካህን ናቸውና)
*ዘወትር በንጽሕና ቅዱስ ሥጋውን ይበላሉ : ክቡር ደሙን
ይጠጣሉ::
*በፍጹም በልባቸው ውስጥ ቂምን : መከፋትን አላሳደሩም::
+በእነዚህና በሌሎች ትሩፋቶቻቸው ደስ የተሰኘ ጌታም ለጻድቁ
የእሳትና የብርሃን ሠረገላን ሰጥቷቸው በዚያ እየበረሩ
ኢየሩሳሌም ይሔዱ ነበር:: ከብዙ የተጋድሎ ዘመናት በሁዋላም
የክብር ባለቤት መድኃኒታችን ክርስቶስ አዕላፍ መላእክትን
አስከተትሎ መጥቶ አላቸው::
"1.ስለ እኔ ረሃብና ጥምን ስለ ታገስክ:
2.ስለ ምናኔሕ:
3.ስለ ተባረከ ምንኩስናህ:
4.ስለ ንጹሕ ድንግልናህ:
5.ቂምና በቀልን ስላለመያዝህ:
6.ስለ ንጹሕ ክህነትህና ማዕጠንትህ:
7.ቅዱስ ወንጌልን በፍቅር ስለ ማንበብህ 7 አክሊላትን
እሰጥሃለሁ::"
+"በሰማይም ከመጥምቁ ዮሐንስ ጐን : 500 የእንቁ
ምሰሶዎች ያሉበትን አዳራሽ ሰጥቼሃለሁ:: በስምህ የሚለምኑ :
በቃል ኪዳንህ የሚማጸኑትንም ሁሉ እንድምርልህ 'አማንየ!
በርእስየ!' ብዬሃለሁ" አላቸው::
+ቅዱሳን መላእክትም "ሃብተ ማርያም ወንድማችን" ሲሉ
አቀፏቸው:: ጌታ ግን በዚያች ሰዓት አንድም ሦስትም ሆኖ
ታያቸውና አቅፎ 3 ጊዜ ሳማቸው:: ከፍቅሩ ጽናትም የተነሳ
ነፍሳቸው ከሥጋቸው ተለየች:: በዝማሬም ወሰዷት:: {ይህች ቀን
(ግንቦት 26) ለጻድቁ ዕለተ ልደታቸው ናት::}
=>አምላከ አበው ወሰማዕት ጣዕመ ፍቅራቸውን:
ክብራቸውን: ጸጋ በረከታቸውንም ይክፈለን::
=>+"+ እግዚአብሔር ፍርድን ይወድዳልና::
ቅዱሳኑንም አይጥላቸውምና::
ለዘለዓለምም ይጠብቃቸዋል . . .
ጻድቃን ምድርን ይወርሳሉ::
በእርስዋም ለዘላለም ይኖራሉ::
የጻድቅ አፍ ጥበብን ያስተምራል::
አንደበቱም ፍርድን ይናገራል::
የአምላኩ ሕግ በልቡ ውስጥ ነው::
በእርምጃውም አይሰናከልም:: +"+ (መዝ. 36:28-31)
<ወስብሐት ለእግዚአብሔር>

=>+*"+<+>††† ሎሚ 26 ግንቦት እዩ †††<+>+"*+

በሰምኣብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ ኣሃዱ ኣምላክ ኣሜን።
††† ሎሚ 26 ግንቦት እዩ †††
††† #ዓመታዊ_በዓለ_ዕረፍት_ሓ ዋርያ_ቅዱስ #ቶማስ †††
ቶማስ ማለት ጸሓይ ማለት እዩ።ቀዳማይ ስሙ ደዲሞስ እዩ
(ማቴ 10፡30፣ ዮሓ 20፡24 ፣ግብ ሓዋ 1፡13)። ጎይታ ክብ
ምውታት ተፈሊዩ ምስ ተንሰአ ኣብ መበል ሻሙናይ መዓልቱ
ሰንበት መዓልቲ ጎድኒ ጎይታ ዳህሲሱ መለኮት ምስ ኣቃጸሎ
"ጎይታይን ኣምላኸይን "ኢሉ ትንሳኤኡ ኣመነ። ዕርገት ናይ
ኣዴና ቅድስት ድንግል ማርያም ዝርኣየ ድማ ሓዋሪያ ቶማስ
እዩ።ሃገረ ስብከቱ ሕንድኬ (ህንዲ) እዩ። ንሱ ብ 30 ቅርሺ
ተሸይጡ ምስ ናይቲ ሃገር ሃብታም ክልኩዮስ የገልግል ነበረ።
እቲ ሃብታም ካኣ "እንታይ ክትሰርሕ ትክእል ፧"ኢሊ ሓተቶ።
ሓዋሪያ ቶማስ ድማ "ህንጻ ምስራሕ ሓወልቲ ምቅራጽ
ይክእል"በሎ። በዚ ተሰማሚዖም ብዙሕ ገንዘብን ወርቕን
ሃቦ።ኣህዛብ ምኩሓት ስለ ዝኾኑ ካኣ "ጥበብ ዘለዎ ሰብ ረኺበ
"ክብል ናብ ንጉስ ከደ። ቶማስ ድማ ነቲ ገንዘብ ወርቅን
ንድካታትን ነደያትን ሂቡ፣ምሂሩ ኣእመኖም ፣ሰበይቲ ልኩዮስ
፣ምስ ደቃን ኣገልገልታን ኣሚና ተጠምቀት።ልኩዮስ ካብ
መገሽኡ ምስ ተመልሰ "ዝሃነጽካዮ ህንጻ፣ዝቀረጽካዮ ሓወልቲ
ዳኣ ኣበይ ኣሎ፧ ኢሉ ሓተቶ። ሓዋርያ ቶማስ ድማ
"ብገንዘብካን ወርቅካን ዘስራሕካዮም ህንጻታት እዚኦም
እዮም " ኢሉ ነቶም ዝኣመኑ ህዝቢ ኣርኣዮ።ልኪዮስ ድማ
"ተጻዊትለይ "ብምባል ኢዱን እግሩን ኣሲሩ ቆርቦቱ ተቀሊጡ
ክሳዕ ዝግፈፍ ገረፎ።ሑጻ ኣሰኪሙ ውን ካብ ቦታ ናብ ቦታ ኮለል
ከም ዝብል ገበሮ። ሰበይቱ ኣርሰንዋ ነዚ ርእያ ሰንቢዳ ወደቀት
ብኡ ብኡ ድማ ሞተት ። ልክዮስ ካኣ "ሰበይተት ዝሞተት
ብሰንክኽኻ እዩ፣ ስለዚ እንተድኣ ኣሕዊኻያ ኣነ ውን ብኣምላኽካ
ክኣምን እየ በሎ።ጎይታ ንቑስሊ ሓዋርያ ቶማስ ከም ማይ
ኣዝሓሎ። ቅዱስ ቶማስ ካኣ በቲ ዝተገፈ ቆርበቱ ነታ ዝሞተት
ሰበይቲ ተንከያ እሞ ንሳ ካኣ ተንሰአት። ሽዑ ልኪዮስ ብጎይታ
ኣሚኑ ተጠመቐ። ብድሕርዚ ንቆርበቱ ተሰኪሙ ካብ ቦታ ናብ
ቦታ እንዳ ተዘዋውወረ ሕሙማት ፈወሰ፣ሙዉታት
ኣተንስአ፣ንኣህዛብ ኣእሚኑ ከም ዝጥመቑ ገበረ።ሓደ ግዜ
ቀንጣፍያ ትብሃል ዓዲ ምስ በጽሐ ሓደ ሰብኣይ ሸውዓተ ደቁ
ተቀቲሎም ሓዚኑ ረኾቦ እሞ ብቆርበቱ ነቶም ደቂ እቲ ሰብኣይ
ተንኪፉ ኣተስኦም። ኣብ ኢናስም ዝተባህለ ዓዲ ውን ትምህርቱ
ሰሚዖም ተኣምሩ ርእዮም ካብ ንጉስ ክሳብ ገባር ኣሚኖም
ተጠመቁ።ዘራጊ ከሎ ጽሩይ ማይ ዘይስተ ግን ካህናተ ጥዖት
ህዝቢ ብጎይታ እናኣመነ ኽገድፎም ስለ ዝጀመረ ጥቅሞም ስለ
ዝጎደሎም ምስ ንጉስን መኻንንትን ኣባኣስዎ እሞ በዚ ዕለት
ብሰይፈ ሰማዕትነት ተቀበለ ግዚኡ ብ 72 ዓ/ም እዩ።
በረከቱ ጸሎቱ ናይ ሓዋርያ ቅዱስ ቶማስ ምስ ኩሉና ህዝበ
ክርስቲያን ይኩን ።
ኣሜን ኣሜን ኣሜን
ስብሓት ለእግዝኣብሄር
ወለወላዲቱ ድንግል
ወለመስቀሉ ክቡር ይኩን!!!
ኣማኑኤል-ኣርኣያ
ምንጪ ምጽሓፍ መዝገበ ታሪኽ