ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ነኝ

ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ነኝ
ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ነኝ

Monday, April 25, 2016

የየዕለታቱ ሰሙነ ሕማማት

፨፨፨ "የየዕለታቱ ሰሙነ ሕማማት"፨፨፨
፨፨፨ ሰኞ:-ጌታችን ከቢታኒያ ሲወጣ ተራበ፤ ቅጠል ያለባትን
በለስ ከሩቅ አይቶ
በለሲቱን ቀረባት፤ ነገረ ግን ከቅጠል በቀር ምንም
አልተገኘባትም፡፡ ከአሁን
ጀምሮ ማንም ከአንች ፍሬን አይብላ ብሎ እረገማት በለስ
የተባሉአ እስራኤላዊ
ናቸው፡፡ ጌታም በዕለተ ሠኞ ሁለት ነገሮችን አድረጓል ፩
ማቴ.21÷18 ቅጠል
ብቻ የተገኘባትን ዕፀበለስ እረግሟል፡፡" ፪…
ሉቃ.19÷45-46" ወደ ቤተ
መቅደስ ገብቶ የሚሸጡትን የሚለውጡትን "ቤቴ የፀሎት ቤት
ናት እንጅ
የነጋደዎች ዋሻ አይደለችም" ብሎ ያንን ነጋደወቹ የያዙትን
በሙሉ
እየገለባበጠ ቤተ መቅደሱን የፀሎት ቤት አድረጓል፡፡ # ፨፨፨
ማክሰኞ:-
ሻጮቹንና ለዋጮቹን ከቤተ መቅደስ ባወጣ ጊዜ ይሔንን
በማን ኃይል
እንዳደረገው፡ የአይሁድ መምህራን ጠይቀዉት ነበር።
ማቴ.21፥13
ስለመሆኑም የጥያቄ ቀን ይባላል፡፡
፨፨፨ ረቡዕ:-ምክረ አይሁድ ይባላል። ምክንያቱም የአይሁድ
ሊቃነ ካህናት እና
ጸሐፍት ፈርሳዊያን ጌታን እንዴት መያዝ እንዳለባቸው ምክር
ያጠናቀቁበት ቀን
ነው፡፡
፨፨፨ ሐሙስ:-በቤተ ክርስቲያን የተለያዩ ስያሜዎች ያላቸው
በርካታ፡
ድርጊቶች የተፈፀመበት ነው፡፡
ፀሎት ሐሙስ ይባላል፡፡ ጌታ ኢየሱስ አይሁድ መጥተው
እስኪይዙት ድረስ
ሲፀልይ ያደረበት ነውና ፀሎት ሐሙስ ተባለ። ሕጽበት ሐሙስ
ይባላል፡፡
ጌታችን በዚህ ዕለት የደቀ መዛሙርቱን እግር ጎንተስ ብሎ
በታላቅ ትኅትና
አጥቧልና፤ የሐዲስ ኪዳን ሐሙስ ይባላል። ምክንያቱም የኦሪት
መስዋዕት
የሆነውን የእንሥሣት ደም ማብቃቃቱን ገልጦ ለድህነተ አለም
ራሱን የተወደደ
መስዋዕት አድረጎ ያቀረበበት ዕለት በመሆኑ፡ የነፃነት ሐሙስ:-
ምክንያቱም
ለሀጢአትና ለዳቢሎስ ባሪያ መህን ማብቃቱንና የሰው ልጅ
ያጣውን፡ ክብር
መልሶ ማግኘቱ የተረጋገጠበት ቀን ስለሆነ ነው፡፡
፨፨፨ ዓርብ:-ጌታችን ከጲላጦስ አደባባይ እስከ ሊጦስጥራ
የተንገላታበት፣
ለአዳምና ለልጆቹ፡ በመልዕልተ መስቀል ለሞት፡ እራሱን
አሳልፎ የሰጠበት ቀን
ነው፡፡
፨፨፨ ቅዳሜ:-በዚች ዕለት የጌታችን መከራ በማሰብ በፆም
ታስባ ስለምትውል
ቅዳም ስዑር ወይም የተሻረችው ቅዳሜ ትባላለች፡፡ ካህናቱም
ለምዕመናን
ልምላሜ ቄጤማን የሚያድሉበት ዕለት ስለሆነ ለምለም
ቅዳሜም ትባላለች፡፡
እንደዚሁም ልዑል እግዚአብሔርም በዚህ ቀን ፳፪ቱን ስነ
ፍጥረታት ፈጥሮ
ከሰራው ያረፈበት ዕለት ናት። መልካም የዖም ሳምብት፥
የስግደትና የእግዚኦታ
ሳምንት ይሁንልን አሜን ይቆየን።
እንዲሁ እንዳለን በሠላም በጤና ጠብቆ ለብረሃነ ትንሳኤው
በሠላም በፍቅር
ያድረሰን፡፡ አሜን።፨፨፨፨