ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ነኝ

ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ነኝ
ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ነኝ

Friday, March 17, 2017

ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ነኝ: =>+*"+<+>††መጋቢት ፯ (7)††

ስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ ፡፡
አሜን ፡፡ ✞✞✞
❖መጋቢት ፯ (7) ቀን የሚከበሩ ዓመታዊ የቅዱሳን በዓላት
✞ ሰማዕትነት በቅዱስ ቴዎዶጦስ ሕይወት ✞
+*" ቅዱስ ቴዎዶጦስ "*+
=>በ3ኛው መቶ ክ/ዘመን ነው:: ጊዜው ለክርስቲያኖች
ሁሉ ፍጹም የመከራ ከመሆኑ የተነሳ "ዘመነ-ሰማዕታት"
ሲባል በወቅቱ ከ47 ሚሊዎን በላይ ክርስቲያኖች
ተጨፍጭፈዋል::
+የዘመኑ ክርስቲያኖች ለመሞት የሚያደርጉትን
እሽቅድምድም እያዩ አሕዛብ "ወፈፌዎች" እያሉ
ይጠሯቸው ነበር:: (ዓለም እንዲህ ናትና!) እብዶቹ
ጤነኞችን "እብድ" ማለታቸውኮ ዛሬም አለ::
(ለነገሩ "ግደልና ጽደቅ" ከሚል መመሪያ በላይ ጤና
ማጣት አይኖርም)
=>ታዲያ በወቅቱ አንድ #ቴዎዶጦስ የሚሉት ወጣት
በምድረ ግብጽ ይኖር ነበር:: ወጣቱ እጅግ ብርቱ
ክርስቲያን ነበርና እንደ ዘመኑ ልማድ ተከሦ በነፍሰ
ገዳዮች ፊት ቀረ:: ክሱ አንድ ብቻ ነው:: "ክርስቶስን
አምልከሃል" የሚል::
+ከሥጋ ሞት ለማምለጥ ደግሞ መንገዱ ያው አንድ ብቻ
ነው:: ፈጣሪውን ክርስቶስን ክዶ ለአሕዛብ አማልክት
(አጋንንት) መገዛት:: #ቅዱስ_ቴዎዶጦስ በገዳዮቹ ፊት
ቆሞ ተናገረ:-
" #እኔ_ክርስቲያን_ክርስቶሳ ዊ_የክርስቶስ_ነኝ:: ምንም
ብታደርጉኝ ከክርስቶስ ፍቅር ልትለዩኝ አትችሉም"(ሮሜ.
8:35) አላቸው::
+እነሱ ግን ነገሩ እውነት አልመሰላቸውምና ሊያሰቃዩት
ጀመሩ::
*ገረፉት
*አቃጠሉት
*ደበደቡት
*ሌላም ሌላም ማሰቃያዎችን በእርሱ ላይ ተጠቀሙ::
የሚገርመው ግን እሱ ሁሉን ሲታገሥ ገዳዮቹ ግን
ደከሙ::
+በመጨረሻም ወደ ገዢው ዘንድ አቅርበው "ብዙ
አሰቃይተነዋል:: ግን ሊሳካልን አልቻለም" በሚል ሰይፍ
(ሞት) ተፈረደበት:: በአደባባይ ሊሰይፉት ሲወስዱት ግን
ትንሽ አዘኑለት መሰል ጨርቅ አምጥተው "ፊትህን ሸፍን"
አሉት:: (ያኔ ትንሽም ቢሆን ሰብአዊነት ሳይኖር አይቀርም)
+ቅዱስ ቴዎዶጦስ ግን ገዳዮቹን በመገረም
እየተመለከታቸው ተናገረ:- "እኛ ክርስቲያኖች ሞትን
አንፈራም:: ሞት ለእኛ ወደ ክርስቶስ መሸገጋገሪያ
ድልድያችን ነውና የምንፈራው ሳይሆን የምንናፍቀው
ነው::" "ኢትፍርሕዎሙ
(አትፍሯቸው)"
(ማቴ. 10:28)
+ይህን ብሎ ወደ ሰማይ ቀና ብሎ ጌታውን አመሰገነ::
ፊቱ ላይ ደስታ እየተነበበ ጨካኞቹ አንገቱን ሰየፉት::
በብርሃን አክሊልም ቅዱሳን መላእክት ከለሉት::
*መሠረታዊው ነገር ቅዱስ ቴዎዶጦስ ለምን አልፈራም?
ነው::
+አጭር መልስ ካስፈለገን ቅዱሱ ያልፈራው ከልቡ
ክርስቶሳዊ በመሆኑ ነው:: ትኩረት እንድንሰጠው
የሚያስፈልገው ግን የሰማዕታት ምስጢራቸው:-
1.በጽኑ የክርስትና መሠረት ላይ መመሥረታቸው
2.ዕለት ዕለት የክርስቶስን ፍቅር መለማመዳቸው
3.ከወሬ (ንግግር) ይልቅ ተግባርን መምረጣቸው
4.በንስሃ ሕይወት መመላለሳቸው
5.ሥጋ ወደሙን የሕይወታቸው ዋና አካል ማድረጋቸው
6.ከእነሱ የቀደሙ ቅዱሳንን ዜና ሕይወት ከልብ
ማንበባቸው
7.በቃለ እግዚአብሔር መታነጻቸው . . . መጠቀስ
የሚችሉ መገለጫዎቻቸው ናቸው::
<+>" ዛሬስ "<+>
=>ዓለማችን ከጠበቅነው በላይ ነፍሰ በላነቷ እየጨመረ
ነው:: ዛሬ የክርስትና ጠላቶች ከጉንዳን በዝተዋል::
*የራሳችን ማንነት
*ክርስትናችን በአፋችን ላይ ብቻ መሆኑ
*እረኞችና በጐች መለያየታቸው . . . ሁሉ እኛ ልናርማቸው
የሚገቡ ናቸው::
*አሸባሪዎች
*አሕዛብ
*የመዝናኛው ዓለም
*ሰይጣን አምላኪ ዝነኞች (Celebrities)
*ሚዲያው
*ማሕበራዊ ድረ ገጾችና መሰል ነገሮች ደግሞ
ልንጠነቀቅባቸው የሚገቡና እኛን ውስጥ ለውስጥ
በልተው የፈጁን የሰይጣን መሣሪያዎች ናቸው::
+ስለዚህም ከዛሬ ጀምረን ባለ መታወክ ክርስትናችንን
ከአፋችን ወደ ልባችን: ከብዕራችን ወደ አንጀታችን
እንድናወርደው ቅድስት ቤተ ክርስቲያን አደራ ትላለች::
+ዛሬ ነገሮችን ረስተን ሌሎች አላስፈላጊ ነገሮችን
ከጀመርን እጅግ አሳፋሪ መሆኑ አይቀርም:: በጐውን
ጐዳና ተከትለን በሃይማኖትና በፍቅረ ክርስቶስ ከጸናን ግን
ማንም ቢመጣም ፈጽሞ አንናወጥም::
+ይልቁኑ
"አምላካችን መጠጊያችንና ኃይላችን:
ባገኘን በታላቅ መከራም ረዳታችን ነው::
ስለዚህም ምድር ብትነዋወጥ: ተራሮችም ወደ ባሕር ልብ
ቢወሰዱ አንፈራም::" (መዝ. 46:1) እያልን ከቅዱስ
ዳዊት ጋር እንዘምራለን::
<< ለዚህ ደግሞ ደመ ሰማዕታት ይርዳን:: በረከታቸው ይድረሰን:: የጌታ ፍቅርም አይለየን >>
+*" ጻድቁ ንጉሥ ቴዎድሮስ "*+
=>በሃገራችን ታሪክ በጣም ተወዳጅ ከነበሩ ነገሥታት
ጻድቁ ቴዎድሮስ ቅድሚያውን ይወስዳል:: በርግጥ
በርካቶቻችን የምናውቀው ስለ ሃገሩ ፍቅር ራሱን የሰዋውን
ዳግማዊ ዐፄ ቴዎድሮስን (1845-1860) ነው:: በበጎ
ሥራውና በቅድስና ሕይወቱ የተመሠከረለት ግን ዛሬ
የምናስበው ቀዳማዊው ነው::
+ቀዳማዊ ዐፄ ቴዎድሮስ የደጉ ዐፄ ዳዊት (ግማደ
መስቀሉን ያመጡት) እና የተባረከችው ሚስታቸው ፅዮን
ሞገሳ ልጅና የጻድቁ ዐፄ ዘርዐ ያዕቆብ ታላቅ ወንድም
ነው:: በኢትዮዽያ ለ3 ዓመታት (ከ1396-1399) ብቻ
ነግሦ እያለ እንደ ንጉሥ ሳይሆን-
*ከጠዋት እስከ ማታ ድሃ እንዳይበደል ፍርድ
እንዳይጉዋደል ይታትር የነበር::
*ጾምና ጸሎትን የሚያዘወትር::
*ወገቡን ታጥቆ ነዳያንን የሚያበላ::
*ለአብያተ ክርስቲያናትም የሚጨነቅ ደግ ሰው ነበር::
+ስለዚህም በሕዝቡ እጅግ ተወዳጅ ነበር:: በነገሠ በ3
ዓመቱ ዐርፎ በዝማሬና በለቅሦ ሥጋውን ተሸክመው
ሲሔዱ ወንዝ ተከፍሎላቸዋል:: ከመቃብሩም ላይ ጸበል
ፈልቁዋል::
=>ዘለዓለም ሥላሴ ደግ መሪና ሰላማዊ ዘመንን ያድሉን::
=>መጋቢት 7 ቀን የሚከበሩ ዓመታዊ የቅዱሳን በዓላት=
1.ጻድቁ ኢትዮዽያዊ ንጉሥ ዐፄ ቴዎድሮስ
2.ቅዱስ ቴዎዶጦስ ሰማዕት
3.ቅዱስ ፊልሞን ሰማዕት
4.ቅዱስ አብላንዮስ ሰማዕት
=>ወርሐዊ በዓላት
1.ሥሉስ ቅዱስ (አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ)
2.አባ ጊዮርጊስ ዘጋስጫ
3.አባ ሲኖዳ (የባሕታውያን አለቃ)
4.አባ ዳንኤል ዘገዳመ ሲሐት
5.አባ ባውላ ገዳማዊ
6.ቅዱስ አትናቴዎስ ሐዋርያዊ
7.ቅዱስ አግናጥዮስ (ለአንበሳ የተሰጠ)
=>+"+ ነፍስ ሁሉ በበላይ ላሉት ባለ ሥልጣኖች ይገዛ::
ከእግዚአብሔር ካልተገኘ በቀር ሥልጣን የለምና::
ያሉትም ባለ ሥልጣኖች በእግዚአብሔር የተሾሙ ናቸው::
ስለዚህ ባ ለሥልጣንን የሚቃወም የእግዚአብሔርን
ሥርዓት ይቃወማል:: . . . ለሁሉ እንደሚገባው አስረክቡ::
ግብር ለሚገባው ግብርን: ቀረጥ ለሚገባው ቀረጥን:
መፈራት ለሚገባው መፈራትን: ክብር ለሚገባው ክብርን
ስጡ:: +"+ (ሮሜ. 13:1-8)
<<< ወስብሐት ለእግዚአብሔር >>>

ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ነኝ:=>+*"+<+>††በቤተክርስቲያናችን ስርአት መሰረት 7 ጊዜ እንፀልያለን ። የእነሱም ትርጉም ††

~በቤተክርስቲያናችን ስርአት መሰረት 7 ጊዜ እንፀልያለን ።
የእነሱም ትርጉም
1= ጠዋት 12:00 ሰአት፡- አንድ ክርስቲያን እግዚአብሔርን
አምላክን በፀሎት የሚያመሰግንበት ምክንያት (ሚስጥር)
እግዚአብሔር አምላክ ሌሊቱንና ጨለማውን አሳልፎ ብርሀን
እንድናይ ስላበቃን በዚህ ሰአት እግዚአብሔር አምላካችንን
እንድናመሰግን ታዝዝዋል። አንድም በዚህ ሰአት ጌታችን
ለክስ ከጲላጦ ፊት ቆሞ የተወቀሰበት ሰአት ስለሆነ አንድም
በዚ ሰአት አባታችን አዳም ያልተፈቀደለትን እፅ በልቶ ከገነት
የተባረረበት ሰአት ስለሆነ ነው። አንድ ክርስቲያን ይህን ሁሉ
እያሰበ ወደ አምላኩ እንዲፀልይ ታዝዋል
2=ከጠዋቱ 3:00 ሰአት፡- አንድ ክርስቲያን እንዲፀልይ
የታዘዘበት ምክንያት (ሚስጥር)
በዚህ ሰአት እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ብስራተ
ገብርኤልን የሰማችበት ሰአት ስለሆነ ነው አንድም በዚህ
ሰአት እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ጌታችንን
የፀነሰችበት ሰአት ስለሆነ ነው አንድም ጌታችን መድሀኒታችን
ኢየሱስ ክርስቶስ ከ ጲላጦስ ፊት ቀርቦ የተገረፈበት ሰአት
ስለሆነ ዮሐ 19 ፥1 ሐዋ ስራ 2፥15 እያንዳንዱ ክርስቲያን
ይሔንን የመሳሰሉ ሁሉ እያሰበ እግዚአብሔር አምላኩን
እንዲያመሰግን ታዝዋል
3= 6:00 ሰአት፡-አንድ ክርስቱያን እኩለ ቀን (ከ ቀኑ
6ሰአት) ሲሆን እንዲፀልይ የታዘዘበት ምክንያት ወይም
(ሚስጥር )
ጌታችን በቀራኔዎ አደባባይ በመስቀል ተሰቅሎበታልና
አንድም ልብሱን ተገፎበታል አንድም ሳዶር አላዶር ዳናት
ሮዳስ በተባሉ ችንካሮች ተቸንክሮበታል አንድ ክርስቲያን ይህን
ሁሉ እያሰበ በዚህ ሰአት እንዲፀልይ ታዞበታል
4= ከቀኑ 9:00 ሰአት፡- አንድ ክርስቲያን የሚፀልይበት
ምክንያት (ሚስጥር)
አይሁዶች ጌታችን መድሀኒታችን ኢየ�ሱስ ክርስቶስን መራራ
ሐሞት አጠጥተውበታል አንድም ቅድስት ነፍሱን ከ ክቡር
ስጋው የለየበት ሰአት ነውና አንድም በመስቀል እንዳለ 7ቱን
አፅርሀ መስቀል የተናገረበት ማር 15፥34 ማቴ 27፥50
አንድ በዚህ ሰአት ይህንን እያሰበ እንዲፀልይ ታዝዋል
5= ከቀኑ 11፡00 ሰአት፡- አንድ ክር�ቲያን እንዲፀልይበት
የታዘዘበት ምክንያት ወይም (ሚስጥር)
ጌታችን መድሀኒታችን እየሱስ ክርስቶስ ወደ ከርሰ መቃብር
የወረደበት ሰአት ስለሆነ አንድም ቀኑን በሰላም አሳልፎ ወደ
ምሽት በሰላም ያደረሰን አምላክ ምስጋ ስለሚገባው ነው
ይህንን የመሳሰሉ ሁሉ ሕዝበ ክርስቲያን እንዲያስቡ ታዘዋል
6= ከምሽቱ 3:00 ሰአት፡- በዚህ ሰአት አንድ ክርስቲያን
እንዲያመሰግን የታዘዘበት ምክንያት (ሚስጥር)
በዚህ ሰአት እራሱ ጌታችን መድሀኒታችን እየሱስ ክርስቶስ
ስርአተ ፀሎት አሳይቶበታል አንድም በዚህ ሰአት ጌታችንን
አይሁድ በይሁዳ ጠቁዋሚነት ተረበርበው የያዙበት ሰአት
ስለሆነ ነው አንድም በዚህ ሰአት አንድ ክርስቲያን ከመተኛቱ
በፊት በሰላም ያዋለንንና ያስመሸንን አምላክ አመስግኖ
መተኛት አለበት ይህን ሁሉ እያሰበ እንዲፀልይ ታዝዋል
7= መንፈቀ ሌሊት ከሌሊቱ 6 :00 ሰአት:- በዚህ ሰአት አንድ
ክርስቲያን እግዚአብሔር አምላኩን እንዲያመሰግንበት
የታዘዘበት ምክንያት (ሚስጥር)
በዚህ ሰአት ጌታችን መድሀኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ
ተወልዶበታልና ነው አንድም ጌታችን መድሀኒታችን ኢየሱስ
ክርስቶስ ሙስና መቃብርን ድል አድርጎበታልና(ተነስቶበታ
ል) በመዝሙረ ዳዊት አመሰግንህ ዘንድ በመንፈቀ ሌሊት
እነሳለው ባለው መሰረት ጳውሎስ ሲላስ በእስር ቤት ሆነው
ወደ እግዚአብሔር የፀለዩበት ስለሆነ ነው አንድም የሰው ልጅ
የሚመጣበት ጊዜ ማታ ይሁን መንፈቀ ሌሊት ይሁን ዶሮ
ሲጮህም ይሁን ሲነጋም ቢሆን አይታወቅምና ባለው
አምላካዊ ቀል መሰረት በመንፈቀ ሌሊት አንድ ክርስቲያን
እንዲፀልይ ታዝዋል
የቅዱሳን ሁሉ ጸሎት እና ምልጃ አክሊልና ጉልላት በሆነው
በእናታችን በወላዲተ አምላክ ቅድስት ድንግል ማርያም
ጸሎት ሁላችንንም ይማረን፡፡

ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ነኝ:=>+*"+<+>††ቅዱስ ዮሐንስ ወልደ ነጎድጓድ††

ዮሐንስ ማለት ፍሰሓ ወሐሴት ሠላም ርህራሄ ወሳህል
ማለት ነው። ወልደ ነጎድጓድ፣ አቡቀለምሲስ፣ ነባቤ መለኮት፣
ታዖሎጎስ ይለዋል፡፡ “ቃዳሚሁ ቃል ውእቱ” ብሎ ምስጢረ
ሥላሴን አምልቶ አስፍቶ ይናገራልና፡፡ ፍቁረ እግዚእ
ይለዋል፡፡ “ዝኩ ካልዕ ረድዕ ዘያፈቅሮ እግዚእ ኢየሱስ”
ይለዋልና፡፡ ዮሐንስ 21፡7 መውደድንስ ሁሉንም ይወዳቸው
የለምን ቢሉ የርሱ የተለየ ነውና፡፡ ከቶማስም የሱ መወደድ
ይበልጣል፡፡ ቶማስ በጦር የተወጋ ጎኑን ቢዳስሰው እጁ ከእሳት
እንደገባ ጅማት ተኮማትሯል፡፡ እርሱን ግን በከናፍሩ ቢስመው
በጭኑ ቢያስቀምጠው ምንም ምን አልሆነም ::
ንጹህ ወድንግል ይለዋል፡፡ ጌታን ከመውደዱ የተነሳ ጌታም
እናቱን እነዃት እናትህ ሲል ድንግል ማርያምን በሱ በኩል
ተሰታናለች፡፡ እኛም ዛሬ ልጆቿ ነንና ደስ ይበለን ይበላችሁ
የድንግል ማርያም የአስራት፣ የተስፋና የስስት ልጆች፡፡ ዮሐንስ
19፡26፡፡ ዮሐንስ ሀገሩ ገሊላ አውራጃ ሲሆን ከታላቅ
ወንድሙ ከያዕቆብና ከአባቱ ከዘብድዮስ ጋር ዓሣ እያጠመደ
ይኖር ነበር። እናቱ ከ36ቱ ቅዱሳት አንስት አንዷ ስትሆን
ማርያም ትባላለች።
ዮሐንስ ከ12ቱ ሐዋርያት አንዱ ሲሆን በሕይትም በኑሮም
ጌታ ስለሚመስል (ፍቁረ እግዚእ) ይባለል። ነገረ መለኮትን
በበለጠ ከሌሎች አምልቶ አስቶ በጥልቀት በማስተማሩ ነባቤ
መለኮት (ታዖሎጎስ)ተሰኝቷል። ስለጌታም ባለው ቅናት ባሳየው
የሀይል ሥራ በኦኔርጌስ (ወልደ ነጎድጓድም) ተብሏል። ፍጥሞ
በምትባል ደሴት በራዕይ መጻእያትን በመግለጡ ባለራዕይ
(በግሪክ አቡቀለምሲስ) ይባለል። በዕለተ ዓርብ በመስቀል ሥር
ተገኝቶ የጌታን መከራ መስቀል በማየቱ ፊቱ በሀዘን
ስለተቋጠረ ቁጽረ ገጽ (ፊቱ በሀዘነ የተቋጠረ) ስምም
ተሰቶታል። ከቅዱስ ጴጥሮስ ጋር የፋሲካን እራት ያዘጋጀ
አንካሳን የፈወሰ ታለቅ ሐዋርያ ነው። (ሊቃስ 22፡8) እስከ
መስቀል አምላኩን ተከትሎ እመቤታችንን በአደራ የተረከበ
ባለአደራ ሐዋርያ ሲሆን ከጰራቅሊጦስ በዓል በኋላ ከቅዱስ
ጴጥሮስ ጋራ በኢየሩሳሌም በአንጾኪያ በሎዶቅያ በእስያ
ከተሞች በተለይ በኤፌሶን በአሁኑ ቱርክ አስተምሯል።
(ዮሐ.19፡26) በወጣትነት ዕድሜው ተጠርቶ በዕለተ ዓርብ
የጌታን መከራ እያሰበ ያነባ የነበረ በፍቅር በታማኝነት
እስከመጨረሻ ድረስ የጸና ከጌታ ያልተለየ ወንጌላዊ ሲሆን
ወንጌልን ጨምሮ 3 መልዕክታትን የጻፈ እንዲሁም ሐዋርያው
ዩሐንስ በፍጥሞ ደሴት በዛሬቱ ቱርክ ለሰባት አመታት ታስሮ
በነበረበት ወቅት ወንጌሉንና ራዕዩን ጽፏል። አይገርምህም
ሐዋርያው ዩሐንስ በእስር እያለ ነው ራዕዩን የጻፈው!!!
ሐዋርያው ቅ/ጳውሎስ ደግሞ በቀዝቃዛ እስር ቤት እያለ ብዙ
መልእክታቱን ጻፈ!!! ሐዋርያቱ በእስር ቢሆኑ እንኳን
ስለቅድስት ቤተክርስቲያን አገልግሎት አብዝተው ያስቡ ነበር።
የሐዋርያቱ ብርታት ያበርታን።
ዩሐንስ ወንጌሉን በፍጥሞ ደሴት ሲጽፍ እንዲህ ብሎ ጀመረ፦
ዩሐንስ 1:1
+++ በመጀመሪያ ቃል ነበረ; ቃልም በእግዚአብሔር ዘንድ
ነበረ ቃልም እግዚአብሔር ነበረ።እኛም በቅዳሴ ላይ ሁሌ
የዩሐንስ ወንጌል ሲነበብ ቀዳሚሁ ቃል ሥጋ ኾነ ወሃደረ
ላዕሌነ ብለን እንቀበላለን። ግሩም ዜማ ከግሩም ሚስጢር
ጋር አባቶቻችን አወረሱን።
እስቲ ሚስጢሩን እንይ፦
በመጀመሪያ ቃል ነበረ፦ እንደምናውቀው ቃል ኢየሱስ
ክርስቶስ ነው። ኢየሱስ ክርስቶስ አልፋና ዖሜጋ መጀመሪያና
መጨረሻ ነውና ራዕ 22:12። ቃልም እግዚአብሔር ነበር፦
መጽሃፍ አንባቢው ያስተውል ይላል; ምን እንደሚል ልብ
እንበል “ቃልም እግዚአብሔር ነበር” ሐዋርያው በመጀመሪያ
ቃል ነበር ብሎን ነበር; ያ ቃል እግዚአሔር እንደሆነ
አስረዳን!!! በዚሁ ምዕራፍ ላይ ወረድ ብሎ /ዩሐንስ 1:14/
“ያ ቃል ሥጋ ሆነ ይለናል” እስቲ ጥያቄ እንጠያየቅ; ሐዋርያው
ያ ቃል ሥጋ ሆነ ብሏል ከማን? ከማን ሥጋን ነሳ?
ከእመቤታችን ከቅድስት ድንግል ማርያም ከሥጋዋ ሥጋ ከነፍሷ
ነፍስ ነስቶ በኤፍራታ በቤቴልሔም ተወለደ።
+++ የፍጥሞ ደሴት ታሪክ እነሆ፦ ሐዋርያው ዩሐንስ በፍጥሞ
ደሴት ወንጌሉን መጻፍ ሲጀምር የመለኮትን ነገር ጽፎ
የሚጨርስ መስሎት ብእሩን አነሳ። በመጀመሪያ ቃል ነበረ
አለና ሊጨርስ አሰበ፤ ያኔ መልአኩ ቅ/ሚካኤል ተገልጦ
በፍጥሞ ደሴት ያለችውን ባህር በእንቁላል ቅርፊት እየቀዳ
ወደ መሬት ሲያፈስ አየው; ሐዋርያው ዩሐንስም እንዴት ይህ
ታላቅ ባሕር በእንቁላል ቅርፊት ያልቃል ብሎ ጠየቀው;
መልአኩም እኔስ ብሞክር ፍጥረትን ነው አንተስ የፈጣሪን
ባሕርይ የሚያልቅ መስሎህ ትሞክር አይደለምን አለው። ያኔ
ሐዋርያው ዩሐንስ ይህን ተረድቶ ወዲያው ከእግዚአብሔር
የተላከ ስሙ ዩሐንስ የሚባል አንድ ሰው አውቃለሁ ብሎ
ስለመጥምቁ ዩሐንስ ታሪክ የቀጠለውም በዚሁ ምክንያት
ነበር። ዩሐንስ 1:19
ከሐዋርያው፣ ከዮሐንስ ወልደ ነጎድጓድ ረድኤትና በረከት
ይክፈለን ምልጃና ጸሎት ከሁላች ጋር ይሁን አሜን !!!
ወስብሐት ለእግዚአብሔር ወለወላዲቱ ድንግል ወለመስቀሉ
ክቡር ይቆየን አሜን።

ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ነኝ:=>+*"+<+>††መጋቢት 5 ፃድቁ አቡነ ገ/መንፈስ ቅዱስ ዓመታዊ ክብረ በዓል ††

መጋቢት 5 ፃድቁ አቡነ ገ/መንፈስ ቅዱስ ዓመታዊ ክብረ
በዓል በደመቀ ሁኔታ ተከብሮ ይውላል ።
በዚህ እለት እምናከብረው የእረፍት መታሰቢያቸውን ሲሆን
ከገድላቸውም እንዲህ ተፅፎ እናገኘዋለን ።
ፃድቁ አቡነ ገብረ መንፈስ ቅዱስ የተወለዱት ግብፅ ንሂሳ
በምትባል ቦታ ከአባታቸው ስምዖን ከእናታው አቅሌስያ ነው።
በአጠቃላይ የኖሩበት ዕድሜ 562 አመት ሲሆን 300
ዓመቱን በግብጽ 262 ቱን በኢትዮጵያ 100 ዓመት በዝቋላ
በተጋድሎ ያሳለፉ ታላቅ አባት ናቸው።
መጋቢት 5 በገድለ አቡነ ገ/መንፈስ ቅዱስ
ዕለቱ ቅዳሜ ለእሁድ አጥቢያ ሰዓቱ ከሌሊቱ ስድስት ሰዓት
ሆኗል፤ አሁንም ህማሙን እየታገለ እያላበው በድካም
ለፍጥረቱ ሁሉ ይለምናል፤ “አቤቱ ህዝብህን አድን ርስትህን
ኢትዮጰያንም ባርክ” ይላል። ህመም የጀመረው መጋቢት 3
ዓርብ ቀን ነው፤መታመሙን የሰሙ እንደርሱ ቅዱሳን የሆኑት
ዘርአ ቡሩክ፤ ፍሬ ቅዱስ፤ያዕቆብ፤ብንያምና ዮሴፍ እንዲሁም
በወቅቱ የኢትዮጰያ ንጉስ የነበረው እንድርያስ ሊጠይቁት
ተሰብስበዋል ወደ አጠገቡ መድረስ ግን አልተቻላቸውም
አባታችን ገብረመንፈስ ቅዱስ የሚጋርደው እንጨት ዛፍ
በሌለበት በርሃ እንደ አንበሳ ተኝቶ አዩት በላዩ ያረፈው
የእግዚያብሔር ጸጋ ከፊቱ የሚወጣው ብርሃን ቀይ መልኩ
ረዥም የራስ ጠጉሩ እንደ ነጭ ሐር የሚሆን ጽሕሙ
አስደነቃቸው። ከሌሊቱ ሰባት ሰዓት ሲሆን ከሰማይ ታላቅ
ነጎድጓድ ድምጽ ተሰማ ጌታችን መላአክትን አስከትሎ ወደ
አባታችን ወረደ፤ ከሰማይ ወደ ምድር ህብሩ አምሳያው ልዩ
ልዩ የሆነ እንደ ጸሐይና እንደ ጨረቃ የሚያበራ እንደ
ወንጪፍ ድንጋይ ይወረወር ነበር ከዚያ የነበሩ ሁሉ ፈሩ ወደ
ኃላም ሸሹ ምድር ራደች ተራሮች ኮረብቶች ተናወጡ ብርቱ
ጩኸት
ንውጽውጽታ ሆነ። “ወዳጄ ገብረመንፈስ ቅዱስ ሰላም ላንተ
ይሁን” እነሆ የማይታበል ቃል ኪዳን እገባልኃለው ስምህን
የጠራ መታሰቢያህን ያደረገውን፤ እጣን ቋጥሮ ግብር ሰፍሮ
መባ ይዞ ቤትህ የመጣውን እምርልኃለው አንተ ከገባህበት
ገነት መንግስተ ሰማያት አገባዋለሁ አለው፤ አባታችንም
“አቤቱ ጌታ ሆይ የኢትዮጰያን ህዝብ ማርልኝ” አለው፤ እነሆ
ምሬልኃለው አስራት በኩራት አድርጌም ሰጥቼሃለው፤
ከመጋቢት አምስት ቀን ጀምሮ ዝክርህን ያድርጉ
በአማላጅነትህም ይማጸኑ አለው። ከዚህ በኃላ ሰባቱ ሊቃነ
መላእክት የአባታችንን ነፍስ ሊቀበሉ ወረዱ በታላቅ
ምስጋናም ወደ ሰማይ አሳረጉት ስጋውንም ይዘውት ሄዱ የት
እንደተቀበረ ግን እስካሁን አይታወቅም አንዳንዱ
በእየሩሳሌም ነው ይላሉ፤ ሌላው በምድረ ከብድ ነው ይላል
ግን እስካሁን ልክ እንደ ሊቀ ነብያት ሙሴ ስጋ የት
እንደተቀበረ አይታወቅም። ገድሉ ትሩፋቱ ከሰማይ ከዋክብት
ከምድር አሸዋ ይበዛል ኢትዮጰያን አብዝቶ ይወዳታል፤
ምድራዊ ምግብ አልተመገበም የእናቱን ጡት እንኳን
አልጠባም፤ ልብስ፤ መጠለያ አልፈለገም፤ የክረምት ቁር የበጋ
ሐሩር እየተፈራረቀበት በተጋድሎ 562 ዓመት ኖረ፤ በዛሬዋ
ቀን ሩጫውን ጨረሰ። ለእግዚያብሔር ምስጋና ይሁን
እኛንም ከአባታችን በረከት ያሳትፈን።
አምላከ ገ/መንፈስ ቅዱስ መንገዱን ያብራልን ። ገድሉንም
ሰሚወች ብቻ ሳንሆን እምንማርበት ያድርግልን ።

Friday, March 3, 2017

ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ነኝ:=>+*"+<+>††የአብይ ጾም ሦስተኛ ሳምንት ምኩራብ††+<+>

ምኩራብ (የዐቢይ ጾም ሦስተኛ ሳምንት)
(ዮሐ. 2÷12-ፍጻ.)፡- ከዚህም በኋላ እርሱና እናቱ÷
ወንድሞቹና ደቀ መዛሙርቱም ወደ ቅፍርናሆም ወረዱ፤
በዚያም ብዙ ያይደለ ጥቂት ቀን ተቀመጡ፡፡ የአይሁድም
የፋሲካቸው በዓል ቀርቦ ነበር፤ ጌታችን ኢየሱስም ወደ
ኢየሩሳሌም ወጣ፡፡ በቤተ መቅደስም በሬዎችንና በጎችን÷
ርግቦችንም የሚሸጡትን÷ገንዘብ ለዋጮችንም ተቀምጠው
አገኘ፡፡ የገመድም ጅራፍ አበጀ፤ በጎችንና በሬዎችን÷ ሁሉንም
ከቤተ መቅደስ አስወጣ፤ የለዋጮችንም ገንዘብ በተነ፤
ገበታዎቻቸውንም ገለበጠ፡፡ ርግብ ሻጮችንም÷ “ይህን
ከዚህ አውጡ፤ የአባቴን ቤት የንግድ ቤት አታድርጉ”
አላቸው፡፡ ደቀ መዛሙርቱም÷ “የቤትህ ቅናት በላኝ” የሚል
ቃል ተጽፎ እንዳለ ዐሰቡ፡፡ አይሁድም መልሰው÷ “ይህን
የምታደርግ ምን ምልክት ታሳያለህ?” አሉት፡፡ ጌታችን
ኢየሱስም÷ “ይህን ቤተ መቅደስ አፍርሱት፤ በሦስተኛውም
ቀን አነሣዋለሁ” ብሎ መለሰላቸው፡፡ አይሁድም÷ “ይህ ቤተ
መቅደስ በአርባ ስድስት ዓመት ተሠራ፤ አንተስ በሦስት ቀኖች
ውስጥ ታነሣዋለህን?” አሉት፡፡ እርሱ ግን ይህን የተናገረው
ቤተ መቅደስ ስለ ተባለ ሰውነቱ ነበር፡፡ ከሙታን በተነሣ
ጊዜም ደቀ መዛሙርቱ ስለዚህ እንደ ነገራቸው ዐሰቡ፤
በመጻሕፍት ቃልና ጌታችን ኢየሱስ በነገራቸውም ነገር
አመኑ፡፡ ጌታችን ኢየሱስም በፋሲካ በዓል በኢየሩሳለም ሳለ
ብዙ ሰዎች ያደረገውን ተአምራት ባዩ ጊዜ በስሙ አመኑ፡፡
እርሱ ጌታችን ኢየሱስ ግን አያምናቸውም ነበር፤ ሁሉን
እያንዳንዱን ያውቀዋልና፡፡ የሰውንም ግብሩን ሊነግሩት
አይሻም፤ እርሱ በሰው ያለውን ያውቅ ነበርና፡፡(ዮሐ. 2÷12-
ፍጻ.)
የዕለተ ሰንበት መዝሙር (ከጾመ ድጓ)
ቦአ ኢየሱስ ምኩራበ አይሁድ ወመሐረ ቃለ ሃይማኖት
ወይቤሎሙ ምጽዋተ አበድር እመሥዋዕት አነ ውእቱ እግዚኣ
ለሰንበት ወአቡሃ ለምሕረት እግዚኣ ውእቱ ለሰንበት ወልደ
እጓለ እመሕያው ኢትግበሩ ቤተ አቡየ ቤተ ምስያጥ ቤትየሰ
ቤተ ጸሎት ይሰመይ ቦአ ምኩራቦሙ ወገሠፆሙ ያርምሙ
አንከሩ ምህሮቶ ሞገስ ቃሉ ወጣዕመ ነገሩ ወሣዕሣዓ አፉሁ፡፡
ትርጉም:- ጌታችን ኢየሱስ ወደ አይሁድ ምኩራብ ገባ፤
የሃይማኖት ቃልን አስተማረ፤ ከመሥዋዕት ይልቅ ምሕረትን
እወዳለሁ፤የሰንበት ጌታዋ የምሕረት አባቷም እኔ ነኝ፤ የሰው
ልጅም የሰንበት ጌታዋ ነው ፡፡ያባቴን ቤት የንግድ ቦታ
አታድርጉት፤ቤቴስ የጸሎት ቤት ይባላል (እያለ የሃይማኖትን
ቃል አስተማራቸው፡)፡ ወደ ምኩራባቸውም ገብቶ ዝም ይሉ
ዘንድ ገሠፃቸው፤ እነርሱም ትምህርቱን፣ የቃሉን ግርማ፣
የአነጋገሩን ጣዕምና፣ የአንደበቱን ቅልጥፍና አደነቁ።
እንደ ቤተክርስቲያናችን ሥርዓትና ትውፊት መሠረት በዐቢይ
ጾም ስምንቱ ሰንበታት ሊዘመር የተዘጋጀው የጾመ ድጓው
መዝሙር ነው፡፡ በየሰንበቱ የሚነበቡት የመጽሐፍ ቅዱስ
ምንባባት ፣ የሚዘመረው የዳዊት መዝሙር (ምስባክ)
ከሰንበቱ ስያሜ ጋር የሚያያዙና የሚዛመዱ ናቸው፡፡
በሰንበታቱ ውስጥ የሚነበበውና የሚዘመረውም ጌታችን
በመዋዕለ ስብከቱ ያስተማራቸውን ትምህርቶችና የሠራቸውን
ዋና ዋና ተዓምራትና መንክራት የሚመለከቱ ናቸው፡፡ ጾሙ
የጌታ ጾም ስለሆነ ሁሉም መዝሙራትና ምንባባት ከጌታ
ትምህርትና ሥራ ጋር የተያያዙ ናቸው፡፡ በዚህ መሠረት
ሦስተኛው ሰንበት ምኩራብ ተብሎ ተሰይሟል፡፡
ምኩራብ ማለት ሰቀላ መሰል አዳራሽ ማለት ነው። አይሁድ
ስግደትና መሥዋዕታቸውን የሚያቀርቡት በኢየሩሳሌም
ባለው መቅደስ ብቻ ነው ብለው ቢያምኑም (ዮሐ 4፥20)
፤በየተበተኑበት ቦታ ምኩራብ እየሠሩ ትምህርተ ኦሪትን
በመማር ሃይማኖታቸውን ያፀኑ ነበር። ምኲራብ የአይሁድ
የጸሎት ቤት ሲሆን በብሉይ ኪዳን ዘመን የአይሁድ አምልኮ
በኢየሩሳሌም በነበረው ቤተ መቅደስና በሥርዓቱ የተመሠረተ
ነበር፡፡ የመጽሐፍ ቅዱስ መዝገበ ቃላት እንደሚገልጸው
ናቡከደነጾር የአይሁዳውያንን ቤተ መቅደሱን አፍርሶ
ሕዝቡንም ወደባቢሎን ካፈለሰ ጊዜ ጀምሮ አይሁድ
በሚገኙባቸው ሥፍራዎች ሁሉ ለጸሎትና ለማኅበረተኛነት ልዩ
ቤት ሊሠሩ እንደጀመሩ ይገልጻል፡፡
አይሁድ በምኲራቦቻቸው የሕግንና የነቢያትን መጻሕፍት /
የብራና ጥቅሎች/ በአንድ ሣጥን ውስጥ ያስቀምጣሉ፡፡
በመሆኑ የጸሎት ሥፍራዎቻቸውን ለትምህርትና ለአምልኮ
ይጠቀሙባቸዋል፡፡ በሕገ ኦሪት የአይሁዳውያን ወደ ቤተ
መቅደስ መሄድ ሕግ ነበር፡፡ በተለያዩ ጊዜያት ለተለያዩ
ተግባራት ከሚሄዱበትም ይልቅ በዓመት አንዴ የሚቀርበውን
መሥዋዕትና መብዓ ለመስጠት ወደ ቤተ መቅደስ ይወጡ
ነበር፡፡ ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስም ሕግ ሊፈጽም ወደ ቤተ
መቅደስ ይሔድ ነበር፡፡ “ዐሥራ ሁለት ዓመትም በሞላው
ጊዜ እንዳስለመዱ ወደ ኢየሩሳሌም ለበዓል ወጡ” እንዲል /
ሉቃ.2፥42/ “ዕለት ዕለትም በቤተ መቅደስ /ምኩራብ/
ያስተምር ነበር፡፡” /ሉቃ.19፥47/ ፡፡
በዚሁ ዕለት የሚዘመረው ጾመ ድጓ ከዋዜማው ጀምሮ እስከ
ሰላሙ ድረስ በዕለተ ሰንበት “ቦአ ኢየሱስ ምኩራበ አይሁድ
ኢየሱስ በሰንበት ቀን ወደ አይሁድ ምኩራብ ገባ” እያለ
ኢየሱስ በአይሁድ ምኩራብ ማስተማሩን እያነሳ ስለሚዘምር
ይህን ሰንበት ለዚህ ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በምኩራብ
እየገባ ለማስተማሩና በምኩራብ የሚሸጡ የሚለውጡ
ነጋዴዎችን ስለማስወጣቱ ቤተ መቅደሱን ስለማስከበሩ
መታሰቢያ ሆኖ ነው፡፡ማቴ21፡12
ጌታችን በምኩራብ እየተገኘ ሲያስተምር ትምህርቱን ሕግን
አውቆ እንደሚያሳውቅ ሠራዔ ሕግ ስለሆነ በሙሉ ሥልጣንና
ኃይል ያስተምር ነበር፡፡“ቦአ ኢየሱስ ምኩራበ አይሁድ
ወመሐረ ቃለ ሃይማኖት ወይቤሎሙ ምጽዋተ አበድር
እመሥዋዕትአነ ውእቱ እግዚኣ ለሰንበት ወአቡሃ ለምሕረት
እግዚኣ ውእቱ ለሰንበት ወልደ እጓለ እመሕያውኢትግበሩ ቤተ
አቡየ ቤተ ምስያጥ ቤትየሰ ቤተ ጸሎት ይሰመይ ቦአ
ምኩራቦሙ ወገሠፆሙያርምሙ አንከሩ ምህሮቶ ሞገስ ቃሉ
ወጣዕመ ነገሩ ወሣዕሣዓ አፉሁ፡፡ ጌታችን ኢየሱስ ወደ
አይሁድ ምኩራብ ገባ፤ የሃይማኖት ቃልን
አስተማረ፤ከመሥዋዕት ይልቅ ምሕረትን እወዳለሁ፤የሰንበት
ጌታዋ የምሕረት አባቷም እኔ ነኝ፤ የሰው ልጅምየሰንበት
ጌታዋ ነው ፡፡ያባቴን ቤት የንግድ ቦታ አታድርጉት፤ቤቴስ
የጸሎት ቤት ይባላል (እያለየሃይማኖትን ቃል አስተማራቸው)
፤ ወደ ምኩራባቸውም ገብቶ ዝም ይሉ ዘንድ
ገሠፃቸው፤እነርሱም ትምህርቱን፣ የቃሉን ግርማ፣ የአነጋገሩን
ጣዕምና፣ የአንደበቱን ቅልጥፍና አደነቁ። የዕለተ ሰንበት
መዝሙር (ከጾመ ድጓ)
ቅዱስ ዳዊትም አስቀድሞ በተናረው ትንቢት መሠረት ጌታ
ለቤተመቅደሱ ቀንቶ አጽድቶት ነበር፡፡
መዝ 68፡9
እስመ ቅንዐተ ቤትከ በልዐኒ
ትዕይርቶሙ ለእለ ይትዔየሩከ ወድቀ ላዕሌየ
ወቀጻዕክዋ በጾም ለነፍስየ፡፡
ትርጉም፦የቤትህ ቅንዓት በልታኛለችና
የሚሰድቡህም ስድብ በላዬ ወድቆአልና
ነፍሴን በጾም አስመረርሁአት፡፡
በነብዩ በኢሳይያስ እንደተጻፈ ጌታ በአይሁድ ምኩራብ ገብቶ
መጽሐፍ እንዲሰጡት ጠይቆ የሚሰሙት ቃል ዛሬ በጆሯቸው
እንደተፈጸመ እንዲህ ሲል እንደነገራቸው፡፡ “ኢየሱስም
በመንፈስ ኃይል ወደ ገሊላ ተመለሰ፤ ስለ እርሱም በዙሪያው
ባለችው አገር ሁሉ ዝና ወጣ። እርሱም በምኵራባቸው
ያስተምር ሁሉም ያመሰግኑት ነበር። ወዳደገበትም ወደ
ናዝሬት መጣ፤ እንደ ልማዱም በሰንበት ቀን ወደ ምኵራብ
ገባ ሊያነብም ተነሣ። የነቢዩንም የኢሳይያስን መጽሐፍ ሰጡት
መጽሐፉንም በተረተረ ጊዜ። “የጌታ መንፈስ በእኔ ላይ ነው
ለድሆች ወንጌልን እሰብክ ዘንድ ቀብቶኛልና ለታሰሩትም
መፈታትን ለዕውሮችም ማየትን እሰብክ ዘንድ የተጠቁትንም
ነጻ አወጣ ዘንድ የተወደደችውንም የጌታን ዓመት እሰብክ
ዘንድ ልኮኛል፡፡” ተብሎ የተጻፈበትን ስፍራ አገኘ።
መጽሐፉንም ጠቅልሎ ለአገልጋዩ ሰጠውና ተቀመጠ
በምኵራብም የነበሩት ሁሉ ትኵር ብለው ይመለከቱት ነበር።
እርሱም። “ዛሬ ይህ መጽሐፍ በጆሮአችሁ ተፈጸመ ”ይላቸው
ጀመር። ሁሉም ይመሰክሩለት ነበር ከአፉም ከሚወጣው
ከጸጋው ቃል የተነሣ እየተደነቁ። “ይህ የዮሴፍ ልጅ
አይደለምን? ”ይሉ ነበር። እርሱም። ያለ ጥርጥር ይህን
ምሳሌ። “ባለ መድኃኒት ሆይ ራስህን ፈውስ፤ በቅፍርናሆም
እንዳደረግኸው የሰማነውን ሁሉ በዚህ በገዛ አገርህ ደግሞ
አድርግ ትሉኛላችሁ” አላቸው። ሉቃ.4፡14
“ከዚህ በኋላ ከእናቱና ከወንድሞቹ ከደቀመዛሙርቱም ጋር
ወደ ቅፍርናሆም ወረደ፣ በዚያም ጥቂት ቀን ኖሩ፡፡ የአይሁድ
ፋሲካም ቀርቦ ነበር ኢየሱስም ወደ ኢየሩሳሌም ወጣ፡፡ ወደ
መቅደስም በሬዎችንና በጎችን ርግቦችንም የሚሸጡትን
ገንዘብ ለዋጮችንም ተቀምጠው አገኘ፤ የገመድም ጅራፍ
አበጅቶ ሁሉን በጎችንም በሬዎችንም ከመቅደስ አወጣቸው፣
የለዋጮችንም ገንዘብ አፈሰሰ፣ ገበታዎቻቸውንም ገለበጠ፣
ርግብ ሻጪዎችንም ይህን ከዚህ ውሰዱ፡፡ የአባቴን ቤት
የንግድ ቤት አታድርጉት አላቸው፡፡ ደቀ መዛሙርቱም የቤትህ
ቅናት ይበላኛል ተብሎ እንደተጻፈ አሰቡ፡፡
አይሁድ መልሰው ይህን ስለምታደርግ ምን ምልክ ት
ታሳየናለህ አሉት፡፡ ኢየሱስም መልሶ ይህን ቤተመቅደስ
አፍርሱት በሦስት ቀንም አነሣዋለሁ አላቸው ስለዚህ አይሁድ
ይህ ቤተ መቅደስ ከአርባ ስድስት ዓመት ጀምሮ ይሠራ ነበር፣
አንተስ በሦስት ቀን ታነሣዋለህን አሉት፡፡ እርሱ ግን ስለ
ሰውነቱ ቤተመቅደስ ይል ነበር፡፡”ዮሐ 2፡12-25 ስለዚህ
ከሙታን ከተነሣ በኋላ ደቀመዛሙርቱ ይህን እንደተናገረ
አሰቡና መጽሐፍንና ኢየሱስ የተናገረውን ቃል አመኑ፡፡
በፋሲካ በዓልም በኢየሩሳሌም ሳለ፣ ያደረገውን ምልክት ባዩ
ጊዜ ብዙ ሰዎች በስሙ አመኑ ነገር ግን ኢየሱስ ሰዎችን ሁሉ
ያውቅ ነበር፤ ስለ ሰውም ማንም ሊመሰክር አያስፈልገውም
ነበርና አይተማመናቸውም ነበር፣ ራሱ በሰው ያለውን ያውቅ
ነበርና፡፡

Saturday, February 25, 2017

ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ነኝ:=>+*"+<+>†† የዐቢይ ጾም ሁለተኛ ሳምንት ቅድሰት ††+*"+<+>

ቅድስት ( የዐቢይ ጾም ሁለተኛ ሳምንት )
«ቅድስት» ማለት የዘይቤ ፍችው « የተቀደሰች የተለየች »
ማለት ነው፡፡ ምስጢራዊ መልእክቱ ግን የምስጢረ አድኅኖት
ታላላቅ ሥራውን ለመጀመር መድኀኒታችን ኢየሱስ ክርስቶሰ
በገዳመ ቆሮንቶስ ገብቶ ከቆመ ሳያርፍ፣ ከዘረጋ ሳያጥፍ
የጾማት የአርብዓው ቀንና ሌሊት ልዩ የሆነችና ክብርት ጾም
የምትጀመርበትን ሁለተኛ ሳምንት ከልብ ያሳስበናል፡፡ ማቴ.
4-2
ቅድሰት የዐቢይ ጾም ሁለተኛ ሰንበት ስያሜ ነው፡፡
ስያሜውም
ከኢትዮያዊው የዜማ ሊቅ ከቅዱስ ያሬድ የተገኘ ነው፡፡ ከዚህ
ሰንበት ዋዜማ ጀምሮ ስለ ዕለተ ሰንበት ቅድስና ይዘመራል፡፡
ቅድስት ቤተ ክርስቲያናችንም ሰንበቱን ስለ ቅድስና ልጆቿን
ታስተምርበታለች ፡፡ በቅዳሴ ጊዜ የሚሰበከው ምስባክ ፤
የሚነበቡ መልዕክታት ፤የሐዋርያት ሥራ ና ወንጌል ስለ
ቅድስት
የሚያስተምሩ ናቸው፡፡
‹‹ቅዱስ›› ማለት ልዩ፤ክቡር ማለት ነው፡፡ እግዚአብሔር
አምላካችን በባሕርዩ ቅዱስ ነው፡፡ ይህም ቅድስና ከማንም
ያላገኘው የባሕርይ ገንዘቡ ነው፡፡ መጻሕፍትም የባሕርይ
ቅድስናውን ተባብረው መስክረዋል፡፡ ባባሕርዩ ቅዱስ ስለሆነ
‹‹ቅዱስ፡ቅዱስ፡ቅዱስ›› እየተባለ ይመሰገናል፡፡( ኢሳ 6፡
1-3፤40፡25 ራዕ 15፡4 ፤ 1ሳሙ2፡2-3፡፡) እኛም ቅዱስ
ልጁ
በሥጋ ተገልጦ እንዳስተማረን በየዕለት ጸሎታችን ‹‹ስምህ
ይቀደስ›› እንለዋለን፡፡ የቅድስና ምንጭ ፡ ቅድስናን የሚሰጥ
እርሱ ብቻ ነው፡፡ ‹‹ ቅዱስ›› የሚለው ቃል ለሰዎች ፡
ለመላእክት ፡ ለቦታ ፡ለዕቃ፡ ለዕለታት … ቢቀጸልም
ቅድስናቸው
በባሕርይው ቅዱስ ከሆነው ከእግዚአብሔር የተገኘ ነው፡፡
ይህም
የጸጋ ቅድስና ይባላል፡፡
እግዚአብሔር ቅዱስ ስለሆነ በመልኩና በምሳሌው አክብሮ
የፈጠረንን እኛም ቅዱሳን እንድንሆን ይፈለጋል፡፡ቅዱስ
ጴጥሮስ
‹‹ዳሩ ግን እኔ ቅዱስ ነኝና ቅዱሳን ሁን›› ተብሎ ስለተጻፈ
የጠራቸው ቅዱስ እንደሆነ እናንተ ደግሞ በኑሮአችሁ ሁሉ
ቅዱሳን ሁኑ ›› ያለንም ይህንን ሲያስተምረን ነው፡፡
ከመፈጠራችን አስቀድሞ መጠን በሌለው ፍቅር የወደደን
እግዚአብሔር ካለመኖር ወደ መኖር ያመጣን ፤ለውርደት
ሳይሆን ለክብር፤ለርኩሰት ሳይሆን ለቅድስና፤ለሞት ሳይሆን
ለሕይወት ነው፡፡የመፈጠራችንም ዓላማ በፊቱ በፍጹም
ምግባርና ሃማኖት በመመላለስ ከእርሱ ጋር እንድንኖር ነው፡፡
ብርሃን ከጨለማ፡ ጽድቅ ከኃጢአት፡ጋር ኅብረት የለውምና
ከእርሱ ጋር ለዘላለም ነግሰን ለመኖር በቅድስና መኖር
ይጠበቅብናል፡፡ ቅዱስ ጳውሎስም ‹‹ እግዚአብሔር ለቅድስና
እንጂ ለርኩሰት አልጠራንምና ›› ያለንም ለዚህ ነው፡፡/1ተሰ
4*7/ እግዚአብሔር እኛን የፈጠረበትን አላማ ለኤፌሶን
ክርስቲያኖች እንዲህ ገልጾላቸዋል ‹‹ በክርስቶስ ኢየሱስ
ሰማያዊ ሥፍራ በመንፈሳዊ በረከት ሁሉ የባረከን የጌታችን
የኢየሱስ ክርስቶስ አባት እግዚአብሔር ይመስገን፡፡ ብሎ
ካመሰገነ በኋላ ‹‹ ዓለም ሳይፈጠር በፊቱ ቅዱሳን ፡ንጹሐንና
ያለነውር በፍቅር ያደርገን ዘንድ ለእርሱ መረጠን›› ኤፌ 1፡
3-4
አስቀድሞ ስለወደደንና ስላከበረንም ከሌሎች ፍጥረታት
በተለየ
መልኩ የሚያስፈልገንን ሁሉ አዘጋጅቶ በእጆቹ ካበጀን በኋላ
የሥነ ፍጥረት ዘውድ አድርጎ በገነት አኖረን ፡፡( ዘፍ 1፡26
፤መዝ 8፡1)
የቀደመው አዳም አታድርግ የተባለውን በማድረጉ
በንዝህላልነትና በስንፍና በከይሲ ዲያብሎስም ምክር
ተዋረደ፡፡
በሞተ ሥጋ ላይም ሞተ ነፍስ ፤በርዕደተ መቃብር ላይ ርዕደተ
ሲኦል ተፈረደበት፡ በባሕርዩ ሞት ገባበት፡ተዳደፈ፡፡ ክፉ
ፍትወታት የሚያጠቁትና የሚያሸንፉት የዲያብሎስና የኃጢአት
ባርያ ሆነ፡፡ በማይለወጥ ፍቅር የወደደን እግዚአብሔር ግን
ጠፍተን እንድንቀር አልተወንም፡፡ በሰጠን ተስፋ፡በተቆጠረው
ሱባኤና በተነገረው ትንቢት መሰረት ዘመኑ ሲደርስ በተዋህዶ
ሰው ሆነ፤ የተዋረደ ሥጋችንን አከበረ፡፡ በከበረ ደሙ
ዋጀን፤ከኃጢአታችን አጠበን፡፡ በእርሱ ምክንያት
የእግዚአብሔር
ልጆች ተባልን ፡፡ጌታችንና መድኃኒታችን ሰው የሆነውና
ለመዳናችን የሆነውን ዋጋ ሁሉ የከፈለው ለእኛ ያለውን
ፍቅርና
ለኃጢአት ያለውን ጥላቻ ለእኛ ለማሳየት ነው፡፡ ‹‹ ነገር ግን
የኃጢአትን ሥራ ይሽር ዘንድ ከእርሱ ጋር የተሰቀለውን
አሮጌውን ሰውነታችን እንደሆነ ይህን እናውቃለን ››
የተባለውም
ለዚህ ነው፡፡ (ሮሜ 6፡6) እኛን ወደ ቀደመ ክብራችን
ለመመለስ የተከፈለውም ዋጋ ታላቅ ከሆነው የጋብቻ
ምስጢር
ጋር በማያያዝ እንዲህ ገልፆታል ‹‹ ክርስቶስ አካሉ ለሆነችው
ቤተ ክርሰቲያን ራስዋ አዳኝዋም እንደሆነ ወንድ ለሴት ራስዋ
ነውና … ወንዶችም ክርስቶስ ቤተ ክርስቲያንን እንደወደዳት
ራሱንም ስለእርስዋ ቤዛ አድርጎ እንደሰጠላት ሚስቶቻቸውን
ይውደዱ፡፡ በውኃ ጥምቀትና በቃሉ ይቀድሳትና ያነጻት ዘንድ
የነጻችና የተቀደሰች ትሆን ዘንድ እንጂ በላይዋ እድፈት ወይም
ርኩሰት እንዳይገኝባት ቤተ ክስቲያኑን ለእርሱ የከበረች
ያደርጋት ዘንድ…›› ኤፌ 5፡23-28
ስለዚህ ጌታችን በደሙ ኃጢአታችንን እንደ ቸርነቱ ይቅር
ብሎናል፡፡ኤፌ 1፡7 ከእንግዲህ የራሳችን አይደለንም ፡፡
በሰውነታችንም ኃጢአትና ዐመፃን ልናደርግበት አይገባም
፡፡‹‹በዚህ በሚሞት ሥጋችሁ ኃጢአት አታንግሷት፤ለምኞቱ
እሺ
አትበሉት፡፡ ከሙታን ተለይቶ እንደተነሳ ራሳችሁን
ለእግዚአብሔር
መሥዋዕት አድርጉ እንጂ ሰውነታችሁን ለኃጢአት የዐመፅ
የጦር መሣሪያ አታድርጉት፤ ሰውነታችሁንም ለእግዚአብሔር
የጽድቅ የጦር መሣሪያ አድርጉ››ተብለናል፡፡ (ሮሜ6፡
12-13)
የተወደዳችሁ ምዕመናን እግዚአብሔር ደስ ብሎት
የሚቀበለውን ህይወት ለመኖር አንፈልጋለን ፡፡ ለመሆኑ ይህ
ሊሆን የሚችለው እንዴት ብንመላለስ ነው? መልሱን
ሐዋርያው
ቅዱስ ያዕቆብ ‹‹አንደበቱን ሳይገታ ልቡን እያሳተ
እግዚአብሔርን የሚያመልክ የሚመስለው ማንም ቢኖር
የእርሱ
አምልኮቱ ከንቱ ነው፡፡ ንጹሕ የሆነ ነውርም የሌለበት
አምልኮ
በእግዚአብሔር አብ ዘንድ ይህ ነው፤ወላጆች የሌሉአቸውን
ልጆች ባልቴቶችንም በችግራቸው መጠየቅ በዓለምም
ከሚገኝ
ርኩሰት ሰውነትን መጠበቅ ነው፡፡››በማለት ይመልስልናል
( ያዕ
1፡26-27)፡፡ በክርስቶስ ደም የተቀደሰና የእግዚአብሔር
ማደሪያ የሆነውን ሰውነታችንን በዓለም ከሚገኝ ርኩሰት
መጠበቅ የሰማያዊ ርስት ወራሾች ያደርገናል፡፡ በዓለም
የሚገኘውን ርኩሰትም ሐዋርያው ቅዱስ ጳውሎስ ‹‹የሥጋ
ሥራ
›› በማለት ገልጾታል፡፡‹‹እርሱም ዝሙት
፣ርኩሰት፣መዳራት፣ጣዖት ማምለክ፣ሥራይ ማድረግ፣መጣላት፣
ኩራት፣የምንዝር ጌጥ ፣ቅናት፣ቁጣ ፣ጥርጥር፣ፉክክር፣
ምቀኝነት፣ መጋደል፣ ስካር ፣ይህንም የመሰለ ሁሉ
ነው፡፡››እነዚህን የሚያደርጉ ሰዎችም ከመንግስተ
እግዚአብሔር
በአፍአ ወይም በውጭ እንደሚቀሩ ሲያስረዳ‹‹አስቀድሜ
እንደነገርኋችሁ ይህን የሚያደርግ የእግዚአብሔርን መንግስት
አያይም›› ብሏል ( ገላ5፡19)።
በሕይወታችን ሁሉ የምግባርና የሃይማኖት ፍሬ አፍርተን
መገኘት ለቅድስና የጠራንን እግዚአብሔርን ደስ ማሰኘት
ነው፡፡
እነዚህንም ነገሮች ቅዱስ ጳውሎስ ‹‹የመንፈስ ፍሬዎች ››
ብሏቸዋል፡፡ እነርሱም ‹‹ፍቅር፣ደስታ
፣ሰላም፣ትዕግስት፣ምጽዋት ፣ቸርነት ፣እምነት ፣ገርነት ንጽሕና
››ናቸው፡፡ገላ 5፡22 እግዚአብሔር ማደርያው ይሆን ዘንድ
የመረጠውን ሰውነታችንን እርሱ የሚከብርበትን ሥራ
ልናደርግበት ያስፈልጋል፡፡ ‹‹በሕይወት የሚኖሩትም ስለ
እነርሱ
ቤዛ ሆኖ ለሞተውና ለተነሣውም እንጂ ወደ ፊት ለራሳቸው
የሚኖሩ እንዳይሆኑ እርሱ ስለሁሉ ቤዛ ሆኖ ሞተ›› እንደተባለ
በሕይወታችን ሁሉ ፋቃዱን በመመርመርና በመፈጸም
በቅድስና
ልንኖር ይገባናል፡፡2ቆሮ 5፡15
ቅድስናችን በኑሮአችን ሁሉ እንዲሆን ታዘናል (1ጴጥ1፡15)
፡፡
ስለዚህ በተሰማራንበት የሥራ መስክ ፣በማኅበራዊ ኑራአችን
፣በምንበላው ምግብ ፣በምንለብሰው ልብስ ፣በንግግራችንና
በመሳሰለው ሁሉ ለእግዚአብሔር ደስ የሚያሰኘውን
በማድረግ
እግዚአብሔርን በሚሞት ሥጋችን እናክብረው፡፡ ‹‹እኛ ደግሞ
ሸክምን ሁሉ የኃጢአትንም ጭንቀት ከእኛ አስወግደን
በፊታችን
ያለውን ሩጫ በትዕግስት እንሩጥ፡፡ የእምነታችንንም ራስና
ፈጻሚውን ኢየሱስን እንከተለው፤ እርሱ ነውርን ንቆ ፣
በፊቱም
ስላለው ደስታ በመስቀል ታግሦ በእግዚአብሔር ዙፋን ቀኝ
ተቀምጧል ›› ተብሎ እንደተጻፈ ደምን እስከ ማፍሰስ ድረስ
ተጋድሎ አድርገን ከኃጢአት ርቀት በቅድስና እንድንኖር
ይገባናል(ዕብ 12፡1)። ሥጋዊ ምኞታችንንና መሻታችንን
ሰቅለን አሮጌው ሰዋችንን አስወግደን ንስሐ ገብተን ቅዱስ
ሥጋውንና ክቡር ደሙን ተቀብለን በቅድስና እንድናኖር
ረድኤተ
እግዚአብሔር አይለየን፡፡
ወስብሐት ለእግዚአብሔር

Wednesday, February 22, 2017

ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ነኝ:=>+*"+<+>††7ቱ ኪዳናት+*"+<+>††

በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሃዱ አምላክ አሜን
እንኩዋን ለእመቤታችን ቅድስት #ድንግል_ማርያም
ዓመታዊ "የኪዳን በዓል" በሰላም አደረሳችሁ +"+"+
+*" 7ቱ ኪዳናት "*+
=>"ተካየደ" ማለት "ተስማማ : ተማማለ" እንደ ማለት
ሲሆን "ኪዳን" በቁሙ "ውል : ስምምነት" እንደ ማለት
ነው:: ይኸውም እግዚአብሔር ከሰዎች ጋር: ሰዎችም ከሰዎች
ጋር የሚያደርጉት ሊሆን ይችላል:: ልዩነቱ የእግዚአብሔር
ቃል ኪዳን ቅዱስና የማይለወጥ መሆኑ ነው::
+እግዚአብሔር አምላክ ከሥነ ፍጥረት ጀምሮ በየጊዜው
ከብዙ ወዳጆቹ ጋር ኪዳንን አድርጉዋል:: ቅድስት ቤተ
ክርስቲያንም እነዚህን ኪዳናት ጥቅልል አድርጋ 7 እንደ ሆኑ
ታስተምራለች:: ስለዚህም ዛሬ ፈጣሪ ቢረዳን እነዚሁን 7
ኪዳናት በጥቂቱ እንመለከታለን::
"ኪዳነ ተካየድኩ ምስለ ኅሩያንየ"
"ከመረጥኩዋቸው ጋር ቃል ኪዳንን አደረግሁ" (መዝ. 88:3)
1. +*" ኪዳነ አዳም "*+
=>አዳም ማለት የእግዚአብሔር ድንቅ ፍጥረት: የፍጡራን
አስተዳዳሪ: ነቢይ: ካህንና ንጉሥ ነው:: እግዚአብሔር ከአዳም
ጋር አስቀድሞ በእጸ በለስ አማካኝነት ቃል ኪዳን ነበራቸው::
ነገር ግን አባታችን በዲያብሎስ ሴራ በመረታቱ ኪዳኑ ፈረሰ::
(ዘፍ. 3:1)
+አዳምና ሔዋን ተጸጽተው ቢያለቅሱ ግን አዲስ የኪዳን
ተስፋ: "ከልጅ ልጅህ ተወልጄ አድንሃለሁ" የሚል ኪዳንን
ተቀበሉ:: (ቀሌምንጦስ: ገላ. 4:4)
2. +*" ኪዳነ ኖኅ "*+
=>ከአዳም እስከ ኖኅ ድረስ ባሉት 10 ትውልድ ዓለም
በዓመፃ ተሞላች:: ቅዱስ ኖኅ በደግነቱ መርከብ ሠርቶ
ቤተሰቡን ሲያተርፍ ዓለም በማየ ሥራዌ ጠፋች:: ከመርከቡ
ከወጣ በሁዋላ ኖኅና እግዚአብሔር በቀስተ ደመና ምልክትነት
ቃል ኪዳን ተጋቡ:: "ኢያማስና ለምድር ዳግመ በማየ አይኅ"
እንዲል:: (ዘፍ. 9:12)
3. +*" ኪዳነ መልከ ጼዴቅ "*+
=>መልከ ጼዴቅ የእግዚአብሔር ካህኑ: የክርስቶስም
ምሳሌው የሆነ የሳሌም ንጉሥ ነው:: በ15 ዓመቱ መንኖ:
አጽመ አዳምን ይዞ: በቀራንዮ በሕብስትና በወይን ያስታኩት
ነበር::
+እግዚአብሔር ለመልከ ጼዴቅ: በሐዲስ ኪዳን ለምትሠራው
ክህነትና ምሥጢረ ቁርባን ምሳሌ አድርጐ በቃል ኪዳን
አትሞታል:: በዚህም ተሰውሮ ይኖራል እንጂ ሞትን እስካሁን
አልቀመሰም:: ይህም ካህኑ መልከ ጼዴቅ ከአብርሃም ጋር
በተገናኙበት ጊዜ ተገልጧል:: (ዘፍ. 14:17, ዕብ. 7:1)
4. +*" ኪዳነ አብርሃም "*+
=>ቅዱስ አብርሃም የሕዝብና የአሕዛብ አባት: ሥርወ
ሃይማኖት: የጽድቅም አበጋዝ ነው:: ስለ ፍቅረ እግዚአብሔር
ሲል ከርስቱና ከወገኖቹ ተለይቶ በቅድስና ኑሯልና
እግዚአብሔር "በዘርሕ አሕዛብ ይባረካሉ" አለው:: (ዘፍ.
12:1) የቃል ኪዳን ምልክትም ይሆነው ዘንድ ግዝረትን
ሰጠው:: (ዘፍ. 17:1-14)
5. +*" ኪዳነ ሙሴ "*+
=>ቅዱስ ሙሴ የነቢያት አለቃ: የእሥራኤል እረኛ:
የእግዚአብሔር ሰው እና ፍጹም ትሑት (የዋህ) ሰው ነው::
በፈጣሪው ትዕዛዝ እሥራኤልን ከግብጽ ባርነት አውጥቶ ለ40
ዘመናት በበርሃ ሲመራቸው ከእግዚአብሔር የኪዳንን ጽላትና
አሠርቱን ትዕዛዛት ተቀብሏል:: (ዘጸ. 20:1, 31:18)
6. +*" ኪዳነ ዳዊት "*+
=>ቅዱስ ዳዊት ሥርወ ነገሥት: ጻድቅ: የዋህና ቡሩክ የሆነ
አባት ነው:: እግዚአብሔር ከእረኝነት ጠርቶ ንጉሥ አድርጐ
ሹሞት "ከሆድህ ፍሬ በዙፋንህ ላይ አኖራለሁ" (መዝ.
131:11) ሲል ምሎለታል:: አክሎም ሰፊ ቃል ኪዳን ሰጥቶ
"አልዋሽህም" ብሎ ሲምልለት እንመለከታለን:: (መዝ.
88:35)
7. +*"+ ኪዳነ ምሕረት +"*+
=>በብሉይ ኪዳን የነበሩ 6ቱ ኪዳናት በዘመናቸው ክቡርና
ሕዝቡን ከመቅሰፍት ይታደጉ የነበሩ ቢሆንም ከሲዖል ማዳን
ግን አልቻሉም:: ስለዚህም አንድ ፍጹም ኪዳን ያስፈልግ
ነበር:: ይህን ፍጹም ኪዳን ይፈጽም ዘንድም ከቅድስት ሥላሴ
አንዱ ወልድ ከሰማያት ወርዶ በድንግል ማርያም ማሕጸን
አደረ::
+በፍጹም ተዋሕዶም በሕቱም ድንግልና ተወልዶ: አድጎ:
ተጠምቆ: አስተምሮ: ሙቶ: ተነስቶና ዐርጐ ሥጋ ማርያምን
በዘባነ ኪሩብ አስቀመጠው:: ኪዳነ ምሕረት (የምሕረት
ኪዳን) የምንለው አንዱ ታዲያ ይሔው ነው::
+የጌታችን መጸነሱ: መወለዱ: መሰደዱ: መጠመቁ:
ማስተማሩ: ሥጋውንና ደሙን መስጠቱ: መሰቀሉ: መሞቱና
መነሳቱ: ማረጉና መንፈስ ቅዱስን መላኩ በአንድ ላይ "ኪዳነ
ምሕረት" ይባላል:: ታዲያ ይህ ሁሉ የተደረገው በሥጋ
ማርያም ነውና የኪዳኑ ባለቤት እመቤታችን ቅድስት ድንግል
ማርያም ናት::
+የእርሷ ኪዳን የ6ቱን አበው ኪዳናት ፍጹም በማድረጉ
የኪዳናት ማሕተም ይባላል:: የድንግል ማርያም ኪዳኗ
ከሲዖልና ከገሃነም ሊታደገን አቅሙ አለውና:: መድኃኒታችን
ክርስቶስ ለድንግል እናቱ ቃል ኪዳኑን ያጸናላት ደግሞ ካረገ
ከዓመታት በሁዋላ ጐልጐታ ላይ ነው::
+እመ ብርሃን በዚያ ቁማ ስለ ኃጥአን ስታለቅስ "እናቴ ሆይ!
በስምሽ ያመነውን: በቃል ኪዳንሽ የተማጸነውን
እምርልሻለሁ" ብሎ ደስ አሰኝቷታልና:: ይሔው በእመ ብርሃን
ምልጃና ቃል ኪዳን ምዕመናን ከመቅሰፍትና ከገሃነመ እሳት
ማምለጥ ከጀመሩ 2ሺ ዓመታት ሆኑ:: ዛሬም እኛ ኃጥአን
ልጆቿ ከእሳት እንደምታድነን አምነን በጥላዋ ሥር
እንኖራለን::
+*" ኢትዝክሪ ብነ አበሳነ (ኃጢአተነ : ወጌጋየነ)
ማርያም እሙ ለእግዚእነ:
በኪዳንኪ: ወበስደትኪ ድንግል ተማሕጸነ:: "*+
"ድንግል ሆይ! ኃጢአታችን: አበሳችንና በደላችንን አታስቢብን
ዘንድ በስደትሽና በኪዳንሽ ተማጽነናል::"
=>የአርያም ንግሥት: የሰማያውያንና ምድራውያን ኁሉ
እመቤት: የአምላክ እናት: ቅድስት: ስብሕት: ክብርት:
ልዕልት: ቡርክት: ፍስሕትና ጥዕምት የሆነች ድንግል ማርያም
የድኅነታችን መሠረት: ላመኑባት አንገት የማታስደፋ እውነተኛ
አማላጅ ናት::
+በዚህች ዕለት የካቲት 16 ስለ ወገኖቿ የሰው ልጆች ፍቅር
በእንባ ያቀረበችውን ልመና የባሕርይ አምላክ የሆነ ልጁዋ
ተቀብሎ በማይዋሽ ንጹሕ አንደበቱ ቃል ኪዳን ገብቶላታል::
በስምሽ ያመነ በቃል ኪዳንሽ የተማመነ እሳትን አያይም
ብሏታል::
=>ቸሩ ልጇ ከበረከተ ኪዳኗ አይለየን:: በዓሉንም የሰላም :
የፍቅርና የበረከት ያድርግልን::
=>የካቲት 16 ቀን የሚከበሩ ዓመታዊ የቅዱሳን በዓላት=
1.ኪዳነ ምሕረት (የሰባቱ ኪዳናት ማሕተም)
2.ቅድስት ኤልሳቤጥ (የመጥምቁ ዮሐንስ እናት /
የእመቤታችን አክስት / የሶፍያ ልጅ)
3.ቅዱስ ገብረ ማርያም ጻድቅ ንጉሠ ኢትዮዽያ (የቅ/ላሊበላ
ወንድም)
=>ወርኀዊ በዓላት
1.ቅዱስ አኖሬዎስ ንጉሥ ጻድቅ
2.አባ አቡናፍር ገዳማዊ
3.አባ ዮሐንስ ወንጌሉ ዘወርቅ
4.አባ ዳንኤል ጻድቅ
=>+"+"+ . . . ኤልሳቤጥም የማርያምን ሰላምታ በሰማች
ጊዜ ፅንሱ በማኅፀንዋ ውስጥ ዘለለ:: በኤልሳቤጥም መንፈስ
ቅዱስ ሞላባት:: በታላቅ ድምፅም ጮኻ እንዲህ አለች:-
አንቺ ከሴቶች መካከል የተባረክሽ ነሽ: የማኅፀንሽም ፍሬ
የተባረከ ነው:: የጌታዬ እናት ወደ እኔ ትመጣ ዘንድ እንዴት
ይሆንልኛል? እነሆ የሰላምታሽ ድምፅ በጀሮየ በመጣ ጊዜ
ፅንሱ በማኅፀኔ በደስታ ዘሎአልና:: ከጌታ የተነገረላት ቃል
ይፈፀማልና ያመነች ብፅዕት ናት:: +"+"+ (ሉቃ. 1:39)
<ወስብሐት ለእግዚአብሔር>

ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ነኝ:=>+*"+<+>†† የእመ ቤታችን የቅድስት ኪዳነ ምህረት የንግስ በዓል ††

""የእመ ቤታችን የቅድስት ኪዳነ ምህረት የንግስ
በዓል"!!!
ኪዳነ ምህረት ማለት የምህረት መሐላ ማለት ነው፡፡
ከ" 33"በዓላተ እግዝእትነ ድንግል ማርያም አንዱ ነው፡፡
እመቤታችንም ከጌታችን መቃብር እየሄደች በምትለምንበት
ጊዜ አይሁድ ለምቀኝነት አያርፉምና ምን ልታመጣብን ነው
በማለት ሊጣሏት ሲመጡ ጌታችንም ከዓይናቸው ሰውሯታል
አይሁድም ጠባቂ ቢያቆሙ እመቤታችን ዕለት ዕለት መሄዷን
አላቋረጠችን እመቤታችንም እንዲህ ብላ ስትጸልይ ልጄ
ወዳጄ ሆይ ከስጋዬ ስጋ ከነፍሴ ነፍስ ነስተህ ሰው በመሆንህ
ዘጠኝ ወር ከ5 ቀን በቻለችህ ማሕጸኔ ከአንተ ጋር ሀገር
ለሀገር ስለ መሰደዴ መትተህ ልምናዬን ትሰማኝ ዘንድ
እለምንሃለሁ አለች በዚህ ጊዜ ንውጽውጽውታ ሆነ መቃብራት
ተሰነጣጠቀ ጌታችንም እልፍ ከእልፍ መላዕክቱ ጋር መጥቶ
ሰላም ለኪ ማርያም ምን እንዳደርግልሽ ትለሚኚኛለሽ
አላት፡፡ እርሷም መታሰቢያዬን ያደረገውን ስለ ስሜ ለችግረኛ
የሚራራውን በስሜ ቤተ ክርስቲያን ያነጻውን መባዕ
የሰጠውን ከሃይማኖት ከፍቅር ጽናት ልጁን በስሜ የጠራውን
ሁሉ ማርልኝ ከሞተ ስጋ ከሞተ ነፍስ አድንልኝ አለችው፡፡
ጌታችንም ይህን ሁለ እንዳደርግልሽ መሐልኩ ለኪ በርእስየ
ወበአቡየ ሕያው ወበመንፈስ ቅዱስ ብሎ ቃል ገብቶላት
አርጓል፡፡
ሌላው በላዔ ሰብ በአማርኛ ሰው በላ ማለት ነው፤ ትክክለኛ
ስሙ ግን ስምዖን ይባላል ቅምር በሚባል አገር የሚኖር
እጅግ ባለጸጋ ነበር፤ እንደ አብርሃም እንግዶችን እየተቀበለ
ድሆችን እየመገበ የሚኖር ጻድቅ ነበር፤ ሰይጣን በዚህ ስራው
ቀናበት ሊፈትነውም በሦስት አረጋዊ ሽማግሌዎች ስላሴ ነን
ብሎ ተገለጠለት ልክ እንደ አብርሃም፤ ሐዋርያው ጳውሎስ
ሰይጣን የብርሃን መልአክ መስሎ ይመጣል እንዳለ፤ እርሱም
ሥላሴ መስለውት ተቀበላቸው ተንከባከባቸውም፤ ምግብ
አቀረበላቸው ምግብ አንበላም የምንጠይቅህን ግን
ትፈጽምልን ዘንድ ቃል ግባልን አሉት ቃል ገባላቸው
እንግዲያውስ የምትወደን ከሆነ አንድያ ልጅህን ሰዋልን
አሉት፤ መጀመሪያ ደነገጠ ኃላ አብርሃም ልጁን ሊሰዋ
አልነበረምን እኔንም ሊፈትኑኝ ይሆናል ብሎ ለማረድ
ተዘጋጀ፤ተው የሚለው ድምጽ አልሰማም፤ አረደው
አወራረደው ይዞላቸው ቀረበ፤ መጀመሪያ ቅመስልን አሉት
ቀመሰው ወዲያው እነዚያ ሰዎች ተሰወሩበት እርሱም
አህምሮውን ሳተ ተቅበዘበዘ ከዚያ በኃላ ምግብ አላሰኘውም
የሰው ስጋ እንጂ መጀመሪያ ቤተሰቦቹን በላ ከዚያም ጓደኞቹን
ጦርና የውኃ መንቀል ይዞ ከቤቱ ወጣ ያገኘውን ሰው እየገደለ
ይበላል የበላቸው ሰው ቁጥር 78 ደረሰ፤ በመንገድ ተቀምጦ
የሚለምን በደዌ የተመታ አንድ ደሃ አገኘ ሊበላው ወደ እርሱ
ተጠጋ ግን ቁስሉን አይቶ ተጸየፈው፤ ደሃውም “ስለ
እግዚያብሔር ከያዝከው ውኃ አጠጣኝ” አለው “ዝም በል
ደሃ” ብሎት አለፈ፤ “ኸረ በውኃ ጥም ልሞት ነው ስለ ጻድቃን
ስለ ቅዱሳን” አለው አሁንም ዝም ብሎት ሄደ ለሦስተኛ ጊዜ
“ስለ አዛኝቷ ስለ እምዬ ማርያም” አለው፤ ሰውነቱን አንዳች
ነገር ወረረው “አሁን የጠራከውን ስም እስኪ ድገመው ስለ
ማን አልከኝ” አለው፤ ስለ አዛኝቷ ስለ እመቤቴ ማርያም
አለው፤ ይህቺስ ደግ እንደሆነች በምልጃዋም ከሲኦል
እንደምታወጣ ህጻን እያለው እናትና አባቴ ይነግሩኝ ነበር፤ በል
እንካ አለው እጁን ዘረጋለት ጥርኝ ውኃ ጠብ አደረገለት ወደ
ጉሮሮው አልወረደም የተሰነጠቀ እጁ ውስጥ ገባ እንጂ፤ በለዔ
ሰብ ከዚያች ደቂቃ በኃላ አዕምሮው ተመለሰለት እንዲህም
አለ “በአንድ ዋሻ ውስጥ ገብቼ ስለ ኃጢያቴ አለቅሳለሁ ስጋዬ
ከአጥንቴ እስኪጣበቅ እጾማለሁ ወዮሊኝ ወዮታም አለቢኝ
አለ፤ ወደ ዋሻ ገባ ምግብ ሳይበላ ውኃም ሳይጠጣ 21 ቀን
ኖሮ በርሃብ ሞተ ይላል ተአምረ ማርያም። ጨለማ የለበሱ
ሰይጣናት እያስፈራሩ እያስደነገጡ ነፍሱን ወደ ሲኦል ሊወስዷት
መጡ፤ እመቤታችን ፈጥና በመካከላቸው ተገኘች፤ ልጄ ወዳጄ
ይህችን ነፍስ ማርሊኝ አለችው እናቴ ሆይ 78 ነፍሳትን የበላ
እንዴት ይማራል አላት፤ የካቲት 16 ቀን በጎለጎታ የገባህልኝ
ቃል ኪዳን አስብ ስምሽን የጠራ መታሰቢያሽን ያደረገን
እምርልሻለው ብለኸኝ የለምን አለችው፤ እርሱም እስኪ
ይህቺን ነፍስ በሚዛን አስቀምጧት አለ ቢያስቀምጧት ጥርኝ
ውኃው መዝኖ ተገኘ፤ ስላቺ ስል ምሬታለው ሰባት ቀን
ሲኦልን አስጎብኝታችሁ ወደ ገነት አግቧት አላቸው። ቦታሽ
እዚህ ነበር እያሉ ሲኦልን አስጎብኝተው ወደ ገነት አገቧት።
ልመናዋ ክብሯ የልጇም ቸርነት ከሁላችን ጋር ይሁን።
ተአምረ ማርያም
ድንግል ማርያም በቃል ኪዳኗ አትለየን

Monday, February 20, 2017

ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ነኝ: =>+*"+<+>†† ዘወረደ /ዘመነ አዳም/- ††

ዘወረደ /ዘመነ አዳም/
የዐቢይ ጾም የመጀመሪያ ሳምንት ዘወረደ: ሙሴኒ:ሕርቃል
ይባላል፡፡ ዘወረደ ማለት፣ ከላይ የመጣ፣ የወረደ ማለት ነው፡፡
ይህም የአምላካችን ሰው መሆን ያመለክታል፡፡ ከሰማይ
ከወረደው በቀር ወደሰማይ የወጣ የለም ካለው ከጌታችን
ከመድኃኒታችን ከኢየሱስ ክርስቶስ ቃል በመነሳት ሊቁ ቅዱስ
ያሬድ በዚህ ዕለት ምስባክ “ዘወረደ እምላዕሉ አይሁድ ሰቀሉ
ወሚመ ኢያእመሩ እግዚአ ኩሉ ዘየሐዩ በቃሉ” በማለት
በጾመ ድጓው መጀመሪያ ላይ ገልጾት ይገኛል፡፡
አዳምን ለማዳን ከሰማይ የወረደውን አይሁድ ሰቀሉት፣
የሰማይን ሥልጣን ያለው የሁሉ ጌታ እንደሆነም ምንም
አላወቁም ብሎ ተናግሮ ነበር፡፡ ይህም ድርሰት በቤተ
ክርስቲያናችን የጾም መጀመሪያ የሆነው ዕለተ ሰንበት
ዋዜማ፣ መግቢያ፣ /መሐትው/ ሆኖ ከዋዜማ በፊት
ምንጊዜም በየዓመቱ ይቆማል፡፡ ይዘመራል፡፡ ይመሰገናል
ማለት ነው፡፡
ስለዚህ የሳምንቱ ስያሜ ከዚህ የተወሰደ ነው፡፡ እንዲሁም
ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ የማዳን ሥራውን
የጀመረው፤ ከሰማየ ሰማያት ወርዶ ሰው በመሆን ፣
በዮርዳኖስ ተጠምቆ በማስተማር እንደሆነ ሁሉ የመጀሪያው
ሳምንት ዘወረደ ይባላል፡፡
በዚህ ሳምንት በተለይም እሑድና ሰኞ የሚነገሩት ውዳሴያት
ከመጻሕፍተ ኦሪትና ነቢያት የተወሰዱ ናቸው፡፡ ሁለተኛም
ሙሴኒ በመባል ይታወቃል፡፡ እግዚአብሔር አምላክ አዳምን
ለማዳን ከሰማይ መውረዱንና በመስቀል መሰቀሉን
ስለሚያወሳ ነው፡፡
በተጨማሪም ይህ የመጀመሪያው ሳምንት ጾመ ሕርቃል
ይባላል፡፡ በ714 ዓ.ም.ሕርቃል /ኤራቅሊየስ/ የቤዛንታይን
ንጉሥ ነበረ፡፡ይህ ሳምንት በስሙ የተጠራበት ምክንያት
በዘመኑ ፋርሶች ኢየሩሳሌምን ወርረው የጌታችን መስቀል
ማርከው ወስደው ነበር፡፡ እርሱ ወደፋርስ ዘመቶ መስቀሉን
ከእነርሱ ነጥቆ ይዞ ወደ ኢየሩሳሌም ተመልሷል፡፡
ሕርቃል ከፋርሶች ጋር ከመዋጋቱ በፊት ሐዋርያት
በሲኖዶሳቸው ነፍስ የገደለ ሰው እስከ እድሜ ልኩ ይጹም
ብለው ሥርዓት ሠርተዋልና ጾሙን ፈርቶ ስለነበር
በኢየሩሳሌም የነበሩ ምእመናን አሳቡን ደግፈው “አንተ
ጠላታችንን አጥፋልን ፣መስቀሉን አስመልስልን እንጂ የአንድ
ሰው እድሜ ቢበዛ ሰባ ሰማንያ ነው ፡፡ጾሙንአምስት አምስት
ቀን ተከፋፍለን እኛ ተከፋፍለን እንጾምልሃለን፡፡”ብለው
ጾመውለታል፡፡
ይህንን መሠረት በማድረግ ያላወቁት አንድ ጊዜ ጾመው
ትተውታል፡፡ ያወቁት ግን ቀድሞም ሐዋርያት ጾመውታል
ብለው ሥርዓት አድርገው በዓመት በዐቢይ ጾም መጀመሪያ
ላይ ጾመ ሕርቃል እያሉ የሚጾሙት ሆነዋል፡፡ስለዚህ
ቤተክርስቲያናችን ይህንን መሠረት በማድረግ በጌታችን
ከመድኀኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ጾም የመጀመሪያውን
ሳምንት ጾመ ሕርቃል በሚል ስያሜ ሰማይ እንዲጾም
አድርጋለች፡፡ /መጋቢት 10 ስንክሳር ይመልከቱ፡፡/
የቤተ ክርስቲያናችን ታሉቁ ሊቅ ቅዱስ ያሬድ፣ በዘወረደ ጾመ
ድጓው ሰንበት ለሰው ልጆች ብቻ ሳይሆን፣ ሕይወት ላለው
ነገር ሁሉ ጸጥታና ሰላም የሰፈነባት የዕረፍት ቀን ስለመሆኗ
“አዘዞ እግዚአብሔር ለሙሴ ወይቤሎ ሰብዕከ ወላህምከ
ወኲሉ ቤትከ ያዕርፍ በሰንበት” ዘፀ.20፥10፣23፣12፣ ጾመ
ድጓ፣ እግዚአብሔር ሙሴን ሕዝብህ የከብትህ መንጋህ
ቤተሰብህ ሀሉ በሰንበት ቀን ከድካማቸው ይረፉ በማለት
አዘዘው ይላል፡፡ በዚህም ዘመነ ጾም፣ ወይም ጾመ ሙሴ
ይባላል፡፡
በጾመ ድጓው ዘወረደ እየተባለ የሚታወቀው፣ በጾመ አርባው
ወቅት በተለይም በመጀመሪያው ሳምንት የሚገኘው ያሬዳዊ
ድርሰት በነግህ በሠለስት፣ በቀትርና በሠርክ እንዲሁም
ቅዳሜና እዡድ በሌሊት የሚዘመር ነው፡፡ በውስጡም
የያዘው ፍሬ አሳብ፣ የጾምን፣ የጸሎትን፣ የምጽዋትንና
የፍቅርን ጠቃሚነት አጉልቶ የሚያስተምር ነው፡፡
በዚህ በጾም ወቅት በቤተ ክርስቲያናችን ሥርዓት በአብዛኛው
ከቅዱስ ያሬድ ድርሰቶች ውስጥ የሚዘመረው ምዕራፍ
የተባለው ነው፡፡ ምዕራፍ የተባለበት ምክንያትም
በየመዝሙራቱ መሀል ሃሌታና ድጓ እያስገባ ለመዝሙሩ
ማረፊያ ስላበጀለት በዚህ ምክንያት ምዕራፍ የሚል ስያሜ
ሊያገኝ ችሏል፡፡ ይህ የዜማ መጽሐፍ በሁለት ታላላቅ ክፍሎች
ይከፈላል፡፡ ይኸውም የዘወትር ምዕራፍና የጾም ምዕራፍ
በመባል ይታወቃል፡፡የዘውትር ምዕራፍ የሚባለው በዓመቱ
ውስጥ ባሉት ቀናት ውስጥ ሳምንታትና በዓላት ሁልጊዜ
በአገልግሎት ላይ የሚውል ሲሆን፣ የጾም ምዕራፍ የሚባለው
ደግሞ በጾመ አርባ ብቻ ለአገልግሎት የሚውል ነው፡፡
ከዚህም በተጨማሪ በዐሥሩ ምህላት አርዕስተ ምህላ በዚሁ
ክፍል ይካተታል፡፡ የምዕራፍ ቅንብር ከመዝሙረ ዳዊት፣
ከድጓና ከጾመ ድጓ ጋር የተቀናጀ ነው፡፡ የትምህርት
አሰጣጡም እንደ ድጓው ወይም እንደ ዝማሬ መዋሥዕቱ
መጽሐፍ ተዘርግቶ ሳይሆን በቃል የሚጠናና የሚወሰን ነው፡፡
ስለሆነም ምዕራፍን ለመማር 150 መዝሙረ ዳዊትን፣
ከነቢያት 15 ምዕራፎችንና 5 መኃልያተ ሰሎሞንን በቃል
ሸምድዶ መያዝ ይጠበቅበታል፡፡ ወይም ግድ ነው፡፡
ጾምን መጾም የፈቃድ ብቻ ሳይሆን የትእዛዝም ነው፡፡
በዘመነ ብሉይ ነቢዩ ኢዩኤል “ቀድሱ ጾመ ወስብኩ ምህላ”
ጾምን ያዙ አጽኑ ምሕላንም ዐውጁ ሸማግሌዎቹን
ከፈጣሪያችን ቤት ሰብስባችሁ በአንድነት ሁናችሁ ወደ
እግዚአብሔር ጩሁ /ለምኑ/ ብሏል፡፡ ኢዮ.ምዕ.1፥11፣
2፣12፣15-16 ሐዋርያው ቅዱስ ጳውሎስም ወኲኑ ላዕካነ፣
ለእግዚአብሔር በጾም ወበንጽሕ፡፡ በጾም፣ በንጽሐና
ተወስናችሁ እግዚአብሔርን አገልግሉ ብሏል 2ቆሮ.6፥4-6፡፡
ጾም ከሌለ ወይም ተገቢ ካልሆነ ጌታችን በምትጾሙበት ጊዜ
እንደ ግብዞች አትሁኑ ስለ ጽድቅ የሚራቡ የሚጠሙ ንዑዳን
ክብራን ናቸው ለምን አለ? ማቴ.5፥፣6፣16፡፡ ነቢዩ ዳዊትም
ሰውነቴን በጾም አሳመምኳት በቀጠና፣ በሰልት አደከምኳት
ለምን አለ መዝ.34፥68፣ ት.ዳን. 9፥3-4፣ 14፥5
ነብዩ ሚኪያስ ሐዋርያት ሙሸራውን ከነሱ ለይተው
የሚወስዱበት ጊዜ ይመጣል ያን ጊዜ ይጾማሉ ያለውን የጌታን
ቃል መሠረት በማድረግ ክርስቶስ በሞት ከተለያቸው በኋላ
ጾመዋል፡፡ ጾምንም ሠርተዋል የሐዋ.ሥራ 13፥3፡፡ ሠለስቱ
ምዕትም ሐዋርያት የጾሙትንና እንዲጾም የወሰኑትን መጾም
ይገባል ብለው ቤተ ክርስቲያን የተቀበለቻቸውን አጽዋማት
እንዲጾሙ መወሰናቸው ይህን የጌታ ቃል መሠረት በማድረግ
ስለሆነ፣ የትእዛዝ መሆኑን ተገንዝበን መጾም አለብን፡፡
ጌታችን መድኀኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስም ሠራዔ ሕግ
እንደመሆኑ አርባ ቀን አርቦ ሌሊት ጾመ እንጂ እርሱ ሳይጾም
ጾሙ አላለንም ማቴ.4፥2፡፡ ጾመን ለማበርከት ያብቃን፡፡
አሜን!

ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ነኝ: =>+*"+<+>†† የዐቢይ ጾም የመጀመሪያው ሳምንት ዘወረደ ††

. ዘወረደ ወይም ሕርቃል ወይምሙሴኒ
✔ የዐቢይ ጾም የመጀመሪያው ሳምንት ዘወረደ ይባላል፡፡
‹‹ዘወረደ እምላዕሉ አይሁድ ሰቀሉ›› የሚልና ይህንን
የመሳሰለ ጌታ እኛን ለማዳንና ፍቅሩን ሊገልጽልን ከሰማያት
መውረዱን ከድንግል ማርያም የእኛን ሥጋ መዋሐዱን
የሚያዘክር ምስጋና የሚቀርብበት ሳምንት ነው፡፡
✔ ሌላም ስም አለው ጾመ ሕርቃል ይባላል፡፡ ይህ ጾም
የጾም መግቢያ የመጀመሪያ ሳምንት የምንጾመው ጾም
ሲሆን ሕርቃል የሚል ስያሜ ተሰጥቶታል፡፡
✔ ሕርቃል ማን ነው? ለምንስ በስሙ ተሰየመ? በ614
ዓ.ም ኪርዮስ የተባለ የፋርስ ንጉሥ ኢየሩሳሌምን በመውረር
ጥቃት አደረሰ፡፡
✔ በዚህ ወቅት በኢየሩሳሌም ንግሥት ዕሌኒ በሠራችው
ቤተመቅደስ ውስጥ ሲገባ ንግሥቷ በክብር አስቀምጣው
የነበረው የጌታችን የመድኃኒታችን የኢየሱስ ክርስቶስ መስቀል
እንደ ፀሐይ ሲያበራ አገኘው፡፡
✔ ቢነካው አቃጠለው ዲያቆናቱን አሸክሞ ሌላውን ንዋየ
ቅድሳት ዘርፎ 60ሺ የሚደርሱትን አቁስሎ ገድሎ 3ሺ
የሚሆኑትን ማርኮ ከተማዋንም አቃጥሎ ወደ ፋርስ ባቢሎን
ይመለሳል፡፡
✔ በዚህ ጊዜ ከጦርነቱ ያመለጡ በየዋሻው በየጉራንጉሩ
ገብተው የተሸሸጉ ተሰብስበው ከ14 ዓመት በኋላ በ628
ጩኸታቸውንና የደረሰባቸውን በደል ለክርስቲየኑ የሮም
ንጉሥ ሕርቃል ይነግሩታል፡፡
✔ እርሱም ሐዋርያት ሰውን የገደለ እድሜውን በሙሉ
ይጹም ስላሉ እንዴት ላድርገው አላቸው እኛ የአንተን እድሜ
ተከፋፍለን እንጾማለን ብለው አንድ አንድ ሳምንት ደርሷቸው
ጾሙን በሚገባ ጾመውታል፡፡
✔ የጌታችን የኢየሱስ ክርስቶስ መስቀልና የተማረኩ
ክርስቲያኖችን ለመመለስ ሕርቃል ጦር መዝዞ በኪርዮስ ላይ
ተነሳበት ድል ለሕርቃል ሆነና መስቀሉን ያለበትን አጥቶ
ሲቸገር መስቀሉን ሲቀብርና ዲያቆናቱን ሲያስገድል በመስኮት
ሆና ያየችው ከኢየሩሳሌም የተማረከች አንዲት ብላቴና
አሳይታው አውጥቶ በልብሰ መንግሥቱ ጠቅልሎ ወደ
ቁስጥንጥንያ ተመለሰ፡፡
✔ የተማረኩት በሙሉ ነጻ ወጡ ይህን ለማሰብ ለማስታወስ
በተጨማሪ በኃጢአት ላይ ድል እንድናገኝ መንፈሳዊ ጦር
በውስጣችን እንዲበዛልን መስቀልህ ከምርኮ እንደተመለሰ
እኛንም ከኃጢአት ምርኮ መልሰን ለሕርቃል ድል መንሳትንና
በጠላቶቹ ላይ ኃይልን እንደሰጠኸው ለእኛም በኃጢአት ላይ
ድል መንሳት መንፈሳዊ ኃይልን ስጠን እያልን እንጾመዋለን፡፡
✔ በጌታ ጾም ላይ እንዲጾም የሆነበት ምክንያት ጾሙ
የጌታ ጾም በሚጾምበት ወቅት ላይ ስለተጾመ
ቤተክርስቲያናችን አብራ ደንግጋዋለች፡፡
✔ እዚህ ላይ በዚያን ጊዜ ለሕርቃል ሕዝቡ ሱባኤ
ይዞለታል፡፡ ዛሬም እኛ ለቤተክርስቲያን ያደረግነውን በማሰብ
እግዚአብሔር አምላክ ለሕርቃል የሰጠውን በጠላቶቹ ላይ
ድል መንሳትን ለእኛም እንዲሰጠን የምንጠይቅበት ስለሆነ
የመጀመሪያውን ሳምንት በሕርቃል ሰይመን ጾሙን
እንጾማለን፡፡
✔ የእኛ ጠላት የጨለማ ገዥ የሆነው ዲያቢሎስ ነውና
እሱን ደግሞ በጾም እንደምናሸንፈው ጌታችን መድኃኒታችን
ኢየሱስ ክርስቶስ አስተምሮናል፡፡
✔ «ዘወረደ» ማለትም በቀጥታ፣ ቃል በቃል ሲተረጐም
«የወረደ» ማለት ነው፡፡ ይህም በምስጢሩ አምላክ ወልደ
አምላክ ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ለቤዛ ዓለም በቅዱስ ፈቃዱ
ሰው ሆኖ ከሰማየ ሰማያት = ከባሕርይ ልዕልናው በትሕትና
ወርዶ ከቅድስት ድንግል ማርያም መወለዱን የሚያመላክት፣
ይህም የሚታወስበት፣ የሚወሳበት የዐቢይ ጾም አንደኛው
ሳምንት ነው፡፡ 《ዮሐ.3-13》፡፡
✔ ሳምንቱ ሙሴኒ የተባለበትም ምክንያት በዚሁ ሳምንት
መጀመሪያ የሰኞ ዕዝል «ከመዝ ይቤ ሙሴ ፀዓቱ
እምትእይንት» «ሙሴ ከከተማ መውጣቱ እንደዚህ ነው አለ»
ስለሚል እንደዚሁም የዚሁ ዕለት ማለት የሰኞ አቡን «ሙሴኒ
ይቤ በውስተ ኦሪት ምድር ሰናይት» እያለ የሙሴን ታሪክ
ስለሚያጠቃቅስ ሳምንቱ ሙሴኒ ተባለ፡፡
✔ ነቢያትም አርባ አርባ ቀን ጾመው ከአለፉ በኋላ የሙሴ
ሕግና ትንቢተ ነቢያት ፈጻሚ የሆነው ምላካችን እንደ እነሱ
40 ቀንና 40 ሌሊት መጾሙን የሚያስታውስ ነው፡፡
《ዘፀ.24-18》፤ 《1ኛ.ነገ.19-8》፤ 《ማቴ. 4-1-4》፡፡
↪ ወስብሐት ለእግዚአብሔር
↪ ምንጭ፡- ጾምና ምጽዋት