#ሰባት_ቁጥር_ምስጢራት
በመጽሐፍ ቅዱስና በስርዓተ ቤተ-ክርስቲያን አስተምህሮ ስባት
ቁጥር ብዙ ምሳሌ እንዳለው ይታወቃል፡፡ በዕብራዊያን
ዘንድም
ሰባት ፍጹም ቁጥር ነው፡፡ ምሳሌ 24፡16 እግዚአብሔር
ከሰኞ
እስከ እሑድ ያሉትን ቀናት በሰባት ቁጥሮች ወስኗል ሕዝበ
እስራኤል ከግብጽ ባርነት ወጥተው በሲና በርሀ ሲጓዙ ይመሩት
የነበሩት በ7 ደመና እንደነበረ ይታወቃል፡፡ ዘዳ 13፡21 ከዚህ
ቀጥለንም ለቤተ-ክርስቲያን አስተምህሮ የ7 ቁጥር
ምስጢራትን
ምሉዕነትን የሚያስረዱ ልዩ ልዩ ማስረጃዎችን በዝርዝር
እንመለከታለን፡፤
ሀ/ ሰባቱ አባቶች
1. ሰማያዊ አባታችን እግዚአብሔር
2. የነፍስ አባት
3. ወላጅ አባት
4. የክርስትና አባት
5. የጡት አባት
6. የቆብ አባት
7. የቀለም አባት
ለ ሰባቱ ዲያቆናት
1. ቅዱስ እስጢፋኖስ
2. ቅዱስ ፊልጶስ
3. ቅዱስ ጵሮክሮስ
4. ቅዱስ ጢሞና
5. ቅዱስ ኒቃሮና
6. ቅዱስ ጳርሜና
7. ቅዱስ ኒቆላዎስ
ሐ ሰባት የጌታ ቃላት /እኔ ነኝ
1. የሕይወት እንጅራ እኔ ነኝ
2. የዓለም ብርሃን እኔ ነኝ
3. እኔ የበጎች በር ነኝ
4. መልካም እረኛ እኔ ነኝ
5. ትነሣዔና ሕይወት እኔ ነኝ
6. እኔ መንገድና ሕይወት ነኝ
7. እውነተኛ የወይን ግንድ እኔ ነኝ
መ ሰባቱ ሰማያት
1. ጽርሐ አርያም
2. መንበረ መንግሥት
3. ሰማይ ውዱድ
4. ኢየሩሳሌም ሰማያዊት
5. ኢዮር
6. ራማ
7. ኤረር
ሠ ሰባቱ ሊቃነ መላእክት
1. ቅዱስ ሚካኤል
2. ቅዱስ ገብርኤል
3. ቅዱስ ሩፋኤል
4. ቅዱስ ራጉኤል
5. ቅዱስ ዑራኤል
6. ቅዱስ ፋኑኤል
7. ቅዱስ ሳቁኤል
ረ ሰባቱ አብያተ ክርስቲያናት
1. የኤፌሶን ቤተ ክርስቲያን
2. የሰርምኔስ ቤተ ክርስቲያን
3. የጴርጋሞን ቤተ ክርስቲያን
4. የትያጥሮስ ቤተ ክርስቲያን
5. የሰርዴስ ቤተ ክርስቲያን
6. የፊልድልፍልያ ቤተ ክርስቲያን
7. የሎዶቅያ ቤተ ክርስቲያን
ሰ ሰባቱ ተዐምራት
ጌታ እኛን ለማዳን በመስቀል ላይ በተሰቀለ ጊዜ የተፈጸሙ
ተዐምራት
1. ፀሐይ ጨልሟል
2. ጨረቃ ደም ሆነ
3. ከዋክብት ረገፉ
4. ዐለቶች ተሠነጠቁ
5. መቃብራት ተከፈቱ
6. ሙታን ተነሡ
7. የቤተ መቅደስም መጋረጃ
ሸ ሰባቱ የመስቀሉ ቃላት
1. አምላኬ አምላኬ ለምን ተውከኝ
2. አባት ሆይ የሚያደርጉትን አያውቁምና ይቅር በላቸው
3. ዛሬ ከእኔ ጋራ በገነት ትሆናለህ
4. እነሆ ልጅሸ እናትህ እነሆት
5. ተጠማሁ
6. ተፈጸመ
7. አባት ሆይ ነፍሴን በእጅህ አደራ እስጥሃለሁ
ቀ ሰባቱ ምሥጢራተ ቤተ ክርስቲያን
1. ምሥጢረ ጥምቀት
2. ምሥጢረ ሜሮን
3. ምሥጢረ ቁርባን
4. ምሥጢረ ክህነት
5. ምሥጢረ ተክሊል
6. ምሥጢረ ንስሐ
7. ምሥጢረ ቀንዲል
በ ሰባቱ ዐበይት አጽዋማት
1. ዐቢይ ጾም
2. የሐዋርያት ጾም
3. የፍልሰታ ጾም
4. ጾመ ነቢያት
5. ጾመ ገሀድ
6. ጾመ ነነዌ
7. ጾመ ድኅነት
ተ ሰባቱ በእግዚአብሔር ዘንድ የተጠሉ ነገሮች
1. ትዕቢተኛ ዓይን ምሳ 16፡6-19
2. ሃሰተኛ ምላስ
3. ንፁህን ደም የምታፈስ እጅ
4. ክፉ ሃሳብን የምታፈልቅ ልብ
5. ለክፋት የምትፈጥን እጅ
6. የሐሰት ምስክርነት
7. በወንድሞች መካከል ጠብን የምታፈራ ምላስ
ቸ ሰባቱ ፀሎት ጊዜያት
1. ነግህ የጠዋት ጸሎት
2. ሠለስት (የ3 ሰዓት ጸሎት)
3. ቀትር (የ6 ሰዓት ጸሎት)
4. ተሰአቱ (የ9 ሰዓት ጸሎት)
5. ሰርክ (የ11 ሰዓት ጸሎት)
6. ነዋም (የምኝታ ጸሎት)
7. መንፈቀ ሌሊት (የሌሊት ጸሎት)
ኀ ሰባቱ ራሶች (2ኛ ነገ. 17፡6)
1. ኢራን
2. ኢራቅ
3. ግሪክ
4. ሚዳን
5. ግብጽ
6. ጣሊያን
7. እስራኤል
ወስብሐት ለእግዚአብሔር ለዘበቅዱሳኒሁ
ይሴባሕ ይእዜኒ ወዘልፈኒ ወለዓለም ዓለም አሜን፡፡ ወአሜን
ለይኩን ለይኩን፡፡
I like it averting and I learn A lot thank's GOD blessed you guys
ReplyDeletewe all are the son and the daughter of GOD. GOD blessed us Amen.
አስፈላጊ ነው
ReplyDeleteእግዚአብሔር ይስጥልን በጣም ስፈልግ የነበረውን ነው ዘርዝረው የጻፉልን:: እግዚአብሔር ይባርቃችሁ::
ReplyDelete