ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ነኝ

ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ነኝ
ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ነኝ

Saturday, March 26, 2016

ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ነኝ: ሰንበት

#ሰንበት !
‹‹ስድስት ቀን ስራ፣ተግባርህም ሁሉ አድርግ በሰባተኛው ቀን
ግን ለእግዚአብሔር ለአምላክህ ሰንበት ነው፡፡
እግዚአብሔርም በሰባተኛው ቀን አርፏልና ስለዚህ
እግዚአብሔር የሰንበትን ቀን ባርኮታል ቀድሶታል፡፡ ›› (ዘጸ
20፡10-11)
ሰንበት ማለት ምን ማለት ነው ?
ሰንበት ማለት አቆመ፣አረፈ ማለት ነው፡፡ይህ ቀን የጌታ ዕረፍት
የተባረከም ቀን ነው፡፡ከማንኛውም ሥጋዊ ሥራ ተቆጥበን
የእግዚአብሔርን ውለታ የምናስብበት ቀን ነው፡፡ ሰው እረፍት
ያስፈልገዋል፡፡ የሰንበት ቀንም የተፈጠረው ለዚህ ነው፡፡ (ዘዳ
5፡14)፣(ማር 2፡38)
ከሳምንቱ ሰባት ቀናት መካከል ለእረፍት የተቀደሰው
የተባረከው ዕለት ሰንበት ብቻ ነው፡፡ ስለሌሎች ቀናት
የተነገረው ‹‹ ያ መልካም እንደሆነ አየ››የተባለው ብቻ ነው፡፡
ሰንበትን ግን ባርኮታል ቀድሶታል፡፡ (ዘፍ 1፡12፣ 18፡ 20፣
25፡31)
በሐዲስ ኪዳን ለክርስቲያን ሁለት ሰንበት አለ ቀዳሚት ሰንበት
(ቅዳሜ) እና ሰንበተ ክርስቲያን(እሑድ)
1. ቀዳሚት ሰንበት (ቅዳሜ) ጌታ ያረፈባት ለእስራኤል ዘሥጋ
የታዘዘው ሰንበት ነው፡፡
ይህ ቀን እስራኤላውያንን እግዚአብሔር አምላክ ከግብፅ
ባርነት ወደ እረፍት እንዳወጣቸው ያመለክታል፡፡(ዘዳ
5-2-16) በእግዚአብሔር እና በህዝቡ መካከል ምልክት ነበረ
ሰንበትን አለማክበር ግን ከባድ ቅጣት ያስከትል ነበር፡፡ (ዘጸ 3፡
17) ፣ (ሕዝ 20፡12) ፣ (ዘኁ 15፡32-36)
ፈሪሳውያን በነበራቸው የተሳሳተ አመለካከት በሰንበት ቀን
እንኳን መልካም ሥራን አይሰሩም ነበር፡፡ስለዚህም በጌታችን
በኢየሱስ ክርስቶስ ተወቅሰዋል፡፡ (ማቴ 12፡14) ፣ (ሉቃ 4፡
16)
በዘመነ ሐዲስ የክርስቲያኖች የቀዳሚት ሰንበት አከባበር እንደ
አይሁድ ለሰው የሚከብድ እንዳይሆን በፍትሐ ነገሥት አንቀጽ
19 ላይ ተገልጿል፡፡
2. ሰንበተ ክርስቲያን (እሑድ)
እሑድ ማለት ‹‹አሐደ›› ከሚለው የግእዝ ቃል የወጣ ሲሆን
ትርጉሙም የመጀመሪያ ማለት ነው፡፡ ይህቺ ዕለት በመጽሐፍ
ቅዱስ ‹‹ከሳምንቱ በፊተኛው ቀን›› በመባል ትታወቃለች፡፡
ዮሐንስም በራዕዩ ‹‹የጌታ ቀን›› ያላት ናት (ራእይ 1፤10) ፡፡
ቅዱስ ያሬድም በድጓው ላይ ‹‹ዕለተ እግዚአብሔር›› የሚላት
ዕለተ እሑድ ናት፡፡
ዕለተ እሑድ እንደ ሰንበት የሚከበርበት ምክንያቶች፡-
- እግዚአብሔር ሥራውን የጀመረባት ለሥነፍጥረት መጀመሪያ
ዕለተ (ጥንተ ዕለት) ናትና
- ዕለተ ሥጋዌ ናት፡፡ ጌታ የተፀነሰባትና እርቅ የተወጠነባት
የፍሰሐ ቀን፡፡
- ዕለተ ትንሣኤ ናት፡፡ ጌታ ከሙታን ተለይቶ የተነሳባት ዕለት
- የቤተ/ክ የልደት ቅን ናት፡፡መንፈስ ቅዱስ ለሐዋሪያት
የወረደባት ኃይልና ፅናትን ያኙባት ዕለት
-ጌታ በክበበ ትስብእት በግርማ መለኮት ዳግም በቅዱሳን
መላእክቱ ታጅቦ በጌትነቱ ለፍርድ የሚመጣባት ታላቅ የፍርድ
ቀን ናትና የተለያዩ መንፈሳዊ አገልግሎቶች የሚካሄዱባት ዕለት
ናት (1ኛ ቆሮ 16፤1)
-የሐዋሪያት ዘመንም በጤሮዓዳ ያሉ ክርስቲያኖች እሑድ ቀን
ይሰበሰቡ ነበር (የሐዋ. 20፤7)
በቤተክርስቲያን ታሪክ ንጉሥ ቆስጠንጢኖስ ዕለተ እሑድ
የክርስቲያኖች ሰንበት ናት በማለት ሥራ እንዳይሰራባት አዋጅ
አስነግሮ ነበር፡፡ ምንም እንኳን ይህቺ ዕለት በሐዲስ ኪዳን
መከበር የጀመረ ቢሆንም በብሉይ ኪዳን ከፋሲካ በፊት የሰንበት
(የቀዳሚት) ማግስት በመባል በኩራት እና ቀዳሚያት
የሚያቀርቡበት ቀን ነበር፡፡ (ራዕ 1፡10)
በቀዳሚት ሰንበት ቅዱስ እግዚአብሔር ከሥራው ሁሉ አርፎ
ሥጋዊ እረፍትን ለሰው እንዳስተማረ በእሑድ ቀን (በሰንበተ
ክርስቲያን) በጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ አዳኝነት
የተገኘውን የዘላለማዊ የነፍስ ዕረፍት የምናስብበት ነው፡፡ (ዕብ
4፡1-10)
ከሰንበት ረድኤት በረከት ይክፈለን!

ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ነኝ: የእመቤታችን 5ቱ ሀዘናት

የእመቤታችን 5ቱ ሀዘናት
◆ ◆ "ስምዖንም ባረካቸው እናቱን ማርያምንም። እነሆ፥
የብዙዎች ልብ አሳብ ይገለጥ ዘንድ፥ ይህ በእስራኤል ላሉት
ለብዙዎቹ ለመውደቃቸውና ለመነሣታቸው ለሚቃወሙትም
ምልክት ተሾሞአል፥ በአንቺም ደግሞ በነፍስሽ ሰይፍ ያልፋል
አላት።" ሉቃስ 2:33-34
◆ ◆ "የአሥራ ሁለት ዓመት ልጅ በሆነ ጊዜ፥ እንደ በዓሉ
ሥርዓት ወደ ኢየሩሳሌም ወጡ፤ ቀኖቹንም ከፈጸሙ በኋላ፥
ሲመለሱ ብላቴናው ኢየሱስ በኢየሩሳሌም ቀርቶ ነበር፥
ዮሴፍም እናቱም አላወቁም ነበር። ከመንገደኞች ጋር የነበረ
ስለ መሰላቸው የአንድ ቀን መንገድ ሄዱ፥ ከዘመዶቻቸውም
ከሚያውቋቸውም ዘንድ ፈለጉት፤ ባጡትም ጊዜ እየፈለጉት ወደ
ኢየሩሳሌም ተመለሱ። ከሦስት ቀንም በኋላ በመምህራን
መካከል ተቀምጦ ሲሰማቸውም ሲጠይቃቸውም በመቅደስ
አገኙት፤ የሰሙትም ሁሉ በማስተዋሉና በመልሱ ተገረሙ።
ባዩትም ጊዜ ተገረሙ፥ እናቱም። ልጄ ሆይ፥ ለምን እንዲህ
አደረግህብን? እነሆ፥ አባትህና እኔ እየተጨነቅን ስንፈልግህ
ነበርን አለችው። እርሱም። ስለ ምን ፈለጋችሁኝ? በአባቴ ቤት
እሆን ዘንድ እንዲገባኝ አላወቃችሁምን? አላቸው።" ሉቃስ
2:41-48
◆ ◆"በዚያን ጊዜም ጲላጦስ ኢየሱስን ይዞ ገረፈው።
ወታደሮችም ከእሾህ አክሊል ጐንጕነው በራሱ ላይ አኖሩ ቀይ
ልብስም አለበሱት፤ እየቀረቡም። የአይሁድ ንጉሥ ሆይ፥ ሰላም
ለአንተ ይሁን ይሉት ነበር፤ በጥፊም ይመቱት ነበር። ጲላጦስም
ደግሞ ወደ ውጭ ወጥቶ። እነሆ፥ አንዲት በደል ስንኳ
እንዳላገኘሁበት ታውቁ ዘንድ እርሱን ወደ ውጭ
አወጣላችኋለሁ አላቸው። ኢየሱስም የእሾህ አክሊል ደፍቶ ቀይ
ልብስም ለብሶ ወደ ውጭ ወጣ። ጲላጦስም። እነሆ ሰውዬው
አላቸው። የካህናት አለቆችና ሎሌዎች ባዩትም ጊዜ። ስቀለው
ስቀለው እያሉ ጮኹ። ጲላጦስም። እኔስ አንዲት በደል ስንኳ
አላገኘሁበትምና እናንተ ወስዳችሁ ስቀሉት አላቸው።" ዮሐንስ
19:1-6
◆ ◆ "ኢየሱስንም ይዘው ወሰዱት፤ መስቀሉንም ተሸክሞ
በዕብራይስጥ ጎልጎታ ወደ ተባለው የራስ ቅል ስፍራ ወደሚሉት
ወጣ። በዚያም ሰቀሉት፥ ከእርሱም ጋር ሌሎች ሁለት፥ አንዱን
በዚህ አንዱን በዚያ ኢየሱስንም በመካከላቸው ሰቀሉ።
ጲላጦስም ደግሞ ጽሕፈት ጽፎ በመስቀሉ ላይ አኖረው፤
ጽሕፈቱም። የአይሁድ ንጉሥ የናዝሬቱ ኢየሱስ የሚል ነበረ።"
ዮሐንስ 19:17-19
◆ ◆ "ከዚህም በኋላ አይሁድን ስለ ፈራ በስውር የኢየሱስ ደቀ
መዝሙር የነበረ የአርማትያስ ዮሴፍ የኢየሱስን ሥጋ ሊወስድ
ጲላጦስን ለመነ፤ ጲላጦስም ፈቀደለት። ስለዚህም መጥቶ
የኢየሱስን ሥጋ ወሰደ። ደግሞም አስቀድሞ በሌሊት ወደ
ኢየሱስ መጥቶ የነበረ ኒቆዲሞስ መቶ ንጥር የሚያህል
የከርቤና የእሬት ቅልቅል ይዞ መጣ። የኢየሱስንም ሥጋ
ወስደው እንደ አይሁድ አገናነዝ ልማድ ከሽቱ ጋር በተልባ እግር
ልብስ ከፈኑት። በተሰቀለበትም ስፍራ አትክልት ነበረ፥
በአትክልቱም ማንም ገና ያልተቀበረበት አዲስ መቃብር ነበረ።
ስለዚህ መቃብሩ ቅርብ ነበረና ስለ አይሁድ ማዘጋጀት ቀን
ኢየሱስን በዚያ አኖሩት።" ዮሐንስ 19:38-42
የእመቤታችን 5 ቱ ሀዘናት
◆ ◆ " ስምዖንም ባረካቸው እናቱን ማርያምንም ። እነሆ ፥
የብዙዎች ልብ አሳብ ይገለጥ ዘንድ ፥ ይህ በእስራኤል ላሉት
ለብዙዎቹ ለመውደቃቸውና ለመነሣታቸው ለሚቃወሙትም
ምልክት ተሾሞአል በአንቺም ደግሞ ፥ በነፍስሽ ሰይፍ ያልፋል
አላት ።" ሉቃስ 2:33-34
◆ ◆ " የአሥራ ሁለት ዓመት ልጅ በሆነ ጊዜ ፥ እንደ በዓሉ
ሥርዓት ወጡ ፤ ወደ ኢየሩሳሌም ቀኖቹንም ከፈጸሙ በኋላ ፥
ሲመለሱ ብላቴናው ኢየሱስ በኢየሩሳሌም ቀርቶ ነበር ፥
ዮሴፍም እናቱም አላወቁም ነበር ። ከመንገደኞች የነበረ ጋር
ስለ መሰላቸው የአንድ ቀን መንገድ ሄዱ ከዘመዶቻቸውም
ከሚያውቋቸውም ዘንድ ፥ ፈለጉት ባጡትም ፤ ጊዜ ወደ
ኢየሩሳሌም እየፈለጉት ተመለሱ ። ከሦስት ቀንም በኋላ
በመምህራን መካከል ተቀምጦ ሲሰማቸውም ሲጠይቃቸውም
በመቅደስ አገኙት የሰሙትም ሁሉ ፤ በማስተዋሉና በመልሱ
ተገረሙ ። ባዩትም ጊዜ ፥ እናቱም ተገረሙ ። ልጄ ሆይ ፥
ለምን እንዲህ አደረግህብን? እነሆ ፥ አባትህና እኔ እየተጨነቅን
ስንፈልግህ ነበርን አለችው ። እርሱም ። ስለ ምን ፈለጋችሁኝ?
በአባቴ ቤት እሆን ዘንድ እንዲገባኝ አላወቃችሁምን? አላቸው
።" ሉቃስ 2:41-48
◆ ◆ " በዚያን ጊዜም ጲላጦስ ኢየሱስን ይዞ ገረፈው ።
ወታደሮችም ከእሾህ አክሊል ጐንጕነው አኖሩ ቀይ በራሱ ላይ ፤
ልብስም አለበሱት እየቀረቡም የአይሁድ ። ሰላም ንጉሥ ሆይ ፥
ለአንተ ይሉት ነበር ፤ ይሁን በጥፊም ይመቱት ነበር ። ደግሞ
ጲላጦስም ወጥቶ ወደ ውጭ ። እነሆ ፥ አንዲት በደል ስንኳ
እንዳላገኘሁበት ዘንድ ታውቁ እርሱን ወደ ውጭ
አወጣላችኋለሁ አላቸው ። ኢየሱስም የእሾህ አክሊል ደፍቶ ቀይ
ልብስም ለብሶ ወደ ውጭ ጲላጦስም ወጣ ። ። ሰውዬው
አላቸው ። እነሆ የካህናት አለቆችና ሎሌዎች ባዩትም ጊዜ
ስቀለው ስቀለው እያሉ ። ። ። ጮኹ ጲላጦስም እኔስ አንዲት
በደል ስንኳ አላገኘሁበትምና እናንተ ወስዳችሁ ስቀሉት አላቸው
።" ዮሐንስ 19:1-6
◆ ◆ " ኢየሱስንም ይዘው ወሰዱት መስቀሉንም ፤ ወደ
ተሸክሞ በዕብራይስጥ ጎልጎታ ተባለው የራስ ቅል ወጣ ። ስፍራ
ወደሚሉት ሰቀሉት ፥ በዚያም ከእርሱም ጋር ፥ ሌሎች ሁለት
አንዱን በዚህ አንዱን በዚያ ኢየሱስንም በመካከላቸው ሰቀሉ
ጲላጦስም ። ደግሞ ጽሕፈት በመስቀሉ ላይ ጽፎ አኖረው ፤
ጽሕፈቱም የአይሁድ ንጉሥ የናዝሬቱ ። ኢየሱስ የሚል ነበረ ።"
ዮሐንስ 19:17-19
◆ ◆ " ከዚህም በኋላ ስለ አይሁድን ፈራ በስውር የኢየሱስ ደቀ
መዝሙር የነበረ የአርማትያስ ዮሴፍ የኢየሱስን ሥጋ ሊወስድ
ጲላጦስን ለመነ ጲላጦስም ፈቀደለት ። ፤ ስለዚህም መጥቶ
የኢየሱስን ሥጋ ወሰደ ። አስቀድሞ በሌሊት ደግሞም ኢየሱስ
ወደ መጥቶ የነበረ ኒቆዲሞስ መቶ ንጥር የሚያህል የከርቤና
የእሬት ቅልቅል ይዞ የኢየሱስንም ሥጋ መጣ ። እንደ አይሁድ
ወስደው አገናነዝ ልማድ ከሽቱ በተልባ እግር ልብስ ጋር ።
ስፍራ ከፈኑት በተሰቀለበትም አትክልት ነበረ ፥ በአትክልቱም
ማንም ያልተቀበረበት ገና አዲስ መቃብር ነበረ ። ስለዚህ ስለ
መቃብሩ ቅርብ ነበረና አይሁድ ማዘጋጀት ቀን ኢየሱስን በዚያ
አኖሩት ።" ዮሐንስ 19:38-42

ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ነኝ: ያለእመቤታችን አማላጅነት አለም አይድንም

ያለእመቤታችን አማላጅነት አለም አይድንም" - - - ይህ
ለሚያምን እንጂ ለማያምን የሚነገር አይደለም!! በስመ አብ
ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሃዱ አምላክ አሜን፡፡ ስለዚህ ቃል
ሰወች ምን ይላሉ? በእውኑ ያለክርስቶስ መዳን አለን? መዳን
በማንም የለም ተብሎ ተፅፏልና፡፡ ነገር ግን ከእናንተ ውስጥ
የቅዱሳንን የፀጋ መጠን የሚያውቅ ማን ነው? ለአንዳንዶቹ
የፀጋ አማልክትነትን እንዲሁ ተቀብለዋልና፡፡ እንግዲህስ
አምላክ ከሆኑ ማዳንም መግደልም እንደሚችሉ አናውቅምን?
ወይንስ ለሃዋርያት የተሰጠ ፀጋ ምንድን ነው? በምድር ሆነው
ሳሉ የመፍታትም የማሰርም ስልጣን የተሰጣቸው አይደለምን?
መፍታትና ማሰርስ ማዳንና መኮነን ማለት አይደለምን? ታዲያ
እኒህ ሃዋርያት ፍጥረትን ያስሩና ይፈቱ ዘንድ ስልጣን ያላቸው
የክርስቶስን የማዳን ሃይል ተጋፉትን? ወይንስ ሙሴ በፈርኦን
ላይ አምላክ ሲሆን የእግዚአብሄርን አምላክነት ተሻማ ይሆን?
አይደለም ሙሴስ የፀጋ አምላክ እንጂ የባህሪ አምላክ ሆኖ
አልተገኝም ደግሞም ፀጋውን ከእግዚአብሄር የተቀበለው ነውና
ሰጭ በፈቃዱ ለተቀባይ ስጦታ ቢሰጥና ተቀባይ ስጦታውን
ቢጠቀምበት ሰጭውን የሚያናድድ አንድም የሚጋፋ
እንዳልሆነ ግልፅ ነው፡፡ ወይንስ በፍርድ ቀን ሃዋርያት በፍርድ
ዙፋን ተቀምጠው እንደሚፈርዱ ተጠቅሷልና ፍርድ
የእግዚአብሄር ሲሆን እኒህ ሃዋርያት ስለምን በእግዚአብሄር
ስራ ገባችሁ የሚል ማነው? የመፍረዱን ስልጣን ከሰጭው
በፀጋ ተለግሰዋልና ሰጭውን እያመሰገኑ በፀጋው ሃሴትን
ቢያደርጉ ነውንጂ እነርሱስ እግዚአብሄር እንደሆኑ የሚያስቡ
አይደለም፡፡ ወይንስ ሲፈርዱ አንዱንም ለሞት አንዱንም
ለህይወት ሲያደርጉ የማዳንና የመኮነን ስራ እየሰሩ አይደለምን?
አልያስ በመንፈስ ቅዱስ ተሹመዋልና በእውነት ነገር ግን
እንደወደዱ ይፈርዳሉ እንጂ ስለመፍረዳቸው ነፃ ፈቃድ
የላቸውምን? ነፃ ፈቃድ ከሌላቸውስ በዚህ ሰው ላይ ፍረዱ
በዚህኛው ግን እንዳትፈርዱ እየተባሉ ሊሰሩ በፍርድ ወንበር
የሚቀመጡ ከሆነ ከቶ የተሰጣቸው ክብር ምን ይሰራላቸዋል?
ሁሉን ትተው ክርስቶስን ስለ መከተላቸውስ ክርስቶስ የገባላቸው
ቃል ለከንቱ ነበርን? የሚያስተውል ያስተውላል፡፡ እንግዲህስ
ለቅዱሳን የተሰጠውን የፀጋ መጠን የሚያውቅ ከሌለ ከቅዱሳን
ሁሉ የምትበልጥ የእመቤታችንን ፀጋ ጠንቅቆ ማወቅ
የሚችል ማነው? ድንግልንስ ይህን ታደርጊያለሽ ፡ ይህንን ግን
ማድረግ አትችይም የሚላት ከፍጥረት ወገን ማን ነው?
እንግዲህ የእግዚአብሄር ቃል የመጣላቸውን እነዚያን አማልክት
ይባሉ ዘንድ የወደደ አምላክ አማልክት ያላቸው እንዲሁ ለከንቱ
ነውን? ቅዱስ ገብርኤልስ ድንግልን ፀጋን የተሞላሽ ሆይ ሲላት
በእውነት ከፀጋ የጎደለባት አንዳች ነገር አለን? እንዲህስ የምንል
ከሆነ ቅዱስ ገብርኤልን ሃሰተኛ እናደርገዋለን፡፡ እመቤታችን
ፀጋወችን ሁሉ ከተሞላች ለአንዳንዶች የተሰጠ የፀጋ አምላክነት
ከእርሷ የተለየ ነውን? ሙሴን የፀጋ አምላክ ያደረገ
እግዚአብሄር ሙሴ የሚታዘዝላትን እመቤት እንደምን አብልጦ
አያደርጋት? የፀጋ አምላክ ከሆነችስ ማዳን ይህ ከባድ ነውን?
ለእመቤታችንስ ከፀጋወች ሁሉ የሚበልጥ ፀጋን ይሄውም
እግዚአብሄርን መውለድ ገንዘቧ ያደረገች አይደለምን? እንግዲህ
መዳን በማን ነው? ያለክርስቶስ መዳን አለን? በፍፁም ሁሉ
ይድኑ ዘንድ የተዘጋጀ መዳኛ ክርስቶስ ነው ፡ ይህም ማዳኑ
የባህርይው ነው፡፡ ነገር ግን ደግሞ እንጠይቃለን ከቶ ሃዋርያት
ሙትን ሲያስነሱ እያዳኑ አይደለምን? ይህንን እንዴት አደረጉ?
ከራሳቸው ስልጣን ነውን? አይደለም ይልቅስ በፀጋ በተሰጣቸው
የማዳን አገልግሎትን ከክርስቶስ ተቀብለው በክርስቶስ ስም
ይፈፅማሉ እንጂ፡፡ እኔ ግን “ያለእመቤታችን አማላጅነት አለም
አይድንም” የሚለውን ሃይለ ቃል ባየ ጊዜ ይህ ሊባል አይገባም
የሚልን ሰው አንድ ጥያቄ እጠይቀዋለሁ ፦ ወንድሜ ሆይ
የድንግልን የፀጋ ስጦታ ሁሉ ታውቃለህን? አልያም ድንግል
ማርያም ይህን ይህን ማድረግ ትችላለች ፡ ይህን ይህን ደግሞ
ማድረግ አትችልም ማለት ትችላለህን? እኔ አንተን ብሆን ግን
ዝም ማለትን እመርጣለሁ ወይንም ምናልባት የቀደሙ
ኦርቶዶክሳውያን ቅዱሳን አባቶችን በመንፈስ እጠይቅ ዘንድ
ልቤን አነሳሳለሁ፡፡ በአንድ ነገር ግን እስማማለሁ እንዲህ ያለ
ቃል ለሚያምኑ የሚነገር እንጂ ለማያምኑ ደግሞም
ለመናፍቃን ይነገር ዘንድ የሚገባ እንዳልሆነ፡፡ እንደኔ ግን ይህን
ቃል ማንም ይናገረው ማንም በአለም እየኖረ አንድም አለም
ብሏልና አለማዊ ሆኖ መልካም ስራን እንኳን ሳይሰራ የሚል
ትርጓሜ ቢኖረው የእመቤታችንን ክብር ያላወቀ ፡ አውቆም
የተሳለቀ ፡ አፉንም በእርሷ ላይ በሽንገላ የከፈተ አይድንም ብየ
እመሰክራለሁ፡፡ አንድም ክብሯን አውቆም ቢሆን ለክብሯ
ራሱን ዘንበል ያላደረገ ፡ አክብሮትን ያልሰጠ ፡ የእግዚአብሄርን
አማናዊ ታቦት ባየ ጊዜ ለጥ ብሎ ያልሰገደ (አማንዊ ታቦት
ስንል እመቤታችንን እንደሆነ ይታወቃል) ፡ ምንም ያክል
በክርስቶስ አምናለሁ ቢል ደግሞም ስጋውን በልቻለሁ ደሙን
ጠጥቻለሁ ቢል ከአማውናዊና ሃዋርያዊት ቤተክርስቲያን
ምስጢረ ቁርባንን አላገኝምና ያገኝ እንኳን ቢመስለው መዳን
እንደማይችል እመሰክራለሁ፡፡ ነገር ግን ይህን እኔ ከራሴ
አመንጭቼ ይህን እላለሁ እንጂ ምን መልካም ነገር ተገኝብኝና
ትርጓሜ ውስጥ ራሴን አስገባለሁ፡፡ አሁን ግን ስለዚህ ጉዳይ
የአባ ጊዮርጊስን አስተምሮ እናጤን ዘንድ እንጀምር ፦ እስኪ
የተወደደ አባት ቅዱስ አባ ጊዮርጊስ ዘጋስጫ ስለእመቤታችን
ክብር እያደነቀ የተናገረውን እንመልከት ፦ አባ ጊዮርጊስ
እመቤታችንን የቤተክርስቲያን መሰረት አንቺ ነሽ ይላታል ፦“
እመቤቴ ማርያም ሆይ ፦ ከልጅሽ ከወዳጅሽ አንደበት
የሃይማኖት አለት ተብሎ ጴጥሮስ የተጠራባት አለት አንቺ ነሽ ፤
የሃዋርያት ጉባኤ የምትሆን ቅድስት ቤተክርስቲያን ባንቺ
ተመሰተች ፤ የንጉሱም ሙሽራ ባንቺ ተጌጠች ፤ - -- ባንቺም
ምሶሶች ቆሙ ፡ ሕንፃዋ ባንቺ ፀና ፡ግድግዳዋም ባንቺ ተሰራ ፡
ጠፈሯም ባንቺ ተጠፈረ ፡ ዋልታዋም ባንቺ ተዋቀረ ፡
ጭምጭሟም ባንቺ ተጨመጨመ ፤ ደጆቿም ባንቺ ተከፈቱ
፤ መቃን መድረኳም በልጅሽ ደም ተረጨ ፤ “ እስኪ እንግዲህ
አባታችንን እንጠይቀው ፦ አባታችን ሆይ የቤተክርስቲያን
መሰረት ክርስቶስ እንደሆነ አላስተማርከንምን ታዲያ ስለምን
አሁን የቤተክርስቲያን መሰረቷ እመቤታችን ነች አልከን ብለን፡፡
አባታችን ግን ይህን ሲናገር አላዋቂ ሆኖ አይደለም ፡
ስህተትንም ሰርቶ አይደለም ድንግልን በጠራ ጊዜ ልጇን
እየጠራ እንጂ ልጇን የባህርይ መሰረት ሲያደርገው ድንግልን
ደግሞ የፀጋ መሰረት ሲያደርጋት እንጂ ፡ ክርስቶስ የለበሰው ስጋ
የነሳው ነፍስ የድንግል ማርያም እንደሆነ ይናገር ዘንድ ይህን
አለ እንጂ ቤተክርስቲያንን በደሙ የመሰረታት ክርስቶስ
እንደሆነ አጥቶት አልነበረም፡፡ ነገር ግን ክርስቶስ ራሱ
ጴጥሮስን አንተ ደንጋይ ነህ በአንተ አለትነት ቤተክርስቲያኔን
እሰራለሁ ባለ ጊዜ በደሙ የተመሰረተችውን ቤተክርስቲያን
ጴጥሮስን እንኳን የፀጋ መሰረቷ እንዲሆን ወደደ፡፡ አባታችን
አባ ጊዮርጊስ አሁንም ይቀጥላል ፦ “የእውነተኛ ፀሃይ እናት
ድንግል ማርያም ሆይ ላንቺ እገዛለሁ ፤ ፍጥረት ሁሉ ላንቺ
ይገዛልና ፤ የልጅሽ ስም በሁሉ ከተነገረ ዘንዳ ያንቺ ስም ከዚያ
ይነገራልና፡፡ የአለም ሁሉ ክብር የነገስታትም ብእላቸው ድንግል
ሆይ ነገስታትና መኳንንት አለምም ሁሉ ከእግርሽ በታች
ከጫማሽ ወድቀው ይገዛሉ፡፡” አባታችን ይህን ባለ ጊዜ ድንግል
ማርያምን የፍጥረታት ሁሉ ገዥ አደረጋት፡፡ እንግዲህ ምን
እንላለን ስለእምነታችን መድከም አባታችን ሆይ ይህ እንዴት
ነው? የፍጥረታት ሁሉ ገዥ እግዚአብሄር አይደለምን? ብለን
ብንጠይቀው እግዚአብሄርን የባህርይ ገዥ ከፍጥረት ሁሉ በላይ
የሆነች እናታችን ማርያምን ግን የፀጋ ገዥ ያደርጋታል፡፡ ታዲያ
ለምን የፀጋስ ገዥ ያደርጋታል የሚል አለን? እንዲህ የሚለውን
ግን እኛ ደግሞ ለምን የፀጋ ገዥ አያደርጋትም ብለን ደግሞ
መልሰን እንጠይቀዋለን፡፡ እርሷ በልጇ ቀኝ የምትቆም ንግስት
ናትና ይህ ለእርሷ ምኗ ነው? ለእርሷ የሁሉ ንጉስ የባህርይ ገዥ
ልጇ ነውና የንጉሱ እናትን የሚናገር ማነው? ታዲያ አባታችን
የፀጋ ገዥ ካደረጋት ገዥ ደግሞ አይፈርድምን? ፈራጅስ አንዱን
ሊኮንን አንዱን ሊያፀድቅ የሚቀመጥ አይደለምን? የማይፈርድ
ከሆነስ ገዥነቱ ለምልክት ነውን? ከቶ ይህስ ከሆነ ምን
ይሰራለታል? አባታችን ቅዱስ አባ ጊዮርጊስ ዘጋስጫ ለማያምኑ
ከባድ የሚመስል ቃልን በአርጋኖን መፅሃፉ ያስነብበናል እንዲህ
ሲል ፦“ ድንግል ሆይ ፦ አዳም ከልጆቹ ጋር ያመሰግንሻል በሱ
የተፈረደ መርገመ ስጋ ባንቺ ጠፍቷልና ፡ እግዚአብሄር ሔዋንን
የረገማት ርግማን ባንቺ ተሽሯልና፡፡ “ ይህ ነገር እንዴት ነው?
የአዳም መርገም በድንግል ጠፋ ይለናልና፡፡ አባታችን ሆይ
ይህንን ስትል የአዳም ዘር ሁሉ መርገም በክርስቶስ የጠፋ
እንደሆነ አስቀድመህ ያስተማርከን አይደለምን? አሁን ይህንን
ለእመቤታችን ማድረግህ ስለምን ነው ብለን በእምነትና
በየዋህነት ብንጠይቀው ምን ብሎ ይመልስልን ይሆን?
አስቀድሞ አርዮስን በዘለፈበት የመፅሃፈ ምስጢር ድርሳኑ ላይ
አርዮስ ሆይ ክርስቶስን ፍጡር ነው ያልክ በፍጡር ደም
እንደምን የሰው ልጅ ይድናል እያለ የክርስቶስን አምላክነት
እየመሰከረ መዳንም በፍጡር ደም ሳይሆን በፈጣሪ እንደሆነ
እያስረዳ አሳፍሮት አይተናልና አሁን ራሱ ድንግል ፍጡር
መሆኗን ስናውቅ አርዮስን በዘለፈበት ቃል እርሱ ወደቀን?
አይደለም በተዋህዶ የከበረው የክርስቶስ ስጋና ደም ከድንግል
የነሳው መሆኑን ሲያጠይቅ ነው እንጂ ፡ አንድም የባህርይ
አዳኝና ርግማን አስወጋጅ ክርስቶስ ሲሆን ድንግል ግን በፀጋ
የተሞላች ፡ በቅድስና የተዋበች ፡ ከመርገም የራቀች ፡
ከሃጢአት የተጠበቀች የአዳም ተስፋው እንደሆነች ሲነግረን ነው
እንጂ ፡ አንድም በወንድ ዘር ምክንያት የሰውን ዘር ሁሉ
ሲቆራኝ የነበረው የባርነት ቀንበር ፡ የዲያቢሎስም ፀሃረኝነት
አንቺ ላይ ሲደርስ ተቁርጧልና ሲለን ነው ፤ እንግዲህ
አባታችንን ይህን ባልክ ጊዜ ሰው ልቡናው ተከፈለበት ብንለው
ምን ይለን ይሆን?እርሱ ግን አስቀድሞ በመፅሃፍ እንዳለው ይህ
ለሚያምን እንጂ ለማያምን የሚነገር አይደለም ይለናል፡፡
ይህንንም የሚመስል ሌላ ደግሞ ይናገራል “ቀድሜ
እንደተናገርሁት አሁንም ደግሞ መልሼ እንገራለሁ ፡ እንዲህ
ስል ኪሩብ የያዘው ዙፋን የረባኝ የጠቀመኝ የለም ፡ ሰማያትም
የረቡኝ የጠቀሙኝ የለም፡፡ እመቤቴ ሆይ አንቺ ግን ከሞት
ባርነት አዳንሽኝ ፡ የአብ በኩር ልጅ ካንቺ ስጋ በመልበሱ
ነው፡፡” ይህንም ሲል ለምን እንዳለ ደግሞ መልሶ ይናገረናል -
ድንግል ሆይ ከሞት ባርነት አዳንሺኝ ስለምን አልኩ ቢል ይህም
የአብ የበኩር ልጅ ክርስቶስ ካንቺ ስጋ በመልበሱ ነው ይለናል፡፡
እንግዲህ የምታስተውሉ መልሱልኝ ድንግል ሆይ ከሞት ባርነት
አዳንሺኝ ከሚል ቃልና ያለ ድንግል ማርያም አማላጅነት አለም
አይድንም ማለት የትኛው የሚልቅ የክብር ቃል ነው?
የትኛውስ ከፍ ያለ ክብር ይሰጣል? ቅዱስ አባታችን ሆይ ይህን
ሁሉ ስለድንግል ትናገር ዘንድ የወደድክ ደግሞም ድንግልን
በዚህ ሁሉ ክብር ያከበርካት ስለምንድን ነው ብንለው
የድንግልን ምስጋናዋን ለመግለፅ ታተርኩ ስለገናንነቷ ግን
ልፈፅመው አልቻልኩም እያለ እንዲህ ይለናል ፦ “ድንግል ሆይ
ባማረ በተወደደ ነገር ሁሉ መሰልሁሽ ምስጋናሽን ግን
ለመፈፀም አልቻልኩም፡፡እግዚአብሄር ን ባመሰገንሁ ጊዜ
ባንቺ ለስሙ ምስጋና አቀርባለሁ ፤ በስምሽም ፀሎቴን
በፀለይሁ ጊዜ ፀሎቴን ለልጅሽ አቀረብሁ፤ዳግመኛም
ውዳሴሽን ወደማወቅ ባህር ልዋኝ ወደድሁ ፡ ወደ ክብርሽ
ገናንነት ወደብ እደርስ ዘንድ ደከምሁ ፡ ያንዲቷን ማእበል
ሞገድ ያህል ስንኳን አላለፍሁም፡፡ ወደ ፅርሀ አርያም ጠፈር
ለመድረስ የሚቻለው ማነው? ከምድር በታች ወዳለው ባህር
መሰረትስ መዋኘት ማን ይችላል? ድንግል ሆይ ክብርሽን
ገናንነትሽን ጠንቅቆ መናገር የሚቻለው ማነው?”፡፡ እኛስ
የአባቶቻችን ልጆች ነንና በእምነት ሆነን ድንግል ሆይ ክብርሽን
ማን ይናገር ዘንድ ይችላል? ገናንነትሽን ማን መመጠን
ይችላል? እንላለለን፡፡ እንግዲህ ለቅዱስ አባታችን ያልተደረሰ
የምስጋናን ባህር ዋኝቶ የጨረሰ የድንግልንም የፀጋ ሙላት
መጨረሻ አይቶ ክብሯ እስከዚህ ድረስ ነው የሚል ማነው?
ለድንግል የተሰጣት ፀጋ ይህን ያክል ነው ይህንን ማድረግ
ትችላለች ፡ ይህንን ማድረግ ግን አትችልም የሚል ማነው?
ቅዱስ አባታችን አባ ጊዮርጊስ ዘጋስጫ ሆይ እስኪ መልስልን
አለም የድንግልን ስም ሳይጠራ ክብርን ያገኛልን? ደግሞስ
ሳያከብራት ይከብራልን? ወይንስ ሳይወዳት ይወደዳልን?
ወይንስ የተከበረ ማንም ቢኖር የተከበረች እናትን አላውቃትም
ሊል ይችላልን? ወይንስ ፃድቅ ማንም ቢኖር የፃድቃን ሁሉ
እናት ድንግል ማርያምን የማይደገፍ አለን? እስኪ ተናገረን
አለም ለዚያውም በሃጢአት ርኩሰት የወደቀ አለም ፡
እግዚአብሄርን የተሳደበ አለም ፡ ለዲያቢሎስ የሰገደ አለም ፡
ለዚያውም የድንግልን ክብር ያናናቀ አለም ቅዱስ ሊሆን
ይችላልን? ወይንስ በአባታችን እዮብ ላይ ሃዘንን ያመጡ እነዚያ
ሰወች ያለ እዮብ ፀሎት በእግዚአብሄር ዘንድ ተሰሙን?
እንግዲህስ ድንግልን ያላከበሩ ፡ በንቀትም የተናገሩ ያለፀሎቷ
ክርስቶስ ፊት በፅድቅ ሊቀርቡ ይቻላቸዋልን? እያልን
በጠየቅነው ጊዜ እንዲህ እያለ ድንግልን ባመሰገነ ጊዜ
በምስጋናው ውስጥ ይመልስልናል ፦ “ ድንግል ሆይ
የማያከብርሽ ለልእልናሽም የማይሰግድ ለዘላለሙ ርጉም
ነው፡፡ በፍፁም ልቦናው የማይወድሽ ፡ ከትልቅ ሃሳቡም
የማያከብርሽ ርጉም ነው ፤ በከንፈሮቹ የማያመሰግንሽ ፡
ባንደበቱም የማይመርቅሽ ርጉም ነው ፤ ለክብርሽ የማይሰግድ
ለገናንነትሽም የማይገዛ እድል ፈንታው ፀዋ ተርታው ገሃነመ
እሳት ነው፡፡” ይህንን ባለ ጊዜ ለድንግል የሚገባ ክብርን
ያልሰጠ በሰማይ በገነት ቦታ እንደሌለው ገለፀ፡፡ ማዳን
የከበዳችሁ ወንድሞች ሆይ አባ ጊዮርጊስን ስሙት ስለድንግል
ማዳን እንዲህ ይለናል ፦ “አቤቱ ክርስቶስ ሆይ ፦ ላንደበቴ ሃይለ
ቃሉን ስጥ የእመቤቴን የማህፀኗን መክበር የድንግልናዋን ነገር
አወራ ዘንድ ፤ እርሷም ደግሞ እኔን ለማዳን የታመነች ናት ፤
ለድንቁርናየም ልቡና ለአይኔም ብርሃኗ ለጆሮየም የበጎ
ምስራች ወሬ ናት፡፡” እርሷም ደግሞ እኔን ለማዳን የተጋች ናት
ባለ ጊዜ በተሰጣት የፀጋ ስጦታ ታድነኛለች ብሎ በድፍረት
መሰከረ ፡ ይህንም ሲል አዳኝ ክርስቶስ መሆኑን አጥቶት
መስሏችሁ እናንተ የምድር ሃጥአን በልባችሁ አታጉረምርሙ
የባህርይ አዳኝ ጌታችን ሲሆን የፀጋ አዳኝ ድንግልን እንዳደረጋት
አስተውሉ እንጂ፡፡ ወንድሞች ሆይ ሰው ምንም ፍጡር ቢሆን
አምላክ ፍጡርን ፈጣሪ ያደረገበትን ጥበብ ተረዱት ቃል ስጋ
በሆነ ጊዜ ሰው አምላክ ሆኗልና በኪሩቤልም ዙፋን
ተቀምጧልና ደግሞም ይህ ስጋ ከድንግል ያለወንድ ዘር የተገኝ
እንደሆነ አስተውሉና ለሰው የተሰጠው የፀጋ ብዛት ምን ያክል
እንደሆነ አድንቁ እንጂ ፡ እንግዲህስ ሰው አምላክ ከሆነ
ከእንግዲህ ለሰው ልጅ የጎደለበት ምን ፀጋ አለ? ስለቅዱሳንስ
የእግዚአብሄር ልጆች እንደሆኑ የተመሰከረላቸው አይደሉምን?
ልጆች ከሆኑ ደግሞ ወራሾቹ ናቸው ፡ ወራሾች ከሆኑ ደግሞ
ከአባታቸው በፀጋ እየተቀበሉ ሲያድኑ ብናይ ይህ አዲስ ነገር
አይደለም፡፡ እንግዲህስ ቅዱሳንን የእግዚአብሄር ልጆች ያደረግን
ድንግል ማርያምን ልጅ አይደለሽም እንላታለንን? አንላትም
ይልቅስ እሷ የእግዚአብሄር ልጅ ብቻ አይደለችም እናቱም
ደግሞ ሆነች እንጂ፡፡ ስለዚህም አባታችን ጊዮርጊስ ክብሯን
እያሰበ እየደጋገመ እንዲህ አላት፦”እመቤቴ ማርያም ሆይ
በሁሉ ተመሰልሽ ፡ በሁሉም መሰሉሽ ፡ አንቺን ግን
የሚመስልሽ የለም፡፡ - - - የአለም ሁሉ መድሃኒት የምትሆን
ብላቴና እግሯ የተመላለሰበቱን ምድር እስም ዘንድ ማን
በከፈለኝ ፤ ይቅርታን የምታሰጥ ብላቴና ጥላዋ ይነካኝ ዘንድ
ማን በከፈለኝ፡፡ የብርሃን ልጅ ወደሄደችበት እከተላት ዘንድ ማን
በከፈለኝ የእግሯንም ጫማ እሽከም ዘንድ ማን በከፈለኝ”
አባቴ ጊዮርጊስ ሆይ እኔስ ካንተ ጋር እመቤቴን አመሰግናት
ዘንድ ማን በከፈለኝ እላለሁ፡፡ አባታችን ሆይ ድንግልን የአለም
ሁሉ መድሃኒት የምትሆን አልካት ፡ ይህ ቃል እንዴት ነው?
የአለም መድሃኒት ኢየሱስ ክርስቶስ እንደሆነ ስታውቅ
እንዲህም እያልክ አስተምረኅን ሳለህ ይህ እንደምን ያለ ምስጋና
ነው? ለእግዚአብሄር የሚሰጠውን ምስጋና ለሰው ሰጠህን?
ይህንስ እንዳላደረክ እኛ እናውቃለን ነገር ግን ክርስቶስን
የባህርይ መድሃኒት ስታደርግ ድንግልን ደግሞ የፀጋ መድሃኒት
አደረግህ ፡ አማናዊ መድሃኒትን ወልዳልናለችና ፡ ቅዱስ ስጋውን
በበላን ክቡር ደሙንም በጠጣን ጊዜ አማናዊ መድሃኒት
የሚሆነን ጌታ ስጋውን ደሙንም ከድንግል ወስዷልና እንዲህ
አለ ፡ ደግሞም እኔ የአለም ብርሃን ነኝ ያለ አምላክ
ለሃዋርያቶቹ እናንተ የአለም ብርሃን ናችሁ ባለ ጊዜ የሱን
ብርሃንነት እንዳልሻረ ድንግልንም ስለተሰጣት ክብር ይህን
በተናገረ ጊዜ የክርስቶስን መድሃኒትነት አልሻረም ፡ ደግሞም
ስለፀሎቷ ሃይልና ስለቅድስናዋ ሙላት ይህንን ተናገረ፡፡
እንግዲህ እናንተ የምታስተውሉ ድንግልን የአለም መድሃኒት
የምትሆኝ ከማለት ይልቅ የአለም አማላጅ ማርያም ማለት
የቱ በክብር ይልቃል? አባታችንም ስለድንግል የፀሎቷ ሃይል
ሲናገር እንዲህ አለ ፦ “ድንግል እመቤቴ ማርያም ሆይ
ከፀሎትሽ ረዳትነት በቀር ሊረዳኝ የሚችል እንደሌለ አወቅሁ፡፡
ከልመናሽም በቀር የሚያድን እንደሌለ ያለበኩርሽም የሚበጀኝ
እንደሌለ አወቅሁ፡፡ --- ድንግል ሆይ ፦ ወዳንቺ ተጠጋሁ
በልጅሽም አመንሁ እርሱንም አመለክሁ ፡ ቸርነቱንም ተስፋ
አደረግሁ፡፡” ወንድሞች ሆይ እንግዲህ ምን እንላለን? አባታችን
አሁን የሚነግረን ከእስካሁኑ ይልቅ የሚበልጥ ነውና ፤ አሁንም
ግን ደግመን የአባታችንን ምክር እንናገራለን ፡ ይህ ለሚያምን
እንጂ ለማያምን አይደለም የሚለውን፡፡ አባታችን አባ ጊዮርጊስ
ዘጋስጫ ግን የድንግልን የክብር ሙላት ባሰበ ጊዜ እየተደነቀ
እንዲህ አለ፦ “በእብራይስጥ ማሪሃም የተባልሽ እመቤታችን
ድንግል ማርያም ሆይ ሁሉ ላንቺ ሆነ ፡ ሁሉም ስላንቺ ተፈጠረ
፡ አዳም ከህቱም ምድር ተፈጠረ አንቺን ያፈራ ዘንድ ነው ፡
ሔዋንም ከአዳም ከግራ ጎኑ ተፈጠረች አንቺን ትወልድ ዘንድ ፤
ምድርም ተፈጠረች አዳም አባትሽን ታስገኝ ዘንድ ፡፡
ለምግቡም ቡቃያውን ታወጣ ዘንድ ሰማይም ስለርሱ ተሰቀለ ፤
ፀሃይና ጨረቃም ከዋክብትም እንዲያበሩለት በመውጣትና
በመግባታቸው የዘመኑ ቁጥር እንዲታወቅ ተፈጠረ ፤ -- -
መላእክትም እንዲያገለግሉት ተፈጠሩ ፤ - -- ድንግል ሆይ
ክብርሽን ገናንነትሽን ለመናገር የሚቻለው ማነው? ምስጋናሽን
መናገር ማን ይችላል? “ ይህ ምስጋና እንዴት ያለ ምስጋና
ነው? እንደኔ በሃጢአት ለደከመ ሰው የሚከብድ ነውና ፤
ስለክርስቶስ ሁሉ በእርሱ ለእርሱ ተፈጠረ የሚልን ቃል መፅሃፍ
እየነገረን ሳለ ሁሉ ስለማርያም ተፈጠረ ይለን ዘንድ የወደደ ይህ
ቅዱስ አባት ይህ ነገር እንዴት ነው? ሁሉ ሲል ክርስቶስንስ
ይጨምራልን? አይደለም የተፈጠረው ሁሉ ሲልስ ሁሉን
ከፈጠረው ውጭ ማለቱ እንደሆነ ይታወቃል፡፡ ሁሉን የፈጠረ
ክርስቶስ ነውና ይህን ተናገረ፡፡ ነገር ግን ስለምን ድንግልን ሁሉ
ላንቺ ሆነ አላት ብንል አንድም የአዳም ዘር ሁሉ በሃጢአት
ወድቆ ሳለ ሰውን የሚወድ አምላክ አዳም ከውድቀት እንዲነሳ
አስቀድሞ ያሰባት ስለሷም ትንቢት ያስነገረላት ፡ በልዩ ልዩ
ምሳሌ የገለጣት ቅድስት እናት የአዳም የውድቀት መነሻ
ድንግል መሆኗን ሲያጠይቅ ነው፡፡ አንድም አዳም የተፈጠረው
አንቺን ሊያስገኝ ነው ሔዋንም የተፈጠረችው አንቺን ትወልድ
ዘንድ ነው እያለ ይናገርና ሃሳቡን ቢገታ አንቺም የምትወለጂው
ሰውን አምላክ የሚያደርገውን ንጉስ ክርስቶስን ልትወልጂ ነው
ሲል ነው ፡ ይህም ማለቱ ክርስቶስን ከሁሉ በላይ ማድረጉ
ነው፡፡ ደግሞም ሁሉ ስላንቺ ተፈጠረ ማለቱ አንደኛ በሰማይ
በምድር ያሉ ፍጥረታት ሁሉ ሰውን ሊያገለግሉ መፈጠራቸውን
ሲናገር ፡ መላእክት እንኳን ሰውን ሊረዱ እንደተፈጠሩ
ማስታወሱና እመቤታችንን ከፍጥረት ሁሉ የበላይ ሲያደርጋት
ነው ፤ እመቤታችንንም ከሁሉ በላይ ቢያደርጋት ከእርሷ
የተወለደውን ክርስቶስን ከሁሉ በላይ ሊያደርግ ቢወድ ነው፡፡
እንግዲህ ወንድሞች ሆይ “ሁሉ ስለ ድንግል ተፈጠረ ከሚለውና
ያለእመቤታችን አማላጅነት አለም አይድንም ከሚለው የትኛው
የበለጠ ክብር አለው? ድንግል ሆይ ክብርሽን ገናንነትሽን
ለመናገር የሚቻለው ማነው? ምስጋናሽን መናገር ማን
ይችላል? የአብ ፍቅር ፡ የወልድ ቸርነት ፡ የመንፈስ ቅዱስ
አንድነት ከሁላችን ጋር ይሁን፡፡ አሜን፡

ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ነኝ: የማዕተብ ሥርዓት

ሃይማኖት የልብ ብቻ አይደለም!!
አንዳንድ ሰዎች የማዕተብ ሥርዓትን ለመቃወምና
ዘመናውያን መስለው ለመታየት ‹‹እምነት በልብ ነው››
ይላሉ፤ ተሳስተዋል!
ሃይማኖት የልብ ብቻ አይደለም፤ የጠቅላላው ሕዋሳት ሁሉ
ናት፡፡ እግዚአብሔርን ስንወደውና ስናመልከው በልባችን ብቻ
ሳይሆን በአፋችንም በአንገታችንም በጠቅላላው ሰብአዊ
ተፈጥሯችን ሁሉ መሆን ይገባዋል፤ ምክንያቱም
እግዚአብሔር የጠቅላላው ሰውነታችን አምላክና ፈጣሪ
ስለሆነ ነው፡፡ ‹‹ስለዚህ በሰው ፊት የሚመሰክርልኝ ሁሉ እኔ
ደግሞ በሰማያት ባለው በአባቴ ፊት እመሰክርለታለሁ፤ በሰው
ፊትም የሚክደኝን ሁሉ እኔ ደግሞ በሰማያት ባለው በአባቴ
ፊት እክደዋለሁ፡፡›› (ማቴ.10÷32÷33)
በዚህ ቃለ ወንጌል መሠረት በኢ-አማንያን ዘንድ ክርስቲያን
መሆናችንን የምንገልፀው በልባችን ብቻ ሳይሆን በቃላችንና
በሥራችንም ጭምር ነው፡፡ በአንገታችንስ እንዳንመሰክርለት
ማን ያግደናል? በአንገታችን ባለው ማዕተብም
ለእግዚአብሔር እንመሰክራለን፡፡
የስሙን ምልክት በአንገታችን እናኖራለን፤ አናፍርበትም!!
የክርስቶስን ሞትና ትንሣኤ በጥምቀታችን እንደምንመሰክር
የጥምቀታችንንም ዓርማ በማተባችን እናረጋግጣለን፡፡
(ሮሜ 16÷13፤ ኢዩኤ. 2÷32፤ ሮሜ 6÷1-5፤
ማቴ.5÷11-12፤ 1ኛጴጥ.3÷21-22፤ 4÷12-16)