ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ነኝ

ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ነኝ
ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ነኝ

Wednesday, March 30, 2016

ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ነኝ: ©ኦርቶዶክስተዋህዶነኝ®™ “ዑራኤል የተባለ መልአክ ሊረዳኝ መጣ፡፡” መ/ዕዝ. ሱቱ. 2፡1

በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን::
በፍጹም መጠበቅን ጠብቆ ለዚህ ያደረሰን አምላካችን ክብርና
ምስጋን አምልኮትና ውዳሴ ይድረሰውና ይህን ታላቅ መልአክ
በችሎታችን መጠን እንድናመሰግን እግዚአብሔር ይርዳን፤
አምላክ ባለንበት ከሁላችን ጋር ይሁን፤ ምስጢሩን ይግለጥልን
አሜን፡፡
“ዑራኤል የተባለ መልአክ ሊረዳኝ መጣ፡፡” መ/ዕዝ. ሱቱ. 2፡1
በመንገድህ ሁሉ ይጠብቁህ ዘንድ መላእክቱን ስለ አንተ
ያዝዛቸዋልና፤ እግርህም በድንጋይ እንዳትሰናከል በእጆቻቸው
ያነሡሃል።
በተኵላና በእባብ ላይ ትጫማለህ፤ አንበሳውንና ዘንዶውን
ትረግጣለህ ::
በእኔ ተማምኖአልና አስጥለዋለሁ፤ ስሜንም አውቆአልና
እጋርደዋለሁ። ይጠራኛል እመልስለትማለሁ፥ በመከራውም
ጊዜ ከእርሱ ጋራ እሆናለሁ፤ አድነዋለሁ አከብረውለሁ። ረጅምን
ዕድሜ አጠግበዋለሁ፥ ማዳኔንም አሳየዋለሁ። መዝ.
90/91/፡11-16
አፈቅሮ ፈድፋደ፡- ዑራኤል ሆይ፣ ከመልኮች ሁሉ ይልቅ ያንተን
መልክአ ጸሎት እወዳለሁ፡፡ የመልክህ ስነ ጸዳል በደመ ወልድ
እግዚአብሔር የታተመ ነውና፡፡
ዑራኤል ሆይ፣ እግዚአብሔር ሀይሉን የሚገልጽብን መልአከ
ብርሃናት አንተ ነህ፡፡ በዐለተ ሥቅለት በደመ ወልድ ዓለምን
ለመቀደስ ከሁሉ ይልቅ አንተ ተሰይመሃልና፡፡ ስለክብርህ
የሰማይ መላእክት አደነቁ፡፡
ለተፈጥሮትከ፡-
ዑራኤል ሆይ፡- ያለ መናገር በጥንት አርምሞ ከነፋስና ከእሳት
ለተፈጠረ ተፈጥሮህ ሰላም እላለሁ፡፡ ዑራኤል ሆይ የተፈጥሮና
የይቅርታና የቸርነት ክቡር መልአክ ነህና ስለኛ ስለሰው ልጆች
ወደ ልዑል እግዚአብሔር ማልድ አማላጅነትህ ዘወትር ከጥፋት
ያድናልና፡፡
ለዝክረ ስምከ፡-
ዑራኤል ሆይ፡- ከማርና ከወተት ይልቅ ለሚጥመው ስም
አጠራርህ ሰላም እላለሁ፡፡
ዑራኤል ሆይ፡- ክፍልህ /ክንፍህ/ በደመ ወልድ እግዚአብሔር
የተከበረ /የታለለ/ ነውና፡፡ ለዓለሙ ሁሉ መድሃኒት ትሆን ዘንድ
ግሩም የሚሆን የእግዚአብሔር ሥልጣን በክብር ከፍ ከፍ
አደረገ፡፡ (መልክአ ዑራኤል)
“የእግዚአብሔር መልአክ በሚፈሩት ሰዎች ዙሪያ ይሰፍራል፥
ያድናቸውማል።” መዝ.33/34/፡7 የሊቀ መልአኩ የክዱስ
ዑራኤል ረድኤቱ በረከቱ ፍጹም አማላጅነቱ ከሁላችን ጋር
ይሁን፡፡
ካለመኖር ወደ መኖር ያመጣኝ፣ ካለማወቅ ወደ መረዳት
ያደረሰኝ አነሳስቶ ላስጀመረኝ አስጀምሮ ላስፈጸመኝ ጥንት
ላሌለው ቀዳማዊ ፍጻሜ ላሌለው ድህራዊ ያልኖረበት ጊዜ
የሌለ የማይኖርበት ጊዜም የማይኖር የዘላለም ንጉስ ሁሉን
ቻይ ፈጣሪ እግዚአብሔርን በራስ ፀጉሬ ቁትር በአጥንቶቼም
ልክ አመሰግናለሁ፡፡
በሰማይ ያሉ መላእክት በምድርም የሚኖሩ የአዳም ዘር ሁሉ
የሚያመሰግኗት በአማላጅነቷ ሁል ጊዜ የማትለየኝ ከፀሐይ
ሰባት እጅ የምታበራ የብርሃን እናት የሁሉ እመቤት የአምላክ
እናት ከተመረጡ የተመረጠች ከተለዩ የተለየች ከተከበሩ
የተከበረች እናቴ እመቤቴ ድንግል ማርያም በቃላት ልገልጸው
ከምችለው በላይ አመሰግናለሁ፡፡ ሌሊትና ቀን ቅዱስ ቅዱስ
ቅዱስ እያሉ የሰራዊት ጌታ እግዚአብሔርን የሚያመሰግኑና
ሳይሰለቹ የሚጠብቁን ሊቀነ መላእክት ቅዱስ ሚካኤል ቅዱስ
ገብርኤል ቅዱስ ሩፋኤል ቅዱስ ዑራኤል ቅዱስ ራጉኤል ቅዱስ
ፋኑኤል እልፍ አእላፋት የሆኑ ጠባቂ መላእክት ሳመሰግን
በደስታ ነው፡፡
በጸሎታቸው ያልተለዩኝን ጻድቃን አባቶቼን አቡነ
ተክለሃይማኖትን አቡነ ገብረምንፈስ ቅዱስን አቡነ
ሀብተማርያምን አቡነ አረጋዊን አቡነ ኪሮስንና ሌሎች ቅዱሳን
አባቶቼን እንዲሁም እናቶቼን ቅድስት ክርስቶስ ሰምራን
ቅድስት አርሴማን ብዙ ያልጠቀስኳቸው ቅዱሳንን ለማመስገን
ቃላት የለኝም፡፡
በሰማኝትነታቸው የጥንካሬ ምሳሌ የሆኑልኝ በጸሎታቸው
የረዱኝን ቅዱሳን ሰማዕታት ቅዱስ ጊዮርጊስን ቅዱስ
እስጢፋኖን መጥመቀ መለኮት ቅዱስ ዮሐንስንና ሌሎችን
ቅዱሳን ሰማዕታትን ሁሉ በእጅጉ አመሰግናለሁ ለዘላለሙ
አሜን፡፡
ወስብሐት ለእግዚአብሔር ለዘበቅዱሳኒሁ ይሴባሕ ይእዜኒ
ወዘልፈኒ ወለዓለም ዓለም አሜን፡፡ ወአሜን ለይኩን ለይኩን፡፡

ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ነኝ: 21

21 21 21 21 21 21 21
# ራእየ_ማርያም
21 21 21 21 21 21 21
# እመቤታችን_በጎልጎታ_ስጸ
ልይ_ልጇ_ፈጣሪዋ_ጌታችን
_አምላካችንና_መድኃኒታች ን_ኢየሱስ_ክርስቶስ_የገ
ለጸላት_ምሥጢር_ራእየ_ማ ርያም ቀርቧልና ይነበብ...
21 21 21 21 21 21 21
በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ ንዌጥን
በረድኤተ እግዚአብሔር ሕያው ራእየ ማርያም ወላዲተ
አምላክ ጸሎታ ወበረከታ የሃሉ ምስሌነ ለዓለመ ዓለም
አሜን።
21
ማርያም ለዮሐንስ እንዲህ አለችው ረቂቅ ምሥጢር በልቡናየ
የማይታወቅ ጌታዬ ፈጣሪዬ ልጄ የገለጸልኝ ምሥጢር በጎልጎታ
ስጸልይ ዐርብ ቀን በቀትር ብሩህ ደመና መጥቶ ከ፫ቱ ሰማያት
አውጥቶ አስቀመጠኝ ሁሉንም አሳየኝ ከአንቺ ከፈለገ ሰማይ
ተወልጃለሁና አንቺም ሰላምታ ይገባሻል እኔም ዕጹብ ድንቅ
ምሥጢርን እገልጽልሻለሁ አለኝ። እኔም መለስኩለት ጌታዬ
ፈጣሪዬ እንዳልህ ይሁን አልሁት ወደታች እይ አለኝ ወደ ታች
ስመለከት ዓለምን ሁሉ አየሁ ሰብእሰ ከንቶ የመሰል
መውዋዕሊሁኒ ከመ ጽላሎት የኃልፍ ሰው ከንቱ ነገርን
ይመስላል ዘመኑም እንደ ጥላ ያልፋል ይጠፋል ነፍሱም
ከሥጋው ትለያለች ለዘለዓለም አትኖርም የምትኖርበትም
አይታወቅም መዝሙር ፻፵፫:፬
21
እንግዲህ ሰው ሁሉ በከንቱ ነውን አልሁት እሱም መልሶ ዳዊት
ያለውን አልሰማሽምን አለኝ ሰው ሁሉ በከንቱ ለምን ይኮራል
ዕለት ዕለትስ ለምን ኃጢአት ይሠራል ዳግመኛስ ጢስ ታይቶ
እንደሚጠፋ የሰውም አኗኗር እንዲሁ ነው አለኝ መዝሙር
፶፩:፩። እኔም መለስሁለት የጻድቃን ነፍስ ከሥጋዋ ስትለይ
አሳየኝ አልሁት። መለሰልኝ ጥቂት ቆዪ አሳይሻለሁ አለኝ።
ከዚህ በኋላ ፲፪ መላእክተ ብርሃን በእጃቸው የወርቅ መስቀል
የወርቅ ጥና ይዘው በደረታቸው የእግዚአብሔርን ምልክት
አድርገው የጻድቃንን ነፍስ ለመቀበል ሲወርዱ አየሁ።
ወደዚያች ነፍስ መላእክተ ጽልመትም መጥተው መረመሯት
ምክንያትም አጥተው ሄዱ መላእክተ ብርሃን ግን ፫ ጊዜ
ጋርደው ከሥጋዋ ስትለይ እንዲህ አሏት ደስ ሲያሰኛት
ሲመክሩዋት አንቺ ንጽሕትና ብርሕት ነፍስ ሆይ ደስ ይበልሽ
ዕፅፍ ድርብ ደስታ ይገባሻል ነይ ውጪ ወደ አገርሽ እንሂድ አሏት
አንቺ ንጽሕት ብርህት ነፍስ ሆይ ቅዱስ ዳዊት የዕድሜዬን
መጠኑን ንገረኝ በእኩሌታው ዕድሜዬ አትውሰደኝ ያለውን
አስተውለሻልና። መዝሙር ፻፩:፳፬።
21
ዳግመኛም ጳውሎስ ዛሬ የሚገዙ የሚነዱ ኋላ እንዳልገዙ
እንዳልነዱ ይሆናሉ ዛሬ የሚበሉ የሚጠጡ ኋላ እንዳልበሉ
እንዳልጠጡ ይሆናሉ። የዚህም ዓለም ንብረት ብልጽግና ኃላፊ
ጠፊ መሆኑን አስበሽ ዲያብሎስን ድል ነስተሽዋልና ዓለምንም
ንቀሽ ጉዱፍ እንደሆነ እንደመርገም ጨርቅ ጥለሽዋልና
የማያረጀውን የማይጠፋውን መርጠሻልና ለዘለዓለም የሚኖር
መንግሥተ ሰማያትን ወደሻልና ነይ ወደ ፈጣሪሽ እንሂድ አሏት
የዚያን ጊዜ ሌሎች መላእክተ ብርሃን ወረዱ የወርቅ ዝርግፍ
ዕንቁ የብርሃን ቀጸላ ፲፪ የብርሃን መብራት ይዘው ከብርሃን
አክሊሎች ጋር ወረዱ ብርሃናቸውም ከፀሐይ ከጨረቃ ፯ እጅ
ያበራል ክርስቶስም ከ፭ኛው ሰማይ ድረስ መጣ እኔም ያችን
ነፍስ ለመገናኘት ሄድኩ መላእክተ ብርሃን ዕልል አሉ እኔም
ከእርሳቸው ጋር ዕልል አልኩ ምእመናን ሁሉ በእጃቸው
አጨበጭበው በቃላቸው ዕልል ብለው ለእግዚአብሔር
ምሥጋና አቀረቡ ዳግመኛ ክብር ሞቱ ለጻድቃን በቅድመ
እግዚአብሔር ፊት የከበረ ነው እንዳለ መዝሙር ፻፲፭:፮።
21
ያችን ነፍስ ወደ እግዚአብሔር አቀረቧት ነፍስ ሆይ ደስ ይበልሽ
ደስታ ይገባሻልና ወደ ፈጣሪሽም እጅ ንሺ ስገጂ አሏት እርሷም
ሰገደች ፈጣሪዋንም እጅ ነሳች አስቀድሞ ይጠብቃት የነበረው
መልአክ እግዚአብሔርን እንዲህ አለው አቤቱ የዚያች ነፍስ
ምግባሯን ነገርኩት እንደ አውነተኛነቷ አክብራት አለው
በእውነት የሚፈርድ ጌታም እንደፈጠርኩሽ ንጽሕት ሆነሽ
የኖርሽ ነፍስ ሆይ እንዴት ነሽ ቃሌን ያላቃለልሽብኝ
ያላበላሸሽብኝ እኔም አላበላሽሽም ሥጋሽንም በጊዜ ምጽአት
አነሣዋለሁ በክብር ከእኔ ዘንድ ትኖሪያለሽ ብሎ በሰው እጅ
ያልተፈተለ ከወተት የነፃ ነጭ ልብሽ ሰጣት ከፀሐይ ከጨረቃ ፯
እጅ የሚያበራ ፫ አክሊለ ብረሃን አቀዳጃት ሚካኤልን ጠርቶ
ንሳ ወደ ገነት ውሰዳት በአብርሃም በይስሐቅ በያዕቆብ አጠገብ
ተቀምጣ በደስታ ትኑር ዳግመኛ እስክመጣ ድረስ ያንጊዜ
ዋጋዋን እከፍላታለሁ ከቅዱሳን ጋር ትቆየኝ አለው፡፡
21
መላእክተ እግዚአብሔርም ይህን ፍርድ በሰሙ ጊዜ አቤቱ
ጌታችን ፍርድህ የተቃና አገዛዝህም በእውነት ነው ብለው ደስ
አላቸው እኔም እንደነሳቸው ደስ አለኝ ያችንም ነፍስ ሸኙዋት
ወደ ገነትም አደረሷት ጻድቃን ሰማዕታት አብርሃምና ይስሐቅ
ያዕቆብ አባቶቻችን እናቶቻችን ባሉበት ቅዱስ ዳዊት
በመካከላቸው በገናውን እየመታ ተቀበሏት እንዲህም አሉዋት
ንጽህትና ብርሕት ነፍስ ሆይ ለዘለዓለም የሚኖር ደስታ ሕይወት
ወደ አለበት ነይ ውጪ አሏት ያችም ነፍስ ከነሱ ጋራ ሄደች፡፡
21
እኛም ከዚህ በኃላ ተመለስን እነኛም እንዲህ እያሉ ሃሌ ሉያ
ቅዱስ ቅዱስ ቅዱስ እግዚአብሔር ፀባኦት ፍጹም ምሉዕ
ሰማያት ወምድር ቅዱሳተ ስብሐቲከ ዳግመኛም ስብሐት ለአብ
ስብሐት ለወልድ ስብሐት ለመንፈስ ቅዱስ እያሉ ፈጣሪያቸውን
አመሰገኑ እኔም ልጄን እንዲህ ስል መለስሁለት የኃጥአን ነፍስ
ከሥጋዋ ስትለይ አሳየኝ አልሁት ጥቂት ቆዬ አሳይሻለሁ አለኝ
ወደታችም አየሁ መላእክተ ብርሃንና መላእክተ ጽልመት ወደ
ኃጥእ ነፍስ ሄዱ መላእክት ብርሃን ቀርበው ያቺን የኃጥእ ነፍስ
መረመሩዋት መልካም ነገር አጥተው ሄዱ ያን ጊዜውን
መንፈስ ቅዱስ ተለያት የገሃነም እሳት ሹም ቆሞ ከሆዷ ገባ ያቺ
ነፍስ በብዙ ጭንቅ ከሥጋዋ ተለየች ሞቱ ለኃጥእ ጽዋግ የኃጥእ
ሞት የከፋ ነው እንዳለ መዝሙር ፴፫:፳፩
21
በክፋቷ በእሳት በትር በእሳት አለንጋ እየደበደቡ እያገረፉ ከሥጋዋ
ለይተው ወሰዷት አንቺ ነፍስ ወደ ማን ትሄጂ እግዚአብሔርን
አታውቂ እያሉ ሲደፏት ሲያዳፏት ወሰዷት ያቺም ነፍስ ኩነኔ
መኖሩን አላውቅም ነበር አውቄ ቢሆን ልልበስ ልብላ ልጠጣ
አልልም ነበር አሁንም ስለእግዚአብሔር ስለእግዝእትነ
ማርያም ደከመኝ አሳርፉኝ አለች ፈጣሪሽንና ማርያምን የካድሽ
ወንጀለኛ አናሳርፍሽም አሏት ሁለተኛም ስለ እግዝእትነ
ማርያም ደከመኝ አሳርፉኝ አለች ማርያም ወዴት
ታውቂያታለሽ እያሉ ሲወስዷት አይቼ ብዙ አለቀስኩ ብዙም
አዘንኩ ልጄን እንዲህ አልኩት ሰው ሆኖ የማይበድል እንጨት
ሆኖ የማይጤስ የለምና እባክህ ማርልኝ አልኩት፡፡
21
ልጄም መለሰልኝ አትዘኝ እናቴ ሆይ ሰው በምድር መልካም
ግብር ካልሰራ መማር አይገባውም አለኝ፡፡ ያን ጊዜ ልቅሶ
አበዛች ይህች ነፍስ ስለእግዝእትነ ማርያም ጥቂት አሳርፉኝ
እያለች ጩኸቷን ማብዛቷን በሰማሁ ጊዜ መሪር ዕንባ
አለቀስሁ ልቅሶዬንም ልጄ በሰማ ጊዜ ስለ እናቴ ስለ ማርያም
ብላችሁ ጥቂት አሳርፏት ይህቺን ነፍስ አለ ያቺንም ነፍስ ጥቂት
አሳረፏት፡፡ ከዚያም በኃላ አንቺ ጎስቋላ ነፍስ ወዴት ትሄጃለሽ
መግቢያሽ ወዴት ነው ወዮለሽ ወዮታ አለብሽ እያሉ ወሰዷት
ከኃጥእም ቦታ አደረሷት አቡሃ ለሐሰት የሐሰት አባት ሐሰት
የሚያናግር ሰው የሚያሳማ ዝሙት የሚያሰራ ወደ መሸታ ቤት
የሚያኬድ ዘፈን የሚያስወድድ ነፍስ የሚያስገድል ሰይጣን ወደ
እርስዋ ከጭፍሮቹ ከመላእክተ ጽልመት ጋር ተሸቀዳደመው
ሄዱ መረመሯትም ወገናቸው ሆና አገኙዋት አንቺ ጎስቋላ ነፈስ
ወደ ማን ትሄጂ ወደ መንግሥተ ሰማያት ትገቢ ትወጃለሽን
እያሉ ተዘባበቱባት ሠራዊተ መላእክት ካሉበት አደረሷት
በመካከላቸው ብትቆም ይህቺን የተረገመች ነፍስ ውሰዱልን
አሉ ሽታዋ አስቸገረን ብለው ጮሁ፡፡
21
ከዚህም በኃላ አንቺ ርግምት ነፍስ ወዮልሽ ወዮታ አለብሽ እያሉ
ወደ ሰማይ አወጧት ከእግዚአብሔር ፊት አደረሷት የፈጠረሽ
እግዚአብሔር ይህ ነው ስገጂ እጅ ንሺ አሏት ያችም ነፍስ
ሰገደች እጅም ነሳች ቀድሞ ይጠብቃት የነበረው መልአክ
ውቃቢ እቤቱ ጠብቅ ያልከኝ ነፍስ ይህቺው ብሎ ለጌታ
አቀረባት ጌታም መልሶ ነፍስ ሆይ ለምን በደልሽኝ ፀሐይና
ጨረቃን እያፈራረቅሁ ሳወጣ ከጻድቃን አለየሁሽ እህልን
ለምግብ ወሀን ለመጠጥ ዕፅዋትን አትክልትን ፈጠርኩልሽ
የነፍስሽን መድኃኒት መልካም ግብር መሥራት ለምን እረሳሽ
ቢላት እኔ ኩነኔ መኖሩን አላወቅም ነበር አውቄ ቢሆን ልብላ
ልጠጣ ልልበስ አልልም ነበር፡፡ ጌታም ካህናትና መጻሕፍት
ካንቺ ዘንድ አልነበሩምን ለምን አልሰማሻቸውም ለነፍስሽ
ስንቅ መልካም ግብር ለምን አልሰራሽም ብሎ ቢጠይቃት
እርሷም የምትመልሰው ብታጣ ዝም አለች፡፡ ከዚህ በኃላ ጌታ
በምድር መልካም ግብር ያልሰራ መማር አይገባውምና ንሱ
ወደ አባቷ ወደ ሰይጣን ውሰዷት ለገሃነመ እሳት ሹም
ለጥልምያኮስ ስጧት አለ ዳግመኛም እስክመጣ ድረስ በሲኦል
በጨላማ ቤት ትኑር አለ ይሀንንም በሰማች ጊዜ ጮኸች ወይኔ
ሳልፈጠር በቀረሁት ይሻለኝ ነበር የተወለድኩባት ቀን ርጉም
ትሁን ብላ አለቀሰች ያች ነፍስ ብታለቅስ ሁላችንም አለቀስን
መላእክትም አክሊላቸውን አውርደው አለቀሱ፡፡
21
ቅዱስ ዳዊትም ቦኑ ለከንቱ ፈጠርኮ ለሰብእ በውኑ የሰውን ልጅ
ለከንቱ ፈጥረኸዋልን እንዳለ መዝሙር ፹፰፡ ፵፯ ጌታም
ወምንት ይበቁዖ ለሰብእ ለእመ ኩሎ ዓለመ ረብሀ ወነፍሶ ኅጎለ
ሰው ሁሉ ዓለምን ቢገዛ ቢነዳ ነፍሱን ካጣ ምን ይጠቅመዋል
እንዳለ ማርቆስ ፰፡፴፮ ለዚያች ነፍስ ሁላችንም አለቀስን፡፡
21
ከዚህ በኃላ ልጄ እንዲህ አለኝ ወደ ገነት እንሂድ አለኝ ሂጄም
ጻድቃን ሰማዕታት ደናግል መነኮሳት መልካም ሰዎች
የሚኖሩበትን አየሁ ወደላይ አወጣኝ ሥሩ የማይታይ ከትልቅ
ገደል አደረሰኝ ከዚያው ፯ ብርሃናትን ከፀሐይ ከጨረቃ ፲፪ እጅ
የሚያበሩ አየሁ ፩ አረጋዊ (ሽማግሌ) ሰው መጥቶ ማርያም
ሆይ አንቺ የከበርሽ የማኀፀንሽም ፍሬ የከበረ ነው አንቺን ያዩ
ዓይኖቼ የከበሩ ናቸው ብሎ እጅ ነሳኝ ልጄን ይህ ሰው ማነው
ብየ ጠየቅሁት ሄኖክ ነው አለኝ፡፡
21
ዳግመኛም እንደሱ አንድ ሰው መጥቶ እጅ ነሳኝ ልጄን ይህስ
ሰው ማነው አልሁት ኤልያስ ነው አለኝ ከዚህ በኃላ ከታች አስከ
ላይ በወርቅ ቀለም የተጻፈ ዓምድ ወርቅ አየሁ ቁመቱ
በመላኩ ክንድ ፲፭ ይሆናል ጽሕፈቱም ረቂቅ ነው እኔም
ይኸንን አይቼ ልጄን ጠየቅሁት ይህ ረቂቅ ጽሕፈት የተጻፈበት
ዓምድ ወርቅ ምንድነው አልሁት የጻድቃን ስማቸው ነው አለኝ
የፊታቸው መልክ ብቻ ነው የተጻፈው ብዬ ብጥይቅ አይደለም
ሁለንተናቸውም ተጽፏል እንጂ አለኝ ሳይወለዱ ነው ከተወለዱ
በኃላ ብለው ካባታቸው ከአዳም በፊት ተጽፈዋል አለኝ፡፡
21
ዳግኛም በዓምደ ወርቅ ከተጻፈው ጽሕፈት የሚበልጥ
የተጻፈበት የእሳት ዓምድ ወርቅ አየሁ በዚያ በእሳት ዓምድ ላይ
የተጻፉ እነማን ናቸው ብለው ኃጥአን ናቸው አለኝ ሳይፈጠሩ ነው
ከተፈጠሩ በኃላ የተጻፈው ብለው ለዚህ ለሥቃይ አስቀድመው
የተጻፉ ናቸው ብሎ አለኝ መጽሐፍ ያለውን አልሰማሽምን አለኝ
ቦ እለ ተሐርዩ እምከርሠ እሞሙ እመሂ ለሢመት ወእመሂ
ለነዲ ከእናታቸው ማኀፀን የተመረጡ ለሹመትም ሆነ ለድኀነት
አሉ እንዳለ ቅዳሴ አትናቴዎስ ቁ. ፻፲፫።
21
ከዚህ በኃላ ወደሌላ ቦታ ወሰደኝ ከፀሐይ ከጨረቃ ፲፪ እጅ
የምታበራ አገር አየሁ በየሰዓቱ ፼ ፼ የሚያፈራ ብዙ ፍሬ ያለው
ብዙ አትክልትም አየሁ ዳግመኛም ተምር ገውዝ ለውዝ ሎሚ
ትርንጎ ፬፼ ከ፷፯ አትክልት መዓዛቸው ልቦና የሚመስጥ በዚያ
ቦታ አየሁ ልጄንም ጠየቅሁት ይህ ቦታ ለማን ይሆናል አልሁት
ወንድ በ፩ሴት ሴት በ፩ ወንድ ተወስነው በንጽሕና ቢኖሩ በሞቱ
ጊዜ መኖሪያቸው ይህ ነው በልቡናቸው ንጹሕ የሆኑ ሰዎች
እግዚአብሔርን ያዩታል ወደ እግዚአብሔርም ይወስዱዋቸዋል
እንዳለ ማቴዎስ ፭:፰።
21
ከዚህ በኃላ በዚህ ቦታ አንፃር የወይን ወንዝ ወደአለበት ቦታ
ወሰደኝ በዚያም ቦታ ደጋጎች አባቶቻችን አዳም አቤል ሴት
መላልኤል ቃይናን ያሬድ አልፋስክድ የቀደሙ አባቶቻችን ሁሉ
አሉበት መጀመሪያ አባታችን አዳም መጥቶ ማርያም ሆይ
እንዴት ነሽ አለኝ አንቺን ያዩ ዓይኖቼ ንዑዳት ክቡራት ናቸው
አለኝ አቤልም መጥቶ አንዴት ነሽ አለኝ የቀደሙ አባቶቻችን
ሁሉ እየመጡ መልካሚቱ ርግብ ማርያም ሆይ እንዴት ነሽ
አንቺን ያዩ ዓይኖቻችን ንዑዳት ክቡራት ናቸው ብለው እጅ ነሡኝ
ሰገዱልኝ ከዚህ በኃላ የመዓር ወንዝ ወዳለበት ወሰደኝ በዚያው
ቦታ ሙሴ አሮን አሞጽ ኢሳይያስ ናሆም ኤርሚያስ ሶፎንያስ
ነቢያት ሁሉ ኤልሳቤጥ ራሔል ሣራ ርብቃ የጸደቁ ሴቶች ሁሉ
አሉ የነቢያት አለቃ ሙሴ መጥቶ እጅ ነሣኝ ሰገደልኝ ፀምር
ፀዐዳ ማርያም ሆይ እነዴት ነሽ አለኝ አንቺን ያዩ ዓይኖች
ንዑዳት ክቡራት ናቸው አለኝ ነቢያትም ሁሉ መጥተው እጅ
ነሡኝ ሰገዱልኝ ጽርሕ ንጽሕት ማርያም ሆይ አንቺን ያዩ
ዓይኖቻችን ንዑዳት ክቡራት ናቸው ብለው እጅ ነሡኝ ሰገዱልኝ
እናቴ ሔዋን መጥታ እንዴት ነሽ አለችኝ ጽርሕት ንጽሕት
እንዴት ነሽ አለችኝ ጽርሕት ንጽሕት ማርያም ሆይ አንቺን ያዩ
ዓይኖቼ ንዑዳት ክቡራት ይሁኑ አለችኝ ክቡራት ቅዱሳት
አንስትም ሁሉ መጥተው እጅ ነሡኝ ሰገዱልኝ የእግዚአብሔር
ማደርያ እንዴት ነሽ አሉኝ ከዚህ በኃላ የወተት ወንዝ ወደአለነት
ቦታ ወሰደኝ በዚያ ቦታ ሄሮድስ የገደላቸው ፲፬፼ ከ፬፻ ሕፃናት
አሉ እነሱም ባዩኝ ጊዜ መጥተው እጅ ነሡኝ ሰገዱልኝ የደናግል
መመኪያቸው ማርያም ሆይ አንቺ ከሁሉ ይልቅ የከበርሽ ነሽ
አንቺን ያዩ ዓይኖቻችን የከበሩ ይሁኑ ብለው እጅ ነሡኝ
ሰገዱልኝ፡፡
21
ከዚህ በኃላ የወይን ወንዝ ወደአለበት ቦታ የሚኖሩ እነማናቸው
አልሁት ባልንጀራቸውን እንደራሳቸው ማለት እንደ ነፍሳቸው
የሚወዱ ለተራበ ያበሉ ለተጠማ ያጠጡ ለታረዘ ያለበሱ ሰዎች
በሞቱ ጊዜ ወደ እግዚአብሔር ይወስዳቸዋል እጅ ለመንሳት
ለመስገድ ወደፈለገ ሰማይ ሲወስዳቸው ቅዱሳን መጥተው
ይቀበሏቸዋል ዓለምን ድል ነሥተዋልና ዲያብሎስን
አሸንፈዋልና መልካም ግብር በመሥራት በእውነት ጎልማሶች
ናቸውና አገራችሁ ግቡ እንደኛ ደስ ይበላችሁ ይሏቸዋል አለኝ፡፡
21
ዳግመኛም ልጄን የማር ወንዝ ወደአለበት ቦታ እነማን
ይኖራሉ አልሁት ለችግረኛና ለምስኪን አስቦ የሚሰጥ እሱ
ምስጉን ነው እግዚአብሔር ከክፉ ቀን ያድነዋል ይጠብቀዋልም
ሕያውም ያደርገዋል፡፡ በምድር ላይ በሕይወት ሥጋ
በሚኖርበር ጊዜ ያስመሰግነዋል በጠላቶቹም እጅ አሳልፎ
አይሰጠውም ታምሞ በአልጋው ላይ ይረዳዋል፡፡ መልካሙን
ምንጣፍ ያነጥፍለታል እንዳለ ቅዱስ ዳዊት መዝሙር ፵፡፩ ፡፡
ዳግመኛም እግዚአብሔር ይራራላቸዋል ደካማውን ከብርቱ
ረዳት የሌለውን ከቀማኛ እጅ ያድናቸዋል ከግፍና ከነፍስ
ጭንቀት ይሠውራቸዋል፡፡ ለሰው የሚራሩ ሰዎች ከቡራን
ናቸው፡፡ መዝሙር ፸፩፡፳ የተበደሉ ሰዎች መንግሥተ
ሰማያትን እጅ ያደርጓታልና ለተበደለ የሚራራ እናት አባት
ለሌለው እናት አባት የሚሆን ክርስቲያንም አረመኔም ቢሆን
ሁሉም የእግዚአብሔር ፍጥረት ነውና ለድኃ ሁሉ የሰጠ በቅንነት
የሚሄድ ጽድቅንም የሚያደርግ ልቦናው ተንኮል የሌለበት
በአንደበቱ ዕውነትን የሚናገር በሰውነቱ ክፋት በቃሉ ሐሰት
የማይገኝበት በባልንጀራው ላይ ክፋትን የማያደርግ ወገኖቹን
የማይዘልፍ የማይሳደብ እግዚአብሔርን የሚፈራ ሰውን
የሚያከብር ባልንጀራውን የማይከዳ ገንዘቡን በአራጣ
የማያበድር ከንጹሑ ላይ መማለጃን ጉቦን የማይቀበል ፍርድን
የማያጓድል ድሀን የማይበድል የከበረ ነው እንዳለ ሮሜ. ፩፡፲፫
ለመስጠት እጃቸውን የዘረጉ ሰዎች በሞቱ ጊዜ ከእግዚአብሔር
ዘንድ ያቀርቧቸዋል እጅ ነሥተው ሰግደው ወደዚህ ያመጧቸዋል
ዋጋቸውንም ያሰጣቸዋል በዚህ ቦታ ለዘለዓለም ደስ ብሎአቸው
ይኖራሉ አለኝ፡፡
21
ዳግመኛም የወተት ወንዝ ወዳለበት ቦታ እነማን ይኖራሉ
አልሁት፤ ከዝሙት ሰውነታቸውን ንጹሕ ያደረጉ ሴቶቸም
በድንግልና የኖሩ በሞቱ ጊዜ ወደ እግዚአብሔር ይወስዳቸዋል
ዋጋቸውንም ይሰጣቸዋል፤ በዚያው ቦታ ደስ ብሏቸው ይኖራሉ
አለኝ፤ ከዚህ በኋላ በወርቅ በዕንቁ የተሸለመች ከፀሐይ
ከጨረቃ ፪ እጅ የምታበራ ምድር አሳየኝ፤ ይህ ቦታ ለማን
ይሆናል ብዬ ልጄን ጠየቅሁት መለሰልኝ፤ አንደበቱን ከሐሜት
የጠበቀ ኩራት የሌለበት ባልንጀራውን የማያዋርድ ምክንያተ
ሐኬት የሌለበት፤ በልቡናው ቂም በቀል የማያኖር የዋህ የሆነ
እነዚህ ሁሉ በሞቱ ጊዜ ወደ እግዚአብሔር ይወስዱዋቸዋል
እጅ ነሥተው ሰግደው ያመጧቸዋል፤ የዋሃንስ ይወርስዋ
ለምድር፡፡ የዋሃን መንግሥተ ሰማይትን ወርሰው በውስጧ
ይኖራሉ፡፡ እንዳለ መዝሙር ፲፬:፪-፭ ዋጋቸውን ይህንን
ይሰጣቸዋል አለኝ፡፡
21
ዳግመኛም በዚህ ቦታ አንፃር ብዙ ሰዎች ተበትነው አየሁ በገነት
በር ብዙ ፍሬ ያለው የሚመስል ትልቅ ዛፍ አለ እነዚያ ሰዎች
ፍሬ ያለው መስሎአቸው በተራቡ ጊዜ ለመብላት ወደ ላይ
ሲወጣ ይወጣሉ፤ ወደታች ሲወርድ ይወርዳሉ ፍሬውን
አያገኙትም ይኸንን ባየሁ ጊዜ መሪር ዕንባ አለቀስኩ ልጄንም
ጠየቅሁት እሊህ ሰዎች ምንድር ናቸው፡፡ አልሁት፤ ይህስ ዕጽ
ምንድር ነው እኔ ዛፉ ፍሬ ያለው መስሎኝ ነበር እነዚህ የተራቡ
ሰዎች ፍሬውን ለመብላት ወደታች ሲወርዱ ይወርዳሉ፡፡
ወደላይ ሲወጣ ይወጣሉ ፍሬውን አላገኙትም ነገሩ ምንድር ነው
አልሁት እረሱም የነዚህን ሰዎች ኃጢአት እነግርሻለሁ አለኝ
በጾም በጸሎት የተጸመዱና በትዕግሥት ፍጹማን ቢሆኑ ለተራቡ
አላበሉም ለተጠማ አላጠጡም ለታረዘ አላለበሱም እንግዳ
አልተቀበሉም ትዕቢተኞች ኩራተኞች ናቸው አለኝ እነዚህ ቃላት
ሰውን ያስኮንናሉን ብዬ ልጄን ጠየቅሁት መለሰልኝ ከነዚህ
ከ፫ቱ ኃጢአት የበለጠ የለም ዲያብሎስም በትዕቢቱና በኩራቱ
ተዋርዷልና አለኝ፡፡ እንዲህም ብዬ ልጄን ጠየቅሁት አስከ መቼ
ድረስ ይኮነናሉ አልሁት ጻድቃን ስለእነርሳቸው
ስለሚለምኑላቸው ዳግመኛ እስከመጣ ድረስ ነው እኔም
እምራቸዋለሁ አልጥላቸውም ወደመንግሥተ ሰማያት ይገባሉ
አለኝ፡፡ ይኸንን በሰማሁ ጊዜ ልጄን አመሰገንኩት፡፡
21
ከዚህም በኃላ ወደሌላ ቦታ ወሰደኝ ከወርቅ መርከብ ላይም
አወጣኝ ወስዶም ከቤት አገባኝ ያች ቤትም ከፀሐይ ከጨረቃ
ይልቅ ታበራለች በውስጧም ብርሃኑን የሚያንፀባርቅ የግምጃ
ምንጣፍ ወሳንሳ ተነጥፎባታል የወርቅ የብርሃን አልጋ
ተዘርግቶባታል ይህች ቦታ ለማን ትሆናለች ብዬ ልጄን
ጠየቅሁት እግዚአብሔር እንድ ያደረጋቸው ባልና ሚስት
አይለያዩም ባልና ሚስት አንድ አካል ናቸው እንዳለ ማቴ. ፲፱፡፯

21
ወንድ በአንድ ሴት ሴት በአንድ ወንድ ተጠብቀው ቢኖሩ በሞቱ
ጊዜ ከዚህ ቦታ ያገባቸዋል ለዘለዓለምም ደስ ብሎአቸው
ይኖራሉ አለኝ፡፡ ከዚህ በኋላ ፬ሺ ከ፬፻ እንደ ፀሐይ የሚያበሩ
መናብርተ ብርሃን አየሁ እሊህ ማናብርት ለማን ይሆናሉ ብዬ
ልጄን ጠየቅሁት በስሜ ስለማመን የሚያስተምሩ ናቸው
አለኝ፡፡ ሁሉም ይጠሏቸዋል ሁሉም ይደበድቧቸዋል
ይገድሏቸዋል ኋላ ግን ከራሳቸው ፀጉር አንዲት አትጠፋም፡፡
በመቻላችሁ ነፍሳችሁን ታድኗታላችሁ እንዳለ ማቴዎስ ፲፡፳፪
፡፡
21
ሲርባቸው ሲጠማቸው ከሀገር ወደ ሀገር ሲሰደዱ ዓለምን የናቁ
ስለሃይማኖት ሰውነታቸውን ለሞት አሳልፈው የሰጡ ፲፪
ሐዋርያት ፸፪ አርድእት እነዚህ ሁሉ ይቀበሏቸዋል አለኝ፡፡
የቅዱሳን ሠራዊት ሁሉ የእግዚአብሔር ማደሪያው ማርያም
ሆይ እንዴት ነሽ ብለው እጅ ነሡኝ ሰገዱልኝ ከዚህ በኋላ
ወደሌላ ቦታ ወሰደኝ ከፀሐይ ከጨረቃ ይልቅ የሚያበሩ ፪፻
ቤተ ክርስቲያን አየሁ እነዚህ ለማን ይሆናሉ ብዬ ልጄን
ጠየቅሁት ለጳጳሳት ለኤጲስ ቆጶሳት ለቀሳውስት ለዲያቆናት
ለአናጎንስጢስ ለመዘምራን ይሆናሉ አለኝ ሁሉም ይገባሉ ብዬ
ጠየቅሁት አይገቡም ጥቂት ናቸው የሚገቡት አለኝ እግዚኦ
እግዚኦ እያሉ የሚዘባበቱብኝ ሁሉ ከመንግሥተ ሰማያት
አይገቡም የአባቴን ፍቃድ የፈጸሙ ይገባሉ ብዬ የተናገርኩትን
አልሰማሽምን አለኝ ማቴዎስ ፲፭:፬ ፡፡
21
ሰውነታቸውን ከዝሙት ንጹሕ ያደረጉ ከሰው ሚስት ያልሄዱ
ኩራት የሌለባቸው ትእቢት ምቀኝነት የሌለባቸው ቂም
በልቦናቸው ያላኖሩ ከአንድ ሴት ወደ አንድ ሴት ከአንድ ወንድ
ወደ አንድ ወንድ የማይሉ ቁጡና ሰካራም ያልሆኑ ለጣኦት
ያልሰገዱ በአምልኮ ባዕድ ያላመለኩ በሐሰት ያልማሉ ቤተ
ክርስቲያን የሚያዘወትሩ በንጹሕ ሆነው ሥጋዬን ደሜን
የሚቀበሉም የሚያቀብሉ ሰዎች እነዚህ ናቸው ከመንግስሥተ
ሰማያት የሚገቡ እነዚህን የነገርኩሽን ቃላት ያልፈጸሙ
መንግሥተ ሰማያት አይገቡም አለኝ፡፡
21
ከዚህ በኋላ ወደ ኢየሩሳሌም ሰማያዊት አደረሰኝ የእሳት
መጋረጃ ያለበት የብርሃን ቤተ መቅደስ አየሁ በእጁ መሰንቆ
በገና ይዞ እየመታ እንደ ፀሐይ የሚያበራ አንድ ሰው አየሁ ያም
ሰው መሰንቆ በገና ሲመታ ምድሯን ያናውጻታል ከኢየሩሳሌም
ደጁ ቆሟል እኔም በገባሁ ጊዜ ወደእኔ መጣ ማርያም ሆይ
ከሁሉ ይልቅ አንቺ የከበርሽ ነሽ ብሎ እጅ ነሳኝ ሰገደልኝ የዚህ
ሰው ስሙ ማነው፤ ብዬ ልጄን ጠየቅሁት ቅዱስ ዳዊት ነው
አለኝ ሃሌ ሉያ ብሎ ሲያመሰግን ሰምቼው፡፡ ሃሌ ሉያ ሲሉ
የሰማኋቸው በዳዊት ቃል ምስጋና ሁሉ ተነግሯልን ብዬ ልጄን
ጠየቅሁት አዎን ምስጋና ሁሉ በዳዊት ቃል ተነግሯል አለኝ
እኔም መልሼ ሃሌ ሉያ ማለት ምን ማለት ነው ብዬ ልጄን
ጠየቅሁት ዓለም ሳይፈጠር የነበረ ዓለምን አሳልፎ የሚኖር
አምላክ የተመሰገነ አምላክ ማለት ነው አለኝ ሃሌ ሉያ ቢል
ለሰው ምስጋና ይሆንለታልን ብዬ ጠየቅሁት አወን በጥቡዕ
ልቡና ሆኖ ሃሌ ሉያ ብሎ ቢያመሰግን ምስጋናው እንደ
መላእክት ይሆንለታል አለኝ ዳግመኛም መለስሁለት ሰው
የታመመ እንደ ሆነ ተኝቶ ቢጸልይ ኃጢአት ይሆንበታልን
አልሁት ለድውይ አይሆንበትም አለኝ፡፡ ከዚህ በኋላ ወደሌላ ቦታ
ወሰደኝ የወርቅ ልብስ ያለበት ዳርቻው የማይታወቅ እንደ
ፀሐይ የሚያበራ አገር አሳየኝ ይህ ቦታ ለማን ይሆናል ብዬ
ልጄን ጠየቅሁት ንብረታቸውን ትተው ዓለመን ንቀው ለመነኑ
ሰዎች ይሆናል አለኝ ይህችን ሀገር የሚያውቃት የለም፡፡ ካህናተ
ሰማይ አይገቡም ከበር ይቆማሉ እንጂ የባሕርይ አባቴ አብ
የሕይወት መንፈስ ቅዱስ እነገባለን አንቺም ግቢ ሀገር
ይሁንልሽ አልኝ ፫ሺ መላእክት ያገልግሉሽ አለኝ መነኮሳት ሁሉ
ይጋባሉን ብዬ ጠየቅሁት ሁሉም አይገቡም አለኝ ሰውነታቸውን
ከዝሙት ንጹሕ ያደረጉት ዓለምን ንቀው የመነኑ ደስታን
ተድላን የጠሉ ቁጡ ያልሆኑ ትዕቢት ኩራት የሌለባቸው ቂም
በልቦናቸው ያላኖሩ ሰውን ከሰው የማያጣሉ ንዝኅላል ያልሆኑ
በየጊዜው በየሰዓቱ ጸሎት የሚያደርጉ ይገባሉ አለኝ በጾም
ተጸምዶ የሚኖር መነኩሴ የሚበልጠው የለም ብሎ መጽሐፍ
የተናገረውን አልሰማሽምን ዳግመኛም ገንዘብ አግኝቶ
ከሚመጸውት መነኩሴ ገንዘብ የሌለው በትምህርትና በጸሎት
ተጸምዶ የሚኖር መነኩሴ ይበልጣል ዳግመኛም ጳውሎስ እኔ
በዓለም ዘንድ ምውት ነኝ ዓለምም በኔ ዘንድ ምውት ናት
እንዳለ፡፡
21
ይኸንን ሁሉ የፈጸመ መነኩሴ ከመንግሥተ ሰማያት ይገባልን
ብዬ ብጠይቀው የማይገቡትን እነግርሻለሁ አለኝ ትዕቢተኞች
ኩራተኞች ሴሰኞች ባልንጀሮቻቸውን የሚጠሉ ባንደበታቸው
እራሳቸውን ከፍ ከፍ የሚያደርጉ መነኮሳትም ሆነው ተሾመው
የሚገዙ የሚነዱ በፈረስ በበቅሎ የሚሄዱ ከቆብ በኋላ
የሚሰስኑ ለሆዳቸው የሚገዙ አለልክ የሚበሉ የሚጠጡ ሁል
ጊዜ ዛሬ ዓመት በዓል ነው እያሉ ለመብል የሚዘጋጁ እነዚህ
መንግሥተ ሰማያት አይገቡም አለኝ ዳግመኛም ነይ ወደ
ምዕራብ እንሂድ የኃጥአን ነፍስ የሚኖሩበትን አሳይሻለሁ አለኝ
ወስዶ በሰማይና በምድር ዳር ከባሕር ዳርቻ አደረሰኝ የእሳት
ባሕር ያለበት የገሃነም ቦታ አሳየኝ ይህ ቦታ ለማን ይሆናል ብዬ
ልጄን ጠየቅሁት በመልካም ግብር ያልተገኙ በኃጢአት የኖሩ
ቦታቸው ይህ ነው አለኝ በዚያ በባሕር ውስጥ ብዙ ሰዎች
ከጉልበታቸው ድረስ ከእንብረታቸው ድረስ ከደረታቸው ድረስ
ከአንገታቸው ድረስ ከከንፈራቸው ድረስ ከእራሳችው ድረስ
የእሳት ባሕር ያጠለቃቸው አየሁ ከጉልበታቸው ድረስ
ያጠለቃቸው እነማን ናቸው ብለው በ፫ ጊዜያት ጸሎት የማይዙ
ናቸው አለኝ፡፡ ከእንብረታቸው ድረስ ያጠለቃቸው እነማን ናቸው
አልሁት ከቤተ ክርስቲያን ውስጥ ዋዛ ፈዛዛ የሚጫወቱ ናቸው
አለኝ ከደረታቸው ድረስ ያጠለቃቸው እነማን ናቸው ብለው
ከቆረቡ በኋላ እህል ውሀ ሳይቀምሱ የሚናገሩ ናቸው አለኝ
ከአንገታቸው ድረስ ያጠለቃቸው እነማን ናቸው ብለው
ባልንጀሮቻቸውን የሚያሙ ናቸው አለኝ ከከንፈራቸው ድረስ
ያጠለቃቸው እነማን ናቸው ብለው ባልንጀራውን እንግደል
የሚሉ ናቸው አለኝ፡፡ ከራሳቸው ድረስ ያጠለቃቸው እነማን
ናቸው ብለው ከጽቅረ ቤተ ክርስቲያን ሴት የሚተኙ ናቸው
አለኝ፡፡ ከዚህም በኋላ ከሥር እስከ ጫፍ ከጫፍ እስከ ሥር
ድረስ በ፭ ሺህ ዓመት የማይደረስ ትልቅ ገደል አሳየኝ ያንዱ
ነፍስ ባንዱ ነፍስ ላይ ሲወድቅ አየሁ እኔም ምንድር ናቸው ብዬ
ልጄን ጠየቅሁት ባባታቸው በወንድማቸው በልጃቸው
በባልንጀራቸው ሚስት የሚሰስኑ ናቸው አለኝ ሴት አራስ ሆና
ወይም መርገሟ በመጣ ጊዜ በሩካቤ ሥጋ የሚገናኙና እንስሳን
ምድርን ሰንጥቀው የሚያወስቡ ወንዱንም በግብረ ሰዶም
የሚያመነዝሩ ካህን ሆኖ ከሌላ ሴት የካህኑም ሚስት ከሌላ
ወንድ ቢሄዱ እነዚህ ሁሉ የኩነኔ ቦታቸው ይህ ነው አለኝ ከዚህ
በኋላ ሌላ ቦታ አሳየኝ ፬ መላእክተ ጽልመት ተሸክመው
ወስደው በእሳት አልጋ አስቀመጠው በእሳት ፍላፃ ሲነድፉት
የእሳት ውሀ ሲአፈሱበት ፩ ሽማግሌ ሰው አየሁ ባየሁትም ጊዜ
ብዙ አለቀስሁ ይህ ሰው ማነው ብዬ ልጄን ጠየቅሁት ጳጳስ ነው
አለኝ ኃጢአቱንም እነግርሻለሁ አለኝ፡፡ የቤተ ክርስቲያንን ሥነ
ሥርዓት አልተከተለም በሕጌ ተጠብቆ አልኖረም ሥጋዬን
ደሜን ያረከሰ ነው ዘመኑንም በዝሙት የፈጸመ ነው ዳግመኛ
እንግዳ አልተቀበለም ለተራቡ አላበላም ለተጠማ አላጠጣም
ለታረዘ አላለበሰም የታመመ አልጠየቀም ያዘኑትን አላረጋጋም
የታሠሩትን አላስፈታም ስለዚህ የዘለዓለም ቦታው ይህ ነው
አለኝ፡፡ ከዚህ በኋላ ፬ መላእክተ ጽልመት በእሳት መንዶ
እየደበደቡ ከእሳት ባሕር ሲጨምሩት ፩ ታላቅ ሰው አየሁ፡፡ ይህ
ሰው ማነው ኃጢአቱስ ምንድር ነው ብዬ ጠየቅሁት፡፡ ሊቀጳጳስ
ነው ኃጢአቱን እነግርሻለሁ አለኝ ፩ነቴን ፫ነቴን ለሕዝብ
አላስተማረም እራሱን ወዳድ የግል ጥቅሙን ፈላጊ ነገሥታትን
መኳንንትን አይመክርም ፍርድ ሲጓደል ድሀ ሲበደል ዳኞችን
አይገሥጽም አያስተምርም ስለዚህ የዘለዓለም ኩነኔው ይህ ነው
አለኝ፡፡
21
ከዚህ በኋላ የመለኮትን ሥጋ ስትበላ ትራባለህን የመለኮትን ደም
ስትጠጣ ትጠማለህን ብለው በአፉ እሳት ሲያጎርሱት እሳት
ሲያጠጡት መላእክተ ጽልመት ሲጎትቱት አንድ ሰው አየሁ ይህ
ሰው ማነው ኃጢአቱስ ምንድር ነው አልሁት ቄስ ነው
ኃጢአቱንም እነግርሻለሁ አለኝ በክህነት ሥራ አልኖረም
ሰውነቱንም ንጹሕ አላደረገም ዘመኑንም በሳቅ በጨዋታ
የፈጸመ ነው የዘለዓለም ኩነኔው ይህ ነው አለኝ፡፡
21
ዳግመኛም መላእከተ ጽልመት ፊት ፊቱን እየደበደቡ በግምባሩ
ሲያዳፉት መላሱን በእሳት ምላጭ ቆርጠው በአፉ ደም ሲዘነብ
ወደ እሳት ባሕርም ሲጨምሩት አንድ ሰው አየሁ ይህ ሰው
ማነው ኃጢአቱስ ምንድር ነው ብዬ ልጄን ጠየቅሁት መለሰልኝ
ዲያቆን ነው አለኝ ኃጢአቱስ ምንድር ነው ብዬ ጠየቅሁት
ኃጢአቱንም እነግርሻለሁ አለኝ በሕጌ አልኖረም ሥጋዬን ደሜን
በንጹሕ አላዘጋጀም ቤተ ክርስቲያን አልወደደም ለግብረ
ተልእኮ አልተፋጠነም ድሀ ቢሞት አልቀበረም ኩሩ ትዕቢተኛ
ነው አለኝ ከዚህ በኋላ ብዙ የተበታተኑ ሰዎች በእሳት መካከል
አየሁ እነዚህ እነማናቸው ብለው በፀሐይ በጨረቃ በከዋክብት
በዕንጨት በድንጋይ የሚያመልኩ ለዛር ለቃልቻ ለጠንቋይ
የሚደግዱ ናቸው ስለዚህ ኩነኔያቸው ለዘለዓለም ይህ ነው አለኝ
ከዚህ በኋላ በእሳት ዛፍ ላይ የተሰቀሉ ብዙ ሰዎች አየሁ ምንድር
ናቸው ብዬ ልጄን ጠየቅሁት (ብዕልን) ክብርን የወደዱ ሀብት
ገንዘብ እያለቸው ለተራበ የማይሰጡ የማይመፀውቱ ድሆቸን
የሚበድሉ ባለጠጎች ናቸው ከመከራ ሥጋ ከመከራ ነፍስ ይድቃሉ
ስለዚህ ለዘለዓለምም ቦታቸው ይህ ነው አለኝ፡፡
21
ከዚህ በኋለ በእሳት ሰንሰለት አንገታቸውን ታስረው ጨለማ
የለበሱ ሴቶች አየሁ እነማን ናቸው ብዬ ልጄን ጠየቅሁት እናት
አባቶቻቸው በሕግ ሳያጋቧቸው ድንግልናቸውን ለማንም በዱር
በጫካ የሚሰጡ የሚሰስኑ ክብረ ንጽሕናቸውን የሚያጎድፉ
ናቸው ስለዚህ ኩነኔአቸውም ለዘለዓለም ይህ ነው አለኝ፡፡
21
ከዚህ በኋላ ልቅሶ ጥርስ ማፋጨት ከአለበት ገሃነመ እሳት
እጃቸውን እግራቸውን ታስረው በእሳት ግንድ ተሰቅለው ብዙ
ሰዎች አየሁ እነማናቸው ብዬ ጠየቅሁት የሰው ገንዘብ የሚበሉ
እንደልባቸው የሚናገሩ በዚህ ዓለም ያላግባብ የከበሩ ወይም
የበለጸጉ የሚገዙ የሚነዱ ብዑላን ነገሥታት መኳንንት ናቸው
ለዘለዓለም የኩነኔያቸው ቦታ ይህ ነው አለኝ፡፡
21
ከዚህ በኋላ የእሳት ውሾች የእሳት እባቦች የእሳት አንበሶች
እግራቸውን እጃቸውን ሲሰብራቸው በእሳት ዛፍ ላይ ተሰቅለው
ብዙ ሰዎች አየሁ እነማናቸው ብዬ ብጠይቀው ከቆብ በኋላ
የሚሰስኑ መነኮሳት ናቸው ሴቶችም በፀነሱ ጊዜ መድኃኒት
እየጠጡ የሚያስወርዱ ናቸው እነኛም ሕፃናት መልካምም ሆነ
ክፉ ብንሠራ ምነው ባደግን አለጊዜያችን አጠፉን ብለው አቤት
አቤት እያሉ ይጮሁባቸዋል አባቴ ግን መልአኩን ሕፃናቶቹን
ወደ መልካም ቦታ ውሰዳቸው ይለዋል እናቶቻቸውም
ለዘለዓለም ኩነኔያቸው ይህ ነው አለኝ በጥቡዕ ልቦና ነስሓ ቢገቡ
አትምራቸውምን አልሁት እምራቸዋለሁ አለኝ ቀሳውስቱም
የነፍስ ልጆቻቸውን መክርው ተቆጥተው ንስሓ ግቡ
አይሏቸውም እነደ ፈሌ እንደ (ፈላ) ይሆናሉ አለኝ፡፡
21
ከዚህ በኋላ እህል እንዳይበሉ ውሀ እንዳይጠጡ ተክልክለው
በእሳት ግንድ ታስረው ብዙ ሰዎች አየሁ እነማን ናቸው ብዬ
ብጠይቀው እንዲህ አለኝ ሴት በመርገም ጊዜዋ ሆና በሩካቤ
ሥጋ የተገናኙ ዓርብ ረቡን ፵ ጾም ሁዳዴን የማይጾሙ የኩነኔ
ቦታቸው ይህ ነው አለኝ ንስሓ ቢገቡ አትምራቸውም ብለው
እምራቸዋለሁ አለኝ፡፡
21
ከዚህ በኃላ በእሳት መካከል እጃቸውን እግራቸውን የተቆረጡ
ሰዎች አየሁ ምንድር ናቸው ብዬ ጠየቅሁት ለሰው ክፉ የሚጥሩ
የሚጽፉም የሰው ገንዘብ የሚሰርቁ የሚነጥቁ የሚዘርፉ
ጉልበት እያላቸው ሠርተው የማይበሉ አታላዮች ኪስ
አውላቂዎች የሰው ቤት በቀን መዝጊያ የሚሰብሩ ሌሊት
ግድግዳ የሚሠረሥሩ ለሰው ነፍስ የማይሳሱ ርኀራኄ የሌላቸው
በገንዘብ እየተገዙ የሰው ነፍስ የሚያጠፉ ዓይናቸውን በስው
ሀብት ላይ የሚያሳርፉ በጧት ወደ መሸታ ቤት የሚገሠግሡ
በብዙ ድካም ያገኙትን ገንዘብ ቤተሰባቸውን በድለው ለመሸታና
ለዝሙት የሚያጠፉ ሰካራሞች አጭበርባሪዎች ናቸው የኩነኔ
ቦታቸውም ለዘለዓለም ይህ ነው አለኝ፡፡
21
ከዚህ በኋላ በእሳት ልጓም ተለጉመው በእሳት ሜንዶ ፊት
ፊታቸውን ሲደበድቧቸው አየሁ ምንድር ናቸው ብዬ ልጄን
ጠየቅሁት ባልንጀራቸውን የሚሰድቡ የሚያዋርዱ ምቀኞች
ተንኮለኞች ሟርተኞች ሰላቢዎች ተዕቢተኞች ሰውን
አሽሟጣጮች ናቸው አለኝ፡፡
21
ዲያብሎስም አዳምን በሰደበ ከማዕረጉ ተዋርዷልና ዳግመኛም
ጨው ባሩድ የሞላበት ጨለማ ጉድጓድ አየሁ በዚያው ውስጥ
እግራቸውን እጃቸውን የተቆረጡ ብዙ ሰዎች አየሁ፤ ምንደር
ናቸው ብዬ ልጄን ጠየቅሁት አንድነቴን ሦስትነቴን ቅድመ
ዓለም ከአብ ያለ እናት መወለዴን ድኀረ ዓለም ከሰማየ ሰማያት
ወርጄ ከድንግል ማርየም ያለ አባት ወወለዴን በሄሮደስ ቅንዓት
ከሀገር ወደ ሀገር መሰደዴን መጠመቄን መገረፌን
በመልዕልተ መስቀል መስቀሌን በቀኖት መቸንከሬን ሞቼ
መነሣቴን ከትንሣኤዬም በኋላ በ፵ኛው ቀን ወደሰማይ ማረጌን
በኃላም ይህን ዓለም ለማሳለፍ በጌትነትና በታለቅ ግርማ
መምጣቴን የማያውቁ አረመኔዎች ናቸው ለዘለዓለም
የሚኖሩበት የኩነኔ ቦታቸው ይህ ነው አለኝ፡፡
21
ከዚህ በኋላ የእሳት እባብ በአንገታቸው በአፋቸው
ተጠምጥሞባቸው ከአፋቸው የእሳት ዲኝ ሲወጣ ብዙ ሰዎች
አየሁ ምንደር ናቸው አልሁት ብዙ ክርስቲያን ሂደው ያላገለገሉ
ካህናት ናቸው ለዘለዓለም የኩነኔ ቦታቸው ይህ ነው አለኝ፡፡
21
ከዚህ በኋላ በእሳት ገመድ አስረው ራሱን ወደታች እግሩን
ወደላይ አድርገው ሰቅለው አንድ ሰው አየሁ ዳግመኛ በእሳት
ጦር ፊት ፊቱን እየወጉ ከእሳት ላይ ሲጥሉት አየሁ ይህ ሰው
ማነው ብዬ ልጄን ጠየቅሁት ቄስ ነው ኃጢአቱንም እነግርሻለሁ
አለኝ በሰንበት ዕጣን አያጥንም ንዝኅላል ትዕቢተኛ ኩራተኛ ነው
ጸሎት አያደርስም የዘለዓለም የኩነኔ ቦታው ይህ ነው አለኝ
ልጄን እንዲህ ስል ጠየቅሁት ቁርባን ምን ጊዜ ይቁረብ እሁድ
በነግህ ቀዳሚት በ፫ ሰዓት ሊቀደስ ይገባል ኦሪት ነቢያትን
ልፈጽማቸው ነው እንጂ ላሳልፋቸውና ልሽራቸው አልመጣሁም
ብሎ መጽሐፍ የተናገረውን አልሰማሽምን አለኝ፡፡
21
ቀዳሚትንም ካንዲት ቀን በቀር አልሻርኳትም ሌሎችን
ሰንበታት እንደ እሁድ ያክብሯቸው አለኝ ማለትም እንደ እሁድ
ያክብሯት ማለት ነው፡፡
21
ከዚህ በኋላ በእሳት ፍላፃ ሲነድፉት አንድ ሰው አየሁ ይህ ሰው
ማነው ብዬ ልጄን ጠየቅሁት ዲያቆን ነው አለኝ ኃጢአቱስ
ምንድር ነው ብዬ ብጠይቀው እነግርሻለሁ አለኝ፡፡
21
መሥዋዕቱን በንጹሕ አላቀረበም በሰዓቱም አላዘጋጀም
ሰውነቱንም ከኃጢአት አላነፃም ለዘለዓለም የኩነኔ ቦታው ይህ
ነው አለኝ፡፡
21
ከዚህ በኋላ ከሌላ ቦታ ወሰደኝ የእሳት ጉድጓድ አየሁ ከውስጡ
ብዙ ሰዎች ሞልተው በአንገታቸው የእሳት እባቦች
ተጠምጥሞባቸው አራት መላእክተ ጽልመት የእሳት ጦር
ሲወረውሩባቸው አየሁ ባየኋቸውም ጊዜ ብዙ አለቀስኩ እሊህ
እናማናቸው ብዬ ልጄን ጠየቅሁት መነኮሳት ናቸው በሕጌ
አልኖሩም ሥራዓቱንም አልጠበቁም መነኮሳት ነን ሲሉ
የመነኮሳትን ሥራ አይሠሩም የማይረባቸውን
የማይጠቅማቸውን ሥጋዊና ዓለማዊ ሹመት ይፈልጋሉ
ዘመናቸውንም በኃጢአት የፈጸሙ ናቸው ለዘለዓለሙ የኩነኔ
ቤታቸው ይህ ነው አለኝ፡፡
21
ከዚህ በኋላ የተዘጋጀ ታላቅ ገሃነም አየሁ ልጄም እናቴም
ማርያም ታየዋለችና ክፈቱ ብሎ የገሃነመ እሳት በር ጠባቂውን
ጠርቶ አስከፍቶ በሮቹ በተከፈቱ ጊዜ አይቼ ፈራሁ ተንቀጠቀጥኩ
ይህ ቦታ ስሙ ማነው ብዬ ልጄን ጠየቅሁት ገሃነመ እሳት ነው
አለኝ በዚህስ ውስጥ የሚኖሩ ምንድን ናቸው ኃጢአታቸውስ
ምንድ ነው አልኩት ሰው ከውሀና ከመንፈስ ቅዱስ ካልተወለደ
በቀር ወደ እግዚአብሔር መንግሥት ይገባ ዘንድ አይቻለውምና
ስለዚህ ያልተጠመቁ አረመኔዎች ናቸው የዘለዓለም ቦታቸወም
ይህ ነው አለኝ፡፡ ዮሐንስ ፫፡፭፡፡ እነዚህም በስቃይ ያሉ ሁሉ
ባዩኝ ጊዜ ማርያም አንቺ ከሁሉ ይልቅ የከበርሽ ነሽ
የማኀፀንሽም ፍሬ የከበረ ነው አንቺን ያዩ ዓይኖቻቸን የከበሩ
ይሁኑ ብለው ጮሁ እኔም ሰው ሆኖ ኃጢአት የማይሠራ የለምና
ልጄን እባክህን ማርልኝ አልሁት እርሱም ዓርብ በሠርክ
መጥተው እስከ ሰኞ ድረስ ስለአንቺ በገነት ያሳርፏቸው አለኝ፡፡
21
ይህንም በሰማሁ ጊዜ ልጄን ፈጣሪዬን አመሰገንኩት
እመቤታችን ድንግል ማርያም ይህንን ከዚህ ቀጥሎ ያለውን
ማስጠንቀቂያ ሰጥታለች እወቁ ተጠንቀቁ ሴት አራስ ሆና
በሩካቤ ሥጋ የተገናኘ በመርገሟም ሰዓት ወንድ ከሴቷ ሴቷም
ከወንድ ፈቃደኛ ሆነው ቢገናኙ ኃጢአት ይሆንባቸዋል በልቡ
ክፋት ያለበት ሰው ይህች መጽሐፍ ካለችበት ቦታ አይድረስ
መጽሐፉንም ከእንደዚህ ካለው መጥፎ ቦታ አታኑሩ ብላ
ተናግራለች፡፡
21
ዳግመኛም ስለ በዓላት አከባበር ቢቻላችሁ ፴፫ቱን ባይቻላችሁ
፭ቱን የጥር ማርያምን የየካቲት ኪዳነ ምሕረትን የግንቦት
ልደታን የሰኔ ማርያም የነሐሴ ፲፮ ፍስለታን እነዚሀን በዓላቴን
ያከበረ ይህን መጽሐፍ የፃፈ ያጻፈ ያነበበ የተረጎመ የሰማ ያሰማ
እነዚህን ሁሉ የፈጸሙ በሞቱ ጊዜ እኔ እቆምላቸዋለሁ ብላ
ለዮሐንስ ነገረቸው፡፡
21
የአምላክ ልጅ ወልደ አምላክ ለችግር አማላጅቱ እመቤታችን
ማርያም የገለጸላት ራእይ ባጭሩ እዚህ ላይ ተፈጸመ፡፡ የልጅዋ
የወዳጅዋ ቸርነት ለሁላችን ይደረግልን የእመቤታችን ረድኤት
በረከት እስከ ዘለዓለሙ ይደርብን አሜን አቡነ ዘበሰማያት፡፡
°°°°°°°
ምንጭ: መዝገበ ጸሎት ወመጽሐፈ ጸሎት ባለ ሰባ ስምንት
ከተሰኘው የጸሎት መጽሐፍ ላይ ከገጽ 591 እስከ 636
የተወሰደ ነው። በዘሪሁን እሸቱ የተዘጋጀ 20/4/2008 ዓ.ም
†† †† † † †† ††
ለአባ ሕርያቆስ ፤ለቅዱስ ኤፍሬም ፤ለቅዱስ ያሬድ ፤ ለአባ
ጊዮርጊስ ዘጋስጫ የተገለጸች ዕመቤታችን እኛንም በበረከት እና
በረድኤት ትጎብኘን ፤ ከልጅዋ ከወዳጅዋ ከመድኃኔዓለም ዘንድ
ታማልደን ፤ አሜን!!!
ወ ስ ብ ሐ ት ለ እ ግ ዚ አ ብ ሄ ር

ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ነኝ: 21

21 21 21 21 21 21 21
# ራእየ_ማርያም
21 21 21 21 21 21 21
# እመቤታችን_በጎልጎታ_ስጸ
ልይ_ልጇ_ፈጣሪዋ_ጌታችን
_አምላካችንና_መድኃኒታች ን_ኢየሱስ_ክርስቶስ_የገ
ለጸላት_ምሥጢር_ራእየ_ማ ርያም ቀርቧልና ይነበብ...
21 21 21 21 21 21 21
በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ ንዌጥን
በረድኤተ እግዚአብሔር ሕያው ራእየ ማርያም ወላዲተ
አምላክ ጸሎታ ወበረከታ የሃሉ ምስሌነ ለዓለመ ዓለም
አሜን።
21
ማርያም ለዮሐንስ እንዲህ አለችው ረቂቅ ምሥጢር በልቡናየ
የማይታወቅ ጌታዬ ፈጣሪዬ ልጄ የገለጸልኝ ምሥጢር በጎልጎታ
ስጸልይ ዐርብ ቀን በቀትር ብሩህ ደመና መጥቶ ከ፫ቱ ሰማያት
አውጥቶ አስቀመጠኝ ሁሉንም አሳየኝ ከአንቺ ከፈለገ ሰማይ
ተወልጃለሁና አንቺም ሰላምታ ይገባሻል እኔም ዕጹብ ድንቅ
ምሥጢርን እገልጽልሻለሁ አለኝ። እኔም መለስኩለት ጌታዬ
ፈጣሪዬ እንዳልህ ይሁን አልሁት ወደታች እይ አለኝ ወደ ታች
ስመለከት ዓለምን ሁሉ አየሁ ሰብእሰ ከንቶ የመሰል
መውዋዕሊሁኒ ከመ ጽላሎት የኃልፍ ሰው ከንቱ ነገርን
ይመስላል ዘመኑም እንደ ጥላ ያልፋል ይጠፋል ነፍሱም
ከሥጋው ትለያለች ለዘለዓለም አትኖርም የምትኖርበትም
አይታወቅም መዝሙር ፻፵፫:፬
21
እንግዲህ ሰው ሁሉ በከንቱ ነውን አልሁት እሱም መልሶ ዳዊት
ያለውን አልሰማሽምን አለኝ ሰው ሁሉ በከንቱ ለምን ይኮራል
ዕለት ዕለትስ ለምን ኃጢአት ይሠራል ዳግመኛስ ጢስ ታይቶ
እንደሚጠፋ የሰውም አኗኗር እንዲሁ ነው አለኝ መዝሙር
፶፩:፩። እኔም መለስሁለት የጻድቃን ነፍስ ከሥጋዋ ስትለይ
አሳየኝ አልሁት። መለሰልኝ ጥቂት ቆዪ አሳይሻለሁ አለኝ።
ከዚህ በኋላ ፲፪ መላእክተ ብርሃን በእጃቸው የወርቅ መስቀል
የወርቅ ጥና ይዘው በደረታቸው የእግዚአብሔርን ምልክት
አድርገው የጻድቃንን ነፍስ ለመቀበል ሲወርዱ አየሁ።
ወደዚያች ነፍስ መላእክተ ጽልመትም መጥተው መረመሯት
ምክንያትም አጥተው ሄዱ መላእክተ ብርሃን ግን ፫ ጊዜ
ጋርደው ከሥጋዋ ስትለይ እንዲህ አሏት ደስ ሲያሰኛት
ሲመክሩዋት አንቺ ንጽሕትና ብርሕት ነፍስ ሆይ ደስ ይበልሽ
ዕፅፍ ድርብ ደስታ ይገባሻል ነይ ውጪ ወደ አገርሽ እንሂድ አሏት
አንቺ ንጽሕት ብርህት ነፍስ ሆይ ቅዱስ ዳዊት የዕድሜዬን
መጠኑን ንገረኝ በእኩሌታው ዕድሜዬ አትውሰደኝ ያለውን
አስተውለሻልና። መዝሙር ፻፩:፳፬።
21
ዳግመኛም ጳውሎስ ዛሬ የሚገዙ የሚነዱ ኋላ እንዳልገዙ
እንዳልነዱ ይሆናሉ ዛሬ የሚበሉ የሚጠጡ ኋላ እንዳልበሉ
እንዳልጠጡ ይሆናሉ። የዚህም ዓለም ንብረት ብልጽግና ኃላፊ
ጠፊ መሆኑን አስበሽ ዲያብሎስን ድል ነስተሽዋልና ዓለምንም
ንቀሽ ጉዱፍ እንደሆነ እንደመርገም ጨርቅ ጥለሽዋልና
የማያረጀውን የማይጠፋውን መርጠሻልና ለዘለዓለም የሚኖር
መንግሥተ ሰማያትን ወደሻልና ነይ ወደ ፈጣሪሽ እንሂድ አሏት
የዚያን ጊዜ ሌሎች መላእክተ ብርሃን ወረዱ የወርቅ ዝርግፍ
ዕንቁ የብርሃን ቀጸላ ፲፪ የብርሃን መብራት ይዘው ከብርሃን
አክሊሎች ጋር ወረዱ ብርሃናቸውም ከፀሐይ ከጨረቃ ፯ እጅ
ያበራል ክርስቶስም ከ፭ኛው ሰማይ ድረስ መጣ እኔም ያችን
ነፍስ ለመገናኘት ሄድኩ መላእክተ ብርሃን ዕልል አሉ እኔም
ከእርሳቸው ጋር ዕልል አልኩ ምእመናን ሁሉ በእጃቸው
አጨበጭበው በቃላቸው ዕልል ብለው ለእግዚአብሔር
ምሥጋና አቀረቡ ዳግመኛ ክብር ሞቱ ለጻድቃን በቅድመ
እግዚአብሔር ፊት የከበረ ነው እንዳለ መዝሙር ፻፲፭:፮።
21
ያችን ነፍስ ወደ እግዚአብሔር አቀረቧት ነፍስ ሆይ ደስ ይበልሽ
ደስታ ይገባሻልና ወደ ፈጣሪሽም እጅ ንሺ ስገጂ አሏት እርሷም
ሰገደች ፈጣሪዋንም እጅ ነሳች አስቀድሞ ይጠብቃት የነበረው
መልአክ እግዚአብሔርን እንዲህ አለው አቤቱ የዚያች ነፍስ
ምግባሯን ነገርኩት እንደ አውነተኛነቷ አክብራት አለው
በእውነት የሚፈርድ ጌታም እንደፈጠርኩሽ ንጽሕት ሆነሽ
የኖርሽ ነፍስ ሆይ እንዴት ነሽ ቃሌን ያላቃለልሽብኝ
ያላበላሸሽብኝ እኔም አላበላሽሽም ሥጋሽንም በጊዜ ምጽአት
አነሣዋለሁ በክብር ከእኔ ዘንድ ትኖሪያለሽ ብሎ በሰው እጅ
ያልተፈተለ ከወተት የነፃ ነጭ ልብሽ ሰጣት ከፀሐይ ከጨረቃ ፯
እጅ የሚያበራ ፫ አክሊለ ብረሃን አቀዳጃት ሚካኤልን ጠርቶ
ንሳ ወደ ገነት ውሰዳት በአብርሃም በይስሐቅ በያዕቆብ አጠገብ
ተቀምጣ በደስታ ትኑር ዳግመኛ እስክመጣ ድረስ ያንጊዜ
ዋጋዋን እከፍላታለሁ ከቅዱሳን ጋር ትቆየኝ አለው፡፡
21
መላእክተ እግዚአብሔርም ይህን ፍርድ በሰሙ ጊዜ አቤቱ
ጌታችን ፍርድህ የተቃና አገዛዝህም በእውነት ነው ብለው ደስ
አላቸው እኔም እንደነሳቸው ደስ አለኝ ያችንም ነፍስ ሸኙዋት
ወደ ገነትም አደረሷት ጻድቃን ሰማዕታት አብርሃምና ይስሐቅ
ያዕቆብ አባቶቻችን እናቶቻችን ባሉበት ቅዱስ ዳዊት
በመካከላቸው በገናውን እየመታ ተቀበሏት እንዲህም አሉዋት
ንጽህትና ብርሕት ነፍስ ሆይ ለዘለዓለም የሚኖር ደስታ ሕይወት
ወደ አለበት ነይ ውጪ አሏት ያችም ነፍስ ከነሱ ጋራ ሄደች፡፡
21
እኛም ከዚህ በኃላ ተመለስን እነኛም እንዲህ እያሉ ሃሌ ሉያ
ቅዱስ ቅዱስ ቅዱስ እግዚአብሔር ፀባኦት ፍጹም ምሉዕ
ሰማያት ወምድር ቅዱሳተ ስብሐቲከ ዳግመኛም ስብሐት ለአብ
ስብሐት ለወልድ ስብሐት ለመንፈስ ቅዱስ እያሉ ፈጣሪያቸውን
አመሰገኑ እኔም ልጄን እንዲህ ስል መለስሁለት የኃጥአን ነፍስ
ከሥጋዋ ስትለይ አሳየኝ አልሁት ጥቂት ቆዬ አሳይሻለሁ አለኝ
ወደታችም አየሁ መላእክተ ብርሃንና መላእክተ ጽልመት ወደ
ኃጥእ ነፍስ ሄዱ መላእክት ብርሃን ቀርበው ያቺን የኃጥእ ነፍስ
መረመሩዋት መልካም ነገር አጥተው ሄዱ ያን ጊዜውን
መንፈስ ቅዱስ ተለያት የገሃነም እሳት ሹም ቆሞ ከሆዷ ገባ ያቺ
ነፍስ በብዙ ጭንቅ ከሥጋዋ ተለየች ሞቱ ለኃጥእ ጽዋግ የኃጥእ
ሞት የከፋ ነው እንዳለ መዝሙር ፴፫:፳፩
21
በክፋቷ በእሳት በትር በእሳት አለንጋ እየደበደቡ እያገረፉ ከሥጋዋ
ለይተው ወሰዷት አንቺ ነፍስ ወደ ማን ትሄጂ እግዚአብሔርን
አታውቂ እያሉ ሲደፏት ሲያዳፏት ወሰዷት ያቺም ነፍስ ኩነኔ
መኖሩን አላውቅም ነበር አውቄ ቢሆን ልልበስ ልብላ ልጠጣ
አልልም ነበር አሁንም ስለእግዚአብሔር ስለእግዝእትነ
ማርያም ደከመኝ አሳርፉኝ አለች ፈጣሪሽንና ማርያምን የካድሽ
ወንጀለኛ አናሳርፍሽም አሏት ሁለተኛም ስለ እግዝእትነ
ማርያም ደከመኝ አሳርፉኝ አለች ማርያም ወዴት
ታውቂያታለሽ እያሉ ሲወስዷት አይቼ ብዙ አለቀስኩ ብዙም
አዘንኩ ልጄን እንዲህ አልኩት ሰው ሆኖ የማይበድል እንጨት
ሆኖ የማይጤስ የለምና እባክህ ማርልኝ አልኩት፡፡
21
ልጄም መለሰልኝ አትዘኝ እናቴ ሆይ ሰው በምድር መልካም
ግብር ካልሰራ መማር አይገባውም አለኝ፡፡ ያን ጊዜ ልቅሶ
አበዛች ይህች ነፍስ ስለእግዝእትነ ማርያም ጥቂት አሳርፉኝ
እያለች ጩኸቷን ማብዛቷን በሰማሁ ጊዜ መሪር ዕንባ
አለቀስሁ ልቅሶዬንም ልጄ በሰማ ጊዜ ስለ እናቴ ስለ ማርያም
ብላችሁ ጥቂት አሳርፏት ይህቺን ነፍስ አለ ያቺንም ነፍስ ጥቂት
አሳረፏት፡፡ ከዚያም በኃላ አንቺ ጎስቋላ ነፍስ ወዴት ትሄጃለሽ
መግቢያሽ ወዴት ነው ወዮለሽ ወዮታ አለብሽ እያሉ ወሰዷት
ከኃጥእም ቦታ አደረሷት አቡሃ ለሐሰት የሐሰት አባት ሐሰት
የሚያናግር ሰው የሚያሳማ ዝሙት የሚያሰራ ወደ መሸታ ቤት
የሚያኬድ ዘፈን የሚያስወድድ ነፍስ የሚያስገድል ሰይጣን ወደ
እርስዋ ከጭፍሮቹ ከመላእክተ ጽልመት ጋር ተሸቀዳደመው
ሄዱ መረመሯትም ወገናቸው ሆና አገኙዋት አንቺ ጎስቋላ ነፈስ
ወደ ማን ትሄጂ ወደ መንግሥተ ሰማያት ትገቢ ትወጃለሽን
እያሉ ተዘባበቱባት ሠራዊተ መላእክት ካሉበት አደረሷት
በመካከላቸው ብትቆም ይህቺን የተረገመች ነፍስ ውሰዱልን
አሉ ሽታዋ አስቸገረን ብለው ጮሁ፡፡
21
ከዚህም በኃላ አንቺ ርግምት ነፍስ ወዮልሽ ወዮታ አለብሽ እያሉ
ወደ ሰማይ አወጧት ከእግዚአብሔር ፊት አደረሷት የፈጠረሽ
እግዚአብሔር ይህ ነው ስገጂ እጅ ንሺ አሏት ያችም ነፍስ
ሰገደች እጅም ነሳች ቀድሞ ይጠብቃት የነበረው መልአክ
ውቃቢ እቤቱ ጠብቅ ያልከኝ ነፍስ ይህቺው ብሎ ለጌታ
አቀረባት ጌታም መልሶ ነፍስ ሆይ ለምን በደልሽኝ ፀሐይና
ጨረቃን እያፈራረቅሁ ሳወጣ ከጻድቃን አለየሁሽ እህልን
ለምግብ ወሀን ለመጠጥ ዕፅዋትን አትክልትን ፈጠርኩልሽ
የነፍስሽን መድኃኒት መልካም ግብር መሥራት ለምን እረሳሽ
ቢላት እኔ ኩነኔ መኖሩን አላወቅም ነበር አውቄ ቢሆን ልብላ
ልጠጣ ልልበስ አልልም ነበር፡፡ ጌታም ካህናትና መጻሕፍት
ካንቺ ዘንድ አልነበሩምን ለምን አልሰማሻቸውም ለነፍስሽ
ስንቅ መልካም ግብር ለምን አልሰራሽም ብሎ ቢጠይቃት
እርሷም የምትመልሰው ብታጣ ዝም አለች፡፡ ከዚህ በኃላ ጌታ
በምድር መልካም ግብር ያልሰራ መማር አይገባውምና ንሱ
ወደ አባቷ ወደ ሰይጣን ውሰዷት ለገሃነመ እሳት ሹም
ለጥልምያኮስ ስጧት አለ ዳግመኛም እስክመጣ ድረስ በሲኦል
በጨላማ ቤት ትኑር አለ ይሀንንም በሰማች ጊዜ ጮኸች ወይኔ
ሳልፈጠር በቀረሁት ይሻለኝ ነበር የተወለድኩባት ቀን ርጉም
ትሁን ብላ አለቀሰች ያች ነፍስ ብታለቅስ ሁላችንም አለቀስን
መላእክትም አክሊላቸውን አውርደው አለቀሱ፡፡
21
ቅዱስ ዳዊትም ቦኑ ለከንቱ ፈጠርኮ ለሰብእ በውኑ የሰውን ልጅ
ለከንቱ ፈጥረኸዋልን እንዳለ መዝሙር ፹፰፡ ፵፯ ጌታም
ወምንት ይበቁዖ ለሰብእ ለእመ ኩሎ ዓለመ ረብሀ ወነፍሶ ኅጎለ
ሰው ሁሉ ዓለምን ቢገዛ ቢነዳ ነፍሱን ካጣ ምን ይጠቅመዋል
እንዳለ ማርቆስ ፰፡፴፮ ለዚያች ነፍስ ሁላችንም አለቀስን፡፡
21
ከዚህ በኃላ ልጄ እንዲህ አለኝ ወደ ገነት እንሂድ አለኝ ሂጄም
ጻድቃን ሰማዕታት ደናግል መነኮሳት መልካም ሰዎች
የሚኖሩበትን አየሁ ወደላይ አወጣኝ ሥሩ የማይታይ ከትልቅ
ገደል አደረሰኝ ከዚያው ፯ ብርሃናትን ከፀሐይ ከጨረቃ ፲፪ እጅ
የሚያበሩ አየሁ ፩ አረጋዊ (ሽማግሌ) ሰው መጥቶ ማርያም
ሆይ አንቺ የከበርሽ የማኀፀንሽም ፍሬ የከበረ ነው አንቺን ያዩ
ዓይኖቼ የከበሩ ናቸው ብሎ እጅ ነሳኝ ልጄን ይህ ሰው ማነው
ብየ ጠየቅሁት ሄኖክ ነው አለኝ፡፡
21
ዳግመኛም እንደሱ አንድ ሰው መጥቶ እጅ ነሳኝ ልጄን ይህስ
ሰው ማነው አልሁት ኤልያስ ነው አለኝ ከዚህ በኃላ ከታች አስከ
ላይ በወርቅ ቀለም የተጻፈ ዓምድ ወርቅ አየሁ ቁመቱ
በመላኩ ክንድ ፲፭ ይሆናል ጽሕፈቱም ረቂቅ ነው እኔም
ይኸንን አይቼ ልጄን ጠየቅሁት ይህ ረቂቅ ጽሕፈት የተጻፈበት
ዓምድ ወርቅ ምንድነው አልሁት የጻድቃን ስማቸው ነው አለኝ
የፊታቸው መልክ ብቻ ነው የተጻፈው ብዬ ብጥይቅ አይደለም
ሁለንተናቸውም ተጽፏል እንጂ አለኝ ሳይወለዱ ነው ከተወለዱ
በኃላ ብለው ካባታቸው ከአዳም በፊት ተጽፈዋል አለኝ፡፡
21
ዳግኛም በዓምደ ወርቅ ከተጻፈው ጽሕፈት የሚበልጥ
የተጻፈበት የእሳት ዓምድ ወርቅ አየሁ በዚያ በእሳት ዓምድ ላይ
የተጻፉ እነማን ናቸው ብለው ኃጥአን ናቸው አለኝ ሳይፈጠሩ ነው
ከተፈጠሩ በኃላ የተጻፈው ብለው ለዚህ ለሥቃይ አስቀድመው
የተጻፉ ናቸው ብሎ አለኝ መጽሐፍ ያለውን አልሰማሽምን አለኝ
ቦ እለ ተሐርዩ እምከርሠ እሞሙ እመሂ ለሢመት ወእመሂ
ለነዲ ከእናታቸው ማኀፀን የተመረጡ ለሹመትም ሆነ ለድኀነት
አሉ እንዳለ ቅዳሴ አትናቴዎስ ቁ. ፻፲፫።
21
ከዚህ በኃላ ወደሌላ ቦታ ወሰደኝ ከፀሐይ ከጨረቃ ፲፪ እጅ
የምታበራ አገር አየሁ በየሰዓቱ ፼ ፼ የሚያፈራ ብዙ ፍሬ ያለው
ብዙ አትክልትም አየሁ ዳግመኛም ተምር ገውዝ ለውዝ ሎሚ
ትርንጎ ፬፼ ከ፷፯ አትክልት መዓዛቸው ልቦና የሚመስጥ በዚያ
ቦታ አየሁ ልጄንም ጠየቅሁት ይህ ቦታ ለማን ይሆናል አልሁት
ወንድ በ፩ሴት ሴት በ፩ ወንድ ተወስነው በንጽሕና ቢኖሩ በሞቱ
ጊዜ መኖሪያቸው ይህ ነው በልቡናቸው ንጹሕ የሆኑ ሰዎች
እግዚአብሔርን ያዩታል ወደ እግዚአብሔርም ይወስዱዋቸዋል
እንዳለ ማቴዎስ ፭:፰።
21
ከዚህ በኃላ በዚህ ቦታ አንፃር የወይን ወንዝ ወደአለበት ቦታ
ወሰደኝ በዚያም ቦታ ደጋጎች አባቶቻችን አዳም አቤል ሴት
መላልኤል ቃይናን ያሬድ አልፋስክድ የቀደሙ አባቶቻችን ሁሉ
አሉበት መጀመሪያ አባታችን አዳም መጥቶ ማርያም ሆይ
እንዴት ነሽ አለኝ አንቺን ያዩ ዓይኖቼ ንዑዳት ክቡራት ናቸው
አለኝ አቤልም መጥቶ አንዴት ነሽ አለኝ የቀደሙ አባቶቻችን
ሁሉ እየመጡ መልካሚቱ ርግብ ማርያም ሆይ እንዴት ነሽ
አንቺን ያዩ ዓይኖቻችን ንዑዳት ክቡራት ናቸው ብለው እጅ ነሡኝ
ሰገዱልኝ ከዚህ በኃላ የመዓር ወንዝ ወዳለበት ወሰደኝ በዚያው
ቦታ ሙሴ አሮን አሞጽ ኢሳይያስ ናሆም ኤርሚያስ ሶፎንያስ
ነቢያት ሁሉ ኤልሳቤጥ ራሔል ሣራ ርብቃ የጸደቁ ሴቶች ሁሉ
አሉ የነቢያት አለቃ ሙሴ መጥቶ እጅ ነሣኝ ሰገደልኝ ፀምር
ፀዐዳ ማርያም ሆይ እነዴት ነሽ አለኝ አንቺን ያዩ ዓይኖች
ንዑዳት ክቡራት ናቸው አለኝ ነቢያትም ሁሉ መጥተው እጅ
ነሡኝ ሰገዱልኝ ጽርሕ ንጽሕት ማርያም ሆይ አንቺን ያዩ
ዓይኖቻችን ንዑዳት ክቡራት ናቸው ብለው እጅ ነሡኝ ሰገዱልኝ
እናቴ ሔዋን መጥታ እንዴት ነሽ አለችኝ ጽርሕት ንጽሕት
እንዴት ነሽ አለችኝ ጽርሕት ንጽሕት ማርያም ሆይ አንቺን ያዩ
ዓይኖቼ ንዑዳት ክቡራት ይሁኑ አለችኝ ክቡራት ቅዱሳት
አንስትም ሁሉ መጥተው እጅ ነሡኝ ሰገዱልኝ የእግዚአብሔር
ማደርያ እንዴት ነሽ አሉኝ ከዚህ በኃላ የወተት ወንዝ ወደአለነት
ቦታ ወሰደኝ በዚያ ቦታ ሄሮድስ የገደላቸው ፲፬፼ ከ፬፻ ሕፃናት
አሉ እነሱም ባዩኝ ጊዜ መጥተው እጅ ነሡኝ ሰገዱልኝ የደናግል
መመኪያቸው ማርያም ሆይ አንቺ ከሁሉ ይልቅ የከበርሽ ነሽ
አንቺን ያዩ ዓይኖቻችን የከበሩ ይሁኑ ብለው እጅ ነሡኝ
ሰገዱልኝ፡፡
21
ከዚህ በኃላ የወይን ወንዝ ወደአለበት ቦታ የሚኖሩ እነማናቸው
አልሁት ባልንጀራቸውን እንደራሳቸው ማለት እንደ ነፍሳቸው
የሚወዱ ለተራበ ያበሉ ለተጠማ ያጠጡ ለታረዘ ያለበሱ ሰዎች
በሞቱ ጊዜ ወደ እግዚአብሔር ይወስዳቸዋል እጅ ለመንሳት
ለመስገድ ወደፈለገ ሰማይ ሲወስዳቸው ቅዱሳን መጥተው
ይቀበሏቸዋል ዓለምን ድል ነሥተዋልና ዲያብሎስን
አሸንፈዋልና መልካም ግብር በመሥራት በእውነት ጎልማሶች
ናቸውና አገራችሁ ግቡ እንደኛ ደስ ይበላችሁ ይሏቸዋል አለኝ፡፡
21
ዳግመኛም ልጄን የማር ወንዝ ወደአለበት ቦታ እነማን
ይኖራሉ አልሁት ለችግረኛና ለምስኪን አስቦ የሚሰጥ እሱ
ምስጉን ነው እግዚአብሔር ከክፉ ቀን ያድነዋል ይጠብቀዋልም
ሕያውም ያደርገዋል፡፡ በምድር ላይ በሕይወት ሥጋ
በሚኖርበር ጊዜ ያስመሰግነዋል በጠላቶቹም እጅ አሳልፎ
አይሰጠውም ታምሞ በአልጋው ላይ ይረዳዋል፡፡ መልካሙን
ምንጣፍ ያነጥፍለታል እንዳለ ቅዱስ ዳዊት መዝሙር ፵፡፩ ፡፡
ዳግመኛም እግዚአብሔር ይራራላቸዋል ደካማውን ከብርቱ
ረዳት የሌለውን ከቀማኛ እጅ ያድናቸዋል ከግፍና ከነፍስ
ጭንቀት ይሠውራቸዋል፡፡ ለሰው የሚራሩ ሰዎች ከቡራን
ናቸው፡፡ መዝሙር ፸፩፡፳ የተበደሉ ሰዎች መንግሥተ
ሰማያትን እጅ ያደርጓታልና ለተበደለ የሚራራ እናት አባት
ለሌለው እናት አባት የሚሆን ክርስቲያንም አረመኔም ቢሆን
ሁሉም የእግዚአብሔር ፍጥረት ነውና ለድኃ ሁሉ የሰጠ በቅንነት
የሚሄድ ጽድቅንም የሚያደርግ ልቦናው ተንኮል የሌለበት
በአንደበቱ ዕውነትን የሚናገር በሰውነቱ ክፋት በቃሉ ሐሰት
የማይገኝበት በባልንጀራው ላይ ክፋትን የማያደርግ ወገኖቹን
የማይዘልፍ የማይሳደብ እግዚአብሔርን የሚፈራ ሰውን
የሚያከብር ባልንጀራውን የማይከዳ ገንዘቡን በአራጣ
የማያበድር ከንጹሑ ላይ መማለጃን ጉቦን የማይቀበል ፍርድን
የማያጓድል ድሀን የማይበድል የከበረ ነው እንዳለ ሮሜ. ፩፡፲፫
ለመስጠት እጃቸውን የዘረጉ ሰዎች በሞቱ ጊዜ ከእግዚአብሔር
ዘንድ ያቀርቧቸዋል እጅ ነሥተው ሰግደው ወደዚህ ያመጧቸዋል
ዋጋቸውንም ያሰጣቸዋል በዚህ ቦታ ለዘለዓለም ደስ ብሎአቸው
ይኖራሉ አለኝ፡፡
21
ዳግመኛም የወተት ወንዝ ወዳለበት ቦታ እነማን ይኖራሉ
አልሁት፤ ከዝሙት ሰውነታቸውን ንጹሕ ያደረጉ ሴቶቸም
በድንግልና የኖሩ በሞቱ ጊዜ ወደ እግዚአብሔር ይወስዳቸዋል
ዋጋቸውንም ይሰጣቸዋል፤ በዚያው ቦታ ደስ ብሏቸው ይኖራሉ
አለኝ፤ ከዚህ በኋላ በወርቅ በዕንቁ የተሸለመች ከፀሐይ
ከጨረቃ ፪ እጅ የምታበራ ምድር አሳየኝ፤ ይህ ቦታ ለማን
ይሆናል ብዬ ልጄን ጠየቅሁት መለሰልኝ፤ አንደበቱን ከሐሜት
የጠበቀ ኩራት የሌለበት ባልንጀራውን የማያዋርድ ምክንያተ
ሐኬት የሌለበት፤ በልቡናው ቂም በቀል የማያኖር የዋህ የሆነ
እነዚህ ሁሉ በሞቱ ጊዜ ወደ እግዚአብሔር ይወስዱዋቸዋል
እጅ ነሥተው ሰግደው ያመጧቸዋል፤ የዋሃንስ ይወርስዋ
ለምድር፡፡ የዋሃን መንግሥተ ሰማይትን ወርሰው በውስጧ
ይኖራሉ፡፡ እንዳለ መዝሙር ፲፬:፪-፭ ዋጋቸውን ይህንን
ይሰጣቸዋል አለኝ፡፡
21
ዳግመኛም በዚህ ቦታ አንፃር ብዙ ሰዎች ተበትነው አየሁ በገነት
በር ብዙ ፍሬ ያለው የሚመስል ትልቅ ዛፍ አለ እነዚያ ሰዎች
ፍሬ ያለው መስሎአቸው በተራቡ ጊዜ ለመብላት ወደ ላይ
ሲወጣ ይወጣሉ፤ ወደታች ሲወርድ ይወርዳሉ ፍሬውን
አያገኙትም ይኸንን ባየሁ ጊዜ መሪር ዕንባ አለቀስኩ ልጄንም
ጠየቅሁት እሊህ ሰዎች ምንድር ናቸው፡፡ አልሁት፤ ይህስ ዕጽ
ምንድር ነው እኔ ዛፉ ፍሬ ያለው መስሎኝ ነበር እነዚህ የተራቡ
ሰዎች ፍሬውን ለመብላት ወደታች ሲወርዱ ይወርዳሉ፡፡
ወደላይ ሲወጣ ይወጣሉ ፍሬውን አላገኙትም ነገሩ ምንድር ነው
አልሁት እረሱም የነዚህን ሰዎች ኃጢአት እነግርሻለሁ አለኝ
በጾም በጸሎት የተጸመዱና በትዕግሥት ፍጹማን ቢሆኑ ለተራቡ
አላበሉም ለተጠማ አላጠጡም ለታረዘ አላለበሱም እንግዳ
አልተቀበሉም ትዕቢተኞች ኩራተኞች ናቸው አለኝ እነዚህ ቃላት
ሰውን ያስኮንናሉን ብዬ ልጄን ጠየቅሁት መለሰልኝ ከነዚህ
ከ፫ቱ ኃጢአት የበለጠ የለም ዲያብሎስም በትዕቢቱና በኩራቱ
ተዋርዷልና አለኝ፡፡ እንዲህም ብዬ ልጄን ጠየቅሁት አስከ መቼ
ድረስ ይኮነናሉ አልሁት ጻድቃን ስለእነርሳቸው
ስለሚለምኑላቸው ዳግመኛ እስከመጣ ድረስ ነው እኔም
እምራቸዋለሁ አልጥላቸውም ወደመንግሥተ ሰማያት ይገባሉ
አለኝ፡፡ ይኸንን በሰማሁ ጊዜ ልጄን አመሰገንኩት፡፡
21
ከዚህም በኃላ ወደሌላ ቦታ ወሰደኝ ከወርቅ መርከብ ላይም
አወጣኝ ወስዶም ከቤት አገባኝ ያች ቤትም ከፀሐይ ከጨረቃ
ይልቅ ታበራለች በውስጧም ብርሃኑን የሚያንፀባርቅ የግምጃ
ምንጣፍ ወሳንሳ ተነጥፎባታል የወርቅ የብርሃን አልጋ
ተዘርግቶባታል ይህች ቦታ ለማን ትሆናለች ብዬ ልጄን
ጠየቅሁት እግዚአብሔር እንድ ያደረጋቸው ባልና ሚስት
አይለያዩም ባልና ሚስት አንድ አካል ናቸው እንዳለ ማቴ. ፲፱፡፯

21
ወንድ በአንድ ሴት ሴት በአንድ ወንድ ተጠብቀው ቢኖሩ በሞቱ
ጊዜ ከዚህ ቦታ ያገባቸዋል ለዘለዓለምም ደስ ብሎአቸው
ይኖራሉ አለኝ፡፡ ከዚህ በኋላ ፬ሺ ከ፬፻ እንደ ፀሐይ የሚያበሩ
መናብርተ ብርሃን አየሁ እሊህ ማናብርት ለማን ይሆናሉ ብዬ
ልጄን ጠየቅሁት በስሜ ስለማመን የሚያስተምሩ ናቸው
አለኝ፡፡ ሁሉም ይጠሏቸዋል ሁሉም ይደበድቧቸዋል
ይገድሏቸዋል ኋላ ግን ከራሳቸው ፀጉር አንዲት አትጠፋም፡፡
በመቻላችሁ ነፍሳችሁን ታድኗታላችሁ እንዳለ ማቴዎስ ፲፡፳፪
፡፡
21
ሲርባቸው ሲጠማቸው ከሀገር ወደ ሀገር ሲሰደዱ ዓለምን የናቁ
ስለሃይማኖት ሰውነታቸውን ለሞት አሳልፈው የሰጡ ፲፪
ሐዋርያት ፸፪ አርድእት እነዚህ ሁሉ ይቀበሏቸዋል አለኝ፡፡
የቅዱሳን ሠራዊት ሁሉ የእግዚአብሔር ማደሪያው ማርያም
ሆይ እንዴት ነሽ ብለው እጅ ነሡኝ ሰገዱልኝ ከዚህ በኋላ
ወደሌላ ቦታ ወሰደኝ ከፀሐይ ከጨረቃ ይልቅ የሚያበሩ ፪፻
ቤተ ክርስቲያን አየሁ እነዚህ ለማን ይሆናሉ ብዬ ልጄን
ጠየቅሁት ለጳጳሳት ለኤጲስ ቆጶሳት ለቀሳውስት ለዲያቆናት
ለአናጎንስጢስ ለመዘምራን ይሆናሉ አለኝ ሁሉም ይገባሉ ብዬ
ጠየቅሁት አይገቡም ጥቂት ናቸው የሚገቡት አለኝ እግዚኦ
እግዚኦ እያሉ የሚዘባበቱብኝ ሁሉ ከመንግሥተ ሰማያት
አይገቡም የአባቴን ፍቃድ የፈጸሙ ይገባሉ ብዬ የተናገርኩትን
አልሰማሽምን አለኝ ማቴዎስ ፲፭:፬ ፡፡
21
ሰውነታቸውን ከዝሙት ንጹሕ ያደረጉ ከሰው ሚስት ያልሄዱ
ኩራት የሌለባቸው ትእቢት ምቀኝነት የሌለባቸው ቂም
በልቦናቸው ያላኖሩ ከአንድ ሴት ወደ አንድ ሴት ከአንድ ወንድ
ወደ አንድ ወንድ የማይሉ ቁጡና ሰካራም ያልሆኑ ለጣኦት
ያልሰገዱ በአምልኮ ባዕድ ያላመለኩ በሐሰት ያልማሉ ቤተ
ክርስቲያን የሚያዘወትሩ በንጹሕ ሆነው ሥጋዬን ደሜን
የሚቀበሉም የሚያቀብሉ ሰዎች እነዚህ ናቸው ከመንግስሥተ
ሰማያት የሚገቡ እነዚህን የነገርኩሽን ቃላት ያልፈጸሙ
መንግሥተ ሰማያት አይገቡም አለኝ፡፡
21
ከዚህ በኋላ ወደ ኢየሩሳሌም ሰማያዊት አደረሰኝ የእሳት
መጋረጃ ያለበት የብርሃን ቤተ መቅደስ አየሁ በእጁ መሰንቆ
በገና ይዞ እየመታ እንደ ፀሐይ የሚያበራ አንድ ሰው አየሁ ያም
ሰው መሰንቆ በገና ሲመታ ምድሯን ያናውጻታል ከኢየሩሳሌም
ደጁ ቆሟል እኔም በገባሁ ጊዜ ወደእኔ መጣ ማርያም ሆይ
ከሁሉ ይልቅ አንቺ የከበርሽ ነሽ ብሎ እጅ ነሳኝ ሰገደልኝ የዚህ
ሰው ስሙ ማነው፤ ብዬ ልጄን ጠየቅሁት ቅዱስ ዳዊት ነው
አለኝ ሃሌ ሉያ ብሎ ሲያመሰግን ሰምቼው፡፡ ሃሌ ሉያ ሲሉ
የሰማኋቸው በዳዊት ቃል ምስጋና ሁሉ ተነግሯልን ብዬ ልጄን
ጠየቅሁት አዎን ምስጋና ሁሉ በዳዊት ቃል ተነግሯል አለኝ
እኔም መልሼ ሃሌ ሉያ ማለት ምን ማለት ነው ብዬ ልጄን
ጠየቅሁት ዓለም ሳይፈጠር የነበረ ዓለምን አሳልፎ የሚኖር
አምላክ የተመሰገነ አምላክ ማለት ነው አለኝ ሃሌ ሉያ ቢል
ለሰው ምስጋና ይሆንለታልን ብዬ ጠየቅሁት አወን በጥቡዕ
ልቡና ሆኖ ሃሌ ሉያ ብሎ ቢያመሰግን ምስጋናው እንደ
መላእክት ይሆንለታል አለኝ ዳግመኛም መለስሁለት ሰው
የታመመ እንደ ሆነ ተኝቶ ቢጸልይ ኃጢአት ይሆንበታልን
አልሁት ለድውይ አይሆንበትም አለኝ፡፡ ከዚህ በኋላ ወደሌላ ቦታ
ወሰደኝ የወርቅ ልብስ ያለበት ዳርቻው የማይታወቅ እንደ
ፀሐይ የሚያበራ አገር አሳየኝ ይህ ቦታ ለማን ይሆናል ብዬ
ልጄን ጠየቅሁት ንብረታቸውን ትተው ዓለመን ንቀው ለመነኑ
ሰዎች ይሆናል አለኝ ይህችን ሀገር የሚያውቃት የለም፡፡ ካህናተ
ሰማይ አይገቡም ከበር ይቆማሉ እንጂ የባሕርይ አባቴ አብ
የሕይወት መንፈስ ቅዱስ እነገባለን አንቺም ግቢ ሀገር
ይሁንልሽ አልኝ ፫ሺ መላእክት ያገልግሉሽ አለኝ መነኮሳት ሁሉ
ይጋባሉን ብዬ ጠየቅሁት ሁሉም አይገቡም አለኝ ሰውነታቸውን
ከዝሙት ንጹሕ ያደረጉት ዓለምን ንቀው የመነኑ ደስታን
ተድላን የጠሉ ቁጡ ያልሆኑ ትዕቢት ኩራት የሌለባቸው ቂም
በልቦናቸው ያላኖሩ ሰውን ከሰው የማያጣሉ ንዝኅላል ያልሆኑ
በየጊዜው በየሰዓቱ ጸሎት የሚያደርጉ ይገባሉ አለኝ በጾም
ተጸምዶ የሚኖር መነኩሴ የሚበልጠው የለም ብሎ መጽሐፍ
የተናገረውን አልሰማሽምን ዳግመኛም ገንዘብ አግኝቶ
ከሚመጸውት መነኩሴ ገንዘብ የሌለው በትምህርትና በጸሎት
ተጸምዶ የሚኖር መነኩሴ ይበልጣል ዳግመኛም ጳውሎስ እኔ
በዓለም ዘንድ ምውት ነኝ ዓለምም በኔ ዘንድ ምውት ናት
እንዳለ፡፡
21
ይኸንን ሁሉ የፈጸመ መነኩሴ ከመንግሥተ ሰማያት ይገባልን
ብዬ ብጠይቀው የማይገቡትን እነግርሻለሁ አለኝ ትዕቢተኞች
ኩራተኞች ሴሰኞች ባልንጀሮቻቸውን የሚጠሉ ባንደበታቸው
እራሳቸውን ከፍ ከፍ የሚያደርጉ መነኮሳትም ሆነው ተሾመው
የሚገዙ የሚነዱ በፈረስ በበቅሎ የሚሄዱ ከቆብ በኋላ
የሚሰስኑ ለሆዳቸው የሚገዙ አለልክ የሚበሉ የሚጠጡ ሁል
ጊዜ ዛሬ ዓመት በዓል ነው እያሉ ለመብል የሚዘጋጁ እነዚህ
መንግሥተ ሰማያት አይገቡም አለኝ ዳግመኛም ነይ ወደ
ምዕራብ እንሂድ የኃጥአን ነፍስ የሚኖሩበትን አሳይሻለሁ አለኝ
ወስዶ በሰማይና በምድር ዳር ከባሕር ዳርቻ አደረሰኝ የእሳት
ባሕር ያለበት የገሃነም ቦታ አሳየኝ ይህ ቦታ ለማን ይሆናል ብዬ
ልጄን ጠየቅሁት በመልካም ግብር ያልተገኙ በኃጢአት የኖሩ
ቦታቸው ይህ ነው አለኝ በዚያ በባሕር ውስጥ ብዙ ሰዎች
ከጉልበታቸው ድረስ ከእንብረታቸው ድረስ ከደረታቸው ድረስ
ከአንገታቸው ድረስ ከከንፈራቸው ድረስ ከእራሳችው ድረስ
የእሳት ባሕር ያጠለቃቸው አየሁ ከጉልበታቸው ድረስ
ያጠለቃቸው እነማን ናቸው ብለው በ፫ ጊዜያት ጸሎት የማይዙ
ናቸው አለኝ፡፡ ከእንብረታቸው ድረስ ያጠለቃቸው እነማን ናቸው
አልሁት ከቤተ ክርስቲያን ውስጥ ዋዛ ፈዛዛ የሚጫወቱ ናቸው
አለኝ ከደረታቸው ድረስ ያጠለቃቸው እነማን ናቸው ብለው
ከቆረቡ በኋላ እህል ውሀ ሳይቀምሱ የሚናገሩ ናቸው አለኝ
ከአንገታቸው ድረስ ያጠለቃቸው እነማን ናቸው ብለው
ባልንጀሮቻቸውን የሚያሙ ናቸው አለኝ ከከንፈራቸው ድረስ
ያጠለቃቸው እነማን ናቸው ብለው ባልንጀራውን እንግደል
የሚሉ ናቸው አለኝ፡፡ ከራሳቸው ድረስ ያጠለቃቸው እነማን
ናቸው ብለው ከጽቅረ ቤተ ክርስቲያን ሴት የሚተኙ ናቸው
አለኝ፡፡ ከዚህም በኋላ ከሥር እስከ ጫፍ ከጫፍ እስከ ሥር
ድረስ በ፭ ሺህ ዓመት የማይደረስ ትልቅ ገደል አሳየኝ ያንዱ
ነፍስ ባንዱ ነፍስ ላይ ሲወድቅ አየሁ እኔም ምንድር ናቸው ብዬ
ልጄን ጠየቅሁት ባባታቸው በወንድማቸው በልጃቸው
በባልንጀራቸው ሚስት የሚሰስኑ ናቸው አለኝ ሴት አራስ ሆና
ወይም መርገሟ በመጣ ጊዜ በሩካቤ ሥጋ የሚገናኙና እንስሳን
ምድርን ሰንጥቀው የሚያወስቡ ወንዱንም በግብረ ሰዶም
የሚያመነዝሩ ካህን ሆኖ ከሌላ ሴት የካህኑም ሚስት ከሌላ
ወንድ ቢሄዱ እነዚህ ሁሉ የኩነኔ ቦታቸው ይህ ነው አለኝ ከዚህ
በኋላ ሌላ ቦታ አሳየኝ ፬ መላእክተ ጽልመት ተሸክመው
ወስደው በእሳት አልጋ አስቀመጠው በእሳት ፍላፃ ሲነድፉት
የእሳት ውሀ ሲአፈሱበት ፩ ሽማግሌ ሰው አየሁ ባየሁትም ጊዜ
ብዙ አለቀስሁ ይህ ሰው ማነው ብዬ ልጄን ጠየቅሁት ጳጳስ ነው
አለኝ ኃጢአቱንም እነግርሻለሁ አለኝ፡፡ የቤተ ክርስቲያንን ሥነ
ሥርዓት አልተከተለም በሕጌ ተጠብቆ አልኖረም ሥጋዬን
ደሜን ያረከሰ ነው ዘመኑንም በዝሙት የፈጸመ ነው ዳግመኛ
እንግዳ አልተቀበለም ለተራቡ አላበላም ለተጠማ አላጠጣም
ለታረዘ አላለበሰም የታመመ አልጠየቀም ያዘኑትን አላረጋጋም
የታሠሩትን አላስፈታም ስለዚህ የዘለዓለም ቦታው ይህ ነው
አለኝ፡፡ ከዚህ በኋላ ፬ መላእክተ ጽልመት በእሳት መንዶ
እየደበደቡ ከእሳት ባሕር ሲጨምሩት ፩ ታላቅ ሰው አየሁ፡፡ ይህ
ሰው ማነው ኃጢአቱስ ምንድር ነው ብዬ ጠየቅሁት፡፡ ሊቀጳጳስ
ነው ኃጢአቱን እነግርሻለሁ አለኝ ፩ነቴን ፫ነቴን ለሕዝብ
አላስተማረም እራሱን ወዳድ የግል ጥቅሙን ፈላጊ ነገሥታትን
መኳንንትን አይመክርም ፍርድ ሲጓደል ድሀ ሲበደል ዳኞችን
አይገሥጽም አያስተምርም ስለዚህ የዘለዓለም ኩነኔው ይህ ነው
አለኝ፡፡
21
ከዚህ በኋላ የመለኮትን ሥጋ ስትበላ ትራባለህን የመለኮትን ደም
ስትጠጣ ትጠማለህን ብለው በአፉ እሳት ሲያጎርሱት እሳት
ሲያጠጡት መላእክተ ጽልመት ሲጎትቱት አንድ ሰው አየሁ ይህ
ሰው ማነው ኃጢአቱስ ምንድር ነው አልሁት ቄስ ነው
ኃጢአቱንም እነግርሻለሁ አለኝ በክህነት ሥራ አልኖረም
ሰውነቱንም ንጹሕ አላደረገም ዘመኑንም በሳቅ በጨዋታ
የፈጸመ ነው የዘለዓለም ኩነኔው ይህ ነው አለኝ፡፡
21
ዳግመኛም መላእከተ ጽልመት ፊት ፊቱን እየደበደቡ በግምባሩ
ሲያዳፉት መላሱን በእሳት ምላጭ ቆርጠው በአፉ ደም ሲዘነብ
ወደ እሳት ባሕርም ሲጨምሩት አንድ ሰው አየሁ ይህ ሰው
ማነው ኃጢአቱስ ምንድር ነው ብዬ ልጄን ጠየቅሁት መለሰልኝ
ዲያቆን ነው አለኝ ኃጢአቱስ ምንድር ነው ብዬ ጠየቅሁት
ኃጢአቱንም እነግርሻለሁ አለኝ በሕጌ አልኖረም ሥጋዬን ደሜን
በንጹሕ አላዘጋጀም ቤተ ክርስቲያን አልወደደም ለግብረ
ተልእኮ አልተፋጠነም ድሀ ቢሞት አልቀበረም ኩሩ ትዕቢተኛ
ነው አለኝ ከዚህ በኋላ ብዙ የተበታተኑ ሰዎች በእሳት መካከል
አየሁ እነዚህ እነማናቸው ብለው በፀሐይ በጨረቃ በከዋክብት
በዕንጨት በድንጋይ የሚያመልኩ ለዛር ለቃልቻ ለጠንቋይ
የሚደግዱ ናቸው ስለዚህ ኩነኔያቸው ለዘለዓለም ይህ ነው አለኝ
ከዚህ በኋላ በእሳት ዛፍ ላይ የተሰቀሉ ብዙ ሰዎች አየሁ ምንድር
ናቸው ብዬ ልጄን ጠየቅሁት (ብዕልን) ክብርን የወደዱ ሀብት
ገንዘብ እያለቸው ለተራበ የማይሰጡ የማይመፀውቱ ድሆቸን
የሚበድሉ ባለጠጎች ናቸው ከመከራ ሥጋ ከመከራ ነፍስ ይድቃሉ
ስለዚህ ለዘለዓለምም ቦታቸው ይህ ነው አለኝ፡፡
21
ከዚህ በኋለ በእሳት ሰንሰለት አንገታቸውን ታስረው ጨለማ
የለበሱ ሴቶች አየሁ እነማን ናቸው ብዬ ልጄን ጠየቅሁት እናት
አባቶቻቸው በሕግ ሳያጋቧቸው ድንግልናቸውን ለማንም በዱር
በጫካ የሚሰጡ የሚሰስኑ ክብረ ንጽሕናቸውን የሚያጎድፉ
ናቸው ስለዚህ ኩነኔአቸውም ለዘለዓለም ይህ ነው አለኝ፡፡
21
ከዚህ በኋላ ልቅሶ ጥርስ ማፋጨት ከአለበት ገሃነመ እሳት
እጃቸውን እግራቸውን ታስረው በእሳት ግንድ ተሰቅለው ብዙ
ሰዎች አየሁ እነማናቸው ብዬ ጠየቅሁት የሰው ገንዘብ የሚበሉ
እንደልባቸው የሚናገሩ በዚህ ዓለም ያላግባብ የከበሩ ወይም
የበለጸጉ የሚገዙ የሚነዱ ብዑላን ነገሥታት መኳንንት ናቸው
ለዘለዓለም የኩነኔያቸው ቦታ ይህ ነው አለኝ፡፡
21
ከዚህ በኋላ የእሳት ውሾች የእሳት እባቦች የእሳት አንበሶች
እግራቸውን እጃቸውን ሲሰብራቸው በእሳት ዛፍ ላይ ተሰቅለው
ብዙ ሰዎች አየሁ እነማናቸው ብዬ ብጠይቀው ከቆብ በኋላ
የሚሰስኑ መነኮሳት ናቸው ሴቶችም በፀነሱ ጊዜ መድኃኒት
እየጠጡ የሚያስወርዱ ናቸው እነኛም ሕፃናት መልካምም ሆነ
ክፉ ብንሠራ ምነው ባደግን አለጊዜያችን አጠፉን ብለው አቤት
አቤት እያሉ ይጮሁባቸዋል አባቴ ግን መልአኩን ሕፃናቶቹን
ወደ መልካም ቦታ ውሰዳቸው ይለዋል እናቶቻቸውም
ለዘለዓለም ኩነኔያቸው ይህ ነው አለኝ በጥቡዕ ልቦና ነስሓ ቢገቡ
አትምራቸውምን አልሁት እምራቸዋለሁ አለኝ ቀሳውስቱም
የነፍስ ልጆቻቸውን መክርው ተቆጥተው ንስሓ ግቡ
አይሏቸውም እነደ ፈሌ እንደ (ፈላ) ይሆናሉ አለኝ፡፡
21
ከዚህ በኋላ እህል እንዳይበሉ ውሀ እንዳይጠጡ ተክልክለው
በእሳት ግንድ ታስረው ብዙ ሰዎች አየሁ እነማን ናቸው ብዬ
ብጠይቀው እንዲህ አለኝ ሴት በመርገም ጊዜዋ ሆና በሩካቤ
ሥጋ የተገናኙ ዓርብ ረቡን ፵ ጾም ሁዳዴን የማይጾሙ የኩነኔ
ቦታቸው ይህ ነው አለኝ ንስሓ ቢገቡ አትምራቸውም ብለው
እምራቸዋለሁ አለኝ፡፡
21
ከዚህ በኃላ በእሳት መካከል እጃቸውን እግራቸውን የተቆረጡ
ሰዎች አየሁ ምንድር ናቸው ብዬ ጠየቅሁት ለሰው ክፉ የሚጥሩ
የሚጽፉም የሰው ገንዘብ የሚሰርቁ የሚነጥቁ የሚዘርፉ
ጉልበት እያላቸው ሠርተው የማይበሉ አታላዮች ኪስ
አውላቂዎች የሰው ቤት በቀን መዝጊያ የሚሰብሩ ሌሊት
ግድግዳ የሚሠረሥሩ ለሰው ነፍስ የማይሳሱ ርኀራኄ የሌላቸው
በገንዘብ እየተገዙ የሰው ነፍስ የሚያጠፉ ዓይናቸውን በስው
ሀብት ላይ የሚያሳርፉ በጧት ወደ መሸታ ቤት የሚገሠግሡ
በብዙ ድካም ያገኙትን ገንዘብ ቤተሰባቸውን በድለው ለመሸታና
ለዝሙት የሚያጠፉ ሰካራሞች አጭበርባሪዎች ናቸው የኩነኔ
ቦታቸውም ለዘለዓለም ይህ ነው አለኝ፡፡
21
ከዚህ በኋላ በእሳት ልጓም ተለጉመው በእሳት ሜንዶ ፊት
ፊታቸውን ሲደበድቧቸው አየሁ ምንድር ናቸው ብዬ ልጄን
ጠየቅሁት ባልንጀራቸውን የሚሰድቡ የሚያዋርዱ ምቀኞች
ተንኮለኞች ሟርተኞች ሰላቢዎች ተዕቢተኞች ሰውን
አሽሟጣጮች ናቸው አለኝ፡፡
21
ዲያብሎስም አዳምን በሰደበ ከማዕረጉ ተዋርዷልና ዳግመኛም
ጨው ባሩድ የሞላበት ጨለማ ጉድጓድ አየሁ በዚያው ውስጥ
እግራቸውን እጃቸውን የተቆረጡ ብዙ ሰዎች አየሁ፤ ምንደር
ናቸው ብዬ ልጄን ጠየቅሁት አንድነቴን ሦስትነቴን ቅድመ
ዓለም ከአብ ያለ እናት መወለዴን ድኀረ ዓለም ከሰማየ ሰማያት
ወርጄ ከድንግል ማርየም ያለ አባት ወወለዴን በሄሮደስ ቅንዓት
ከሀገር ወደ ሀገር መሰደዴን መጠመቄን መገረፌን
በመልዕልተ መስቀል መስቀሌን በቀኖት መቸንከሬን ሞቼ
መነሣቴን ከትንሣኤዬም በኋላ በ፵ኛው ቀን ወደሰማይ ማረጌን
በኃላም ይህን ዓለም ለማሳለፍ በጌትነትና በታለቅ ግርማ
መምጣቴን የማያውቁ አረመኔዎች ናቸው ለዘለዓለም
የሚኖሩበት የኩነኔ ቦታቸው ይህ ነው አለኝ፡፡
21
ከዚህ በኋላ የእሳት እባብ በአንገታቸው በአፋቸው
ተጠምጥሞባቸው ከአፋቸው የእሳት ዲኝ ሲወጣ ብዙ ሰዎች
አየሁ ምንደር ናቸው አልሁት ብዙ ክርስቲያን ሂደው ያላገለገሉ
ካህናት ናቸው ለዘለዓለም የኩነኔ ቦታቸው ይህ ነው አለኝ፡፡
21
ከዚህ በኋላ በእሳት ገመድ አስረው ራሱን ወደታች እግሩን
ወደላይ አድርገው ሰቅለው አንድ ሰው አየሁ ዳግመኛ በእሳት
ጦር ፊት ፊቱን እየወጉ ከእሳት ላይ ሲጥሉት አየሁ ይህ ሰው
ማነው ብዬ ልጄን ጠየቅሁት ቄስ ነው ኃጢአቱንም እነግርሻለሁ
አለኝ በሰንበት ዕጣን አያጥንም ንዝኅላል ትዕቢተኛ ኩራተኛ ነው
ጸሎት አያደርስም የዘለዓለም የኩነኔ ቦታው ይህ ነው አለኝ
ልጄን እንዲህ ስል ጠየቅሁት ቁርባን ምን ጊዜ ይቁረብ እሁድ
በነግህ ቀዳሚት በ፫ ሰዓት ሊቀደስ ይገባል ኦሪት ነቢያትን
ልፈጽማቸው ነው እንጂ ላሳልፋቸውና ልሽራቸው አልመጣሁም
ብሎ መጽሐፍ የተናገረውን አልሰማሽምን አለኝ፡፡
21
ቀዳሚትንም ካንዲት ቀን በቀር አልሻርኳትም ሌሎችን
ሰንበታት እንደ እሁድ ያክብሯቸው አለኝ ማለትም እንደ እሁድ
ያክብሯት ማለት ነው፡፡
21
ከዚህ በኋላ በእሳት ፍላፃ ሲነድፉት አንድ ሰው አየሁ ይህ ሰው
ማነው ብዬ ልጄን ጠየቅሁት ዲያቆን ነው አለኝ ኃጢአቱስ
ምንድር ነው ብዬ ብጠይቀው እነግርሻለሁ አለኝ፡፡
21
መሥዋዕቱን በንጹሕ አላቀረበም በሰዓቱም አላዘጋጀም
ሰውነቱንም ከኃጢአት አላነፃም ለዘለዓለም የኩነኔ ቦታው ይህ
ነው አለኝ፡፡
21
ከዚህ በኋላ ከሌላ ቦታ ወሰደኝ የእሳት ጉድጓድ አየሁ ከውስጡ
ብዙ ሰዎች ሞልተው በአንገታቸው የእሳት እባቦች
ተጠምጥሞባቸው አራት መላእክተ ጽልመት የእሳት ጦር
ሲወረውሩባቸው አየሁ ባየኋቸውም ጊዜ ብዙ አለቀስኩ እሊህ
እናማናቸው ብዬ ልጄን ጠየቅሁት መነኮሳት ናቸው በሕጌ
አልኖሩም ሥራዓቱንም አልጠበቁም መነኮሳት ነን ሲሉ
የመነኮሳትን ሥራ አይሠሩም የማይረባቸውን
የማይጠቅማቸውን ሥጋዊና ዓለማዊ ሹመት ይፈልጋሉ
ዘመናቸውንም በኃጢአት የፈጸሙ ናቸው ለዘለዓለሙ የኩነኔ
ቤታቸው ይህ ነው አለኝ፡፡
21
ከዚህ በኋላ የተዘጋጀ ታላቅ ገሃነም አየሁ ልጄም እናቴም
ማርያም ታየዋለችና ክፈቱ ብሎ የገሃነመ እሳት በር ጠባቂውን
ጠርቶ አስከፍቶ በሮቹ በተከፈቱ ጊዜ አይቼ ፈራሁ ተንቀጠቀጥኩ
ይህ ቦታ ስሙ ማነው ብዬ ልጄን ጠየቅሁት ገሃነመ እሳት ነው
አለኝ በዚህስ ውስጥ የሚኖሩ ምንድን ናቸው ኃጢአታቸውስ
ምንድ ነው አልኩት ሰው ከውሀና ከመንፈስ ቅዱስ ካልተወለደ
በቀር ወደ እግዚአብሔር መንግሥት ይገባ ዘንድ አይቻለውምና
ስለዚህ ያልተጠመቁ አረመኔዎች ናቸው የዘለዓለም ቦታቸወም
ይህ ነው አለኝ፡፡ ዮሐንስ ፫፡፭፡፡ እነዚህም በስቃይ ያሉ ሁሉ
ባዩኝ ጊዜ ማርያም አንቺ ከሁሉ ይልቅ የከበርሽ ነሽ
የማኀፀንሽም ፍሬ የከበረ ነው አንቺን ያዩ ዓይኖቻቸን የከበሩ
ይሁኑ ብለው ጮሁ እኔም ሰው ሆኖ ኃጢአት የማይሠራ የለምና
ልጄን እባክህን ማርልኝ አልሁት እርሱም ዓርብ በሠርክ
መጥተው እስከ ሰኞ ድረስ ስለአንቺ በገነት ያሳርፏቸው አለኝ፡፡
21
ይህንም በሰማሁ ጊዜ ልጄን ፈጣሪዬን አመሰገንኩት
እመቤታችን ድንግል ማርያም ይህንን ከዚህ ቀጥሎ ያለውን
ማስጠንቀቂያ ሰጥታለች እወቁ ተጠንቀቁ ሴት አራስ ሆና
በሩካቤ ሥጋ የተገናኘ በመርገሟም ሰዓት ወንድ ከሴቷ ሴቷም
ከወንድ ፈቃደኛ ሆነው ቢገናኙ ኃጢአት ይሆንባቸዋል በልቡ
ክፋት ያለበት ሰው ይህች መጽሐፍ ካለችበት ቦታ አይድረስ
መጽሐፉንም ከእንደዚህ ካለው መጥፎ ቦታ አታኑሩ ብላ
ተናግራለች፡፡
21
ዳግመኛም ስለ በዓላት አከባበር ቢቻላችሁ ፴፫ቱን ባይቻላችሁ
፭ቱን የጥር ማርያምን የየካቲት ኪዳነ ምሕረትን የግንቦት
ልደታን የሰኔ ማርያም የነሐሴ ፲፮ ፍስለታን እነዚሀን በዓላቴን
ያከበረ ይህን መጽሐፍ የፃፈ ያጻፈ ያነበበ የተረጎመ የሰማ ያሰማ
እነዚህን ሁሉ የፈጸሙ በሞቱ ጊዜ እኔ እቆምላቸዋለሁ ብላ
ለዮሐንስ ነገረቸው፡፡
21
የአምላክ ልጅ ወልደ አምላክ ለችግር አማላጅቱ እመቤታችን
ማርያም የገለጸላት ራእይ ባጭሩ እዚህ ላይ ተፈጸመ፡፡ የልጅዋ
የወዳጅዋ ቸርነት ለሁላችን ይደረግልን የእመቤታችን ረድኤት
በረከት እስከ ዘለዓለሙ ይደርብን አሜን አቡነ ዘበሰማያት፡፡
°°°°°°°
ምንጭ: መዝገበ ጸሎት ወመጽሐፈ ጸሎት ባለ ሰባ ስምንት
ከተሰኘው የጸሎት መጽሐፍ ላይ ከገጽ 591 እስከ 636
የተወሰደ ነው። በዘሪሁን እሸቱ የተዘጋጀ 20/4/2008 ዓ.ም
†† †† † † †† ††
ለአባ ሕርያቆስ ፤ለቅዱስ ኤፍሬም ፤ለቅዱስ ያሬድ ፤ ለአባ
ጊዮርጊስ ዘጋስጫ የተገለጸች ዕመቤታችን እኛንም በበረከት እና
በረድኤት ትጎብኘን ፤ ከልጅዋ ከወዳጅዋ ከመድኃኔዓለም ዘንድ
ታማልደን ፤ አሜን!!!
ወ ስ ብ ሐ ት ለ እ ግ ዚ አ ብ ሄ ር