በስም ኣብ ወወልድ ወመንፍስ ቁዱስ ኣሃዱኣምላክ ኣሜን
እንኳን ኣደርሳቹሁ ኣደርስን ለእናታችን ለቅድስተ ቁዱሳን
ለኪዳን ምህርት ክብር በዓል ቀኑ የበርከት ቀን ይሁኑላቹ
ኣሜን።
{መልክአ ኪዳነ ምህረት }
፩ እግዚአብሔር ኣብ። እመቤቴ ኪዳን ምህርት ሆይ በአካል
ሦስት ሲሆን በመለኮታዊ ባሕርዩ በኣንድነቱ ጸንቶ የሚኖር
የብርሃን መገኛ እሱ እግዚአብሔር አብ ለቃል ኪዳንሽ
የተሰጠው ልዩ ክብር ብሩህ አድርጒ ያሳየኝ ዘንድ የቸርነቱ ጸዳለ
ብርሃን ዓይነ ልቡናዬን ያብራልኝ።
የቃል ኪዳኗ እመቤቴ ሆይ : ከእግዚአብሔር በታች በስማይም
በምድርም እንቺ የሁሉ እመቤት ነሽ እኮን።
፪ ለዝክረ ስምኪ። እመቤቴ ኪዳን ምህርት ሆይ በብርሃነዊው
ኮኮብ ለተመስለው ስም ኣጠራርሽ ስለምታ ይግባል ፤በጨለማ
ለሚኖሩ ሕዝቦች ብርሃኑን አብርቶላቸዋልና።
የቃል ኪዳኗ እመቤቴ ሆይ የኣምላክ ቃል ኪዳኑ መዛግብት
በዕለተ ዓርብ የተገኘውን የደኅንነታችን ተስፋ ያስገኘሽ ዕውነተኛ
መዝገብ ነሽ እኮን። ኣባታችን ቀዳማዊ ኣዳም በጭንቅና
በኀዘን ከገነት ወጥቶ በተስደደ ጊዜ ከልቡነው ኅዘን
ተረጋግቶብሻልና።
፫ ለስእርተ ርእስኪ ። እመቤቴ ኪዳን ምህርት ሆይ ያለ
ማቋረጥ ሰማያዊ ጠል ለረበረበበትና የሐር ጉንጉን
ለሚመስለው ስእርተ ርእስሽ ሰላምታ ይገባል ።
የቃል ኪዳኗ እመቤቴ ሆይ ሞትን የሚያስከትል ፤እንደ ኤልያስ
ሥጋዊ ሕይወት ያይደለ የነፍሴን ሕይወት ይስጠኝ ዘንድ በታላቅ
ጉባዔ ፊት የምሕረት ቃል ኪዳን በገባልሽ ልጅሽ ዘንድ አማልጅ
ኣሜን።
እመቤታችን ኪዳን ምህርት ሆይ እኛ ሃጥያቶኞች ከልጅሽ
ከወዳጅሽ ከእየሱስ ከርስቶስ ኣስታሬቂን ሃጥያታችን የበዛ
ግብራችን የከፊ በሃጥያት ለኣፍንጫ የሚከረፍፍ ነውና ልጅሽ
በቸርነቱ እና በይቅርባይኖቱ ያጥበን ዘንድ ኣማልጅን ጾማችን
ጾሎታችንም ይቀበልልን ኣሜን ።
ወስብሃት ለእግዚአብሔር ወለወላዲቱ ድንግል ወለመስቀሉ
ክብር ኣሜን ካለ መኖር ወደ መኖር ያመጣን እግዚአብሔር
ክብር ምስጋና ይግባው ለቅድስተ ሰላሴ ኣሜን
ኢትየጽያ ሃገራችን ኦርቶዶክስ ሃይማኖታችን እግዚአብሔር
ይጠብቅልን ኣሜን ።
No comments:
Post a Comment