እመቤታቸን እና ሚሪና፡፡
ይህ ደንገተኛ ተዓምር የተከሰተዉ በሶርያ ነዉ፡፡
ወይዘሮ ሚሪና ኦርቶዶክስ እና ጠንካራ ክርስትያን
ናት፡፡መጸለይ በጣም የምትወደዉ ነገር ነዉ
በጣም፡፡ዘወትር በእግዚአብሔር ፊት መቆም
መጸለይ እንደዚሁም መዘመር ሁሌም
የምታደርገዉ ነገር ነዉ፡፡የምትጸልየዉ ለራሷ ብቻ
አይደለም ለሁሉ ሰዉ እንደዚሁም ለዓለም
ህዝቦች ነዉ በተለየይ ከእመቤታችን ሥዕል ፊት
መጸለይ ትወዳለች፡፡አንድ ቀን ግን ያልጠበቀችዉ
ነገር ተከሰተ ለታመመችዉ ጓደኛዋ ልትጸልይ ወደ
ከሌሎች ጓደኞቿ ጋር ሆና ወደ ታመመችዉ ቤት
ሄደች፡፡ከዚያም በእጇ ላይ ያልታበ ድንገተኛ
ብርሐን መታየት እና የዘይት መፍሰስ ተከሰተ
ስለሆነም የታመመችውን ጓደኛዋን ስትነካት
ተፈወሰች፡፡ሁሉም በጣም ተደነቁ፡፡ቀጥለውም
አጅበዋት ወደ ቤት ሄዱ ወደ ውስጥ እንደ ገቡ
ሁሌ ሚሪና የምትጸልይበት የእመቤታችን ሥዕል
ዘይት ማፍሰስ ጀመረ የሚፈሰውም ከእመቤታችን
አይኖች ነበር ደመና የከበበውም ይመስል
ነበር፤ሁሉም ከመደነቃቸዉ የተነሳ ለሚያውቋቸዉ
ሰዎች ሁሉ መናገር ጀመሩ ይህ ዜና ለሶርያ
ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ፓትርያርክ እንደዚሁም
ለግሪክ ኦርቶዶክስ ጳጳስ ለካቶሊካውያን ጳጳሳት
እንደዚሁም የድንግል ማርያም አማላጅነት
ለሚቀበሉ ሁሉ ተዳረሰ፡፡ከዚያም ልክ ጌታ
ሲሰቀል እንደ ነበረዉ የስቃይ ምልከት መታየት
ጀመሩ ማለትም ግንባሩ ላይ የነበሩት ቁስሎች
እንደዚሁም እጆቹ እግሮቹ ላይ በሚስማር
የተወጉበት ጎኑ ላይ የተወጋበት አይነት በሚሪና
አካላት ላይ መታየት ጀመሩ፡፡እነዚህ ምልክቶች
ሲታዬ በጣም ትታመም ነበር ከዚያም በራዕይ
ጌታችንን እና እመቤታችንን ታይ ነበር፡፡
መልዕክትም ይነግሯት እና ሰዉ ሁሉ ወደ ንሰሐ
እና ወደ ቅዱስ ቁርባን እንዲቀርቡ ለሰዉ ሁሉ
ከሰማይ የመጣውን መልዕክት ትናገር ነበር፡፡
በሶርያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስትያን
ፓትርያርክ ትዕዛዝ መሰረት በሶርያ ወደ ሚገኘዉ
የሰማዕታት አለቃ የቅዱስ ጊዮርጊስ ካቴድራል
እንድትመጣ እና እዚያ ከዘይቷ ለሰዉ ሁሉ
እንድትሰጥ ተነገራት እርሷም መጣች ታላላቅ
ተዓምራትም ተፈጸሙ ከሰማይ የመጣላትን
መልዕክቶች ለሰዉ ሁሉ ተናገረች፡፡የአምላክ
እናት ተገልጣላት መልዕክት ነገረቻት ‹‹‹ልጄ
ሚሪና ዘይት በፈሰሰበት ሥዕሌ ፊት ሁሉም ሰዉ
ሻማ አብርቶ ይጸልይ ጸሎቱም ይሰማል
አባዝታችሁም ለሰዉ ሁሉ አዳረርሱ እኔ በተባዛዉ
ሥዕል ላይ ተዓምራትን አደርጋለሁ››› አለቻት
ይህንንም መልዕክት ለሰዎች ተነናገረች ድንግል
እንዳለችወው ብዙ እና ድንቅ ተዓምራት ተገለጡ
እመቤታችን በወይዘሮ ሚሪና ላይ የገለጠችዉ ተዓምር
ከሶርያ አልፎ በዓለም ሁሉ ተዳረሰ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ
ካቶሊኩ እንደዚሁም ሌሎች እምነት ተከታዮች በድንግል
ማርያም ሥዕል ፊት ከዓለም ተሰባስበዉ መዘመር መጸለይ
ጀመሩ፡፡እናታችን ድንግል ማርያም የፍቅር እናት ስለሆነች
ከማንኛውም ኃይማኖት የመጣውን ሰዉ በፍቅር ፈውሳ ወደ
ቤቱ ትሸኘዋለች፡፡በወይዘሮ ሚሪና ቤት ጠባብ ቢሆንም
በድንግል ተዓምር ለሁሉም በቃ፡፡ ጌታችን እና እመቤታችን
እንደ ገና መልዕክት በህልሟ ነገሯት፡፡‹‹ጌታችን በትልቅ
ተራራ እና በሚያምር ገነት በሆነ ቦታ ላይ ታያት ስለሆነም
ጌታ እንዲህ አላት ‹‹‹ልጄ የተባረክሽ ነሽ አኔ ሰማይን እና
ምድር የሰውን ልጆች ሁሉ የፈጠርኩ ጌታ አምላክ ነኝ
ለሰውም ልጆች መዳን መከራን የተቀበልኩ ነኝ በደሜ
ፈሳሽነት ዓለም ድኗል›››ብሏት ተሰወረ፡፡ከዚያም ከጥቂት
ደቂቃዎች በኋላ ነቃች እመቤታችን እንደገና ከቤቷ አጠገብ
ባለዉ ዛፍ ላይ እንደምትገለጥ በድምጽ ነገረቻት ወደ ዛፉ
ሄደች በሚያስደነግጥ አእነና በሚያስፈራ ግርማ እመቤታችን
ከሰማይ ወረደች ሚሪናም በጣም ደነገጠች ወዲያውኑ
እየሮጠች ወደ ቤቷ ገባች በሚቀጥለዉ ቀን የእግዚአብሔር
መልዓክ መጥቶ ‹‹‹የጌታ እናትን ለምን ታቃልያለሽ እርሷ
መልዕክት ልትነግርሽ እና ሰውንም ልትባርክ ነበር በዛፉ ላይ
የተገለጠችዉ››› አላት ከትንሽ ደቂቃዎች በኋላ እመቤታችን
በህልም ተገልጣላት ‹‹‹ለምን ያልኩሽን አላደረግሽም?
አይንሽን ብርሐን እወስደዋለሁ፡፡›››አለቻ ት በመሆኑም
ሚሪና አይኗን ስትገልጥ ታውራ ነበር በጣም ደንግጣ
በኃይለኛዉ ማልቀስ ጀመረች ነገር ግን በሰራችዉ ስራ
ስለሆነም እመቤታችን ይቅርታ ጠየቀቻት በመታወሯም
አላማረረችም ነበር፡፡በሶስተኛውም ቀን ነጭ ብርሐን ማየት
ጀመረች ፊቷ በወይራ ቅዱስ ዘይት መሞላት ጀመረ ከአፏም
ዘይት ይወጣ ነበር ምንጩ አይታወቅም ግን ሚሪና ባለቤቷን
‹‹‹አፌን አሽትልኝ››› አለችዉ እርሱም ሲያሸተዉ እንደ አበባ
አይነት ልዬ መዓዛ ያለዉ ነበር ከዚያም አይኗን የሆነ እጅ 3
ጊዜ ሲነካት ማስታወክ ጀመረች የምታስታውከዉ ቅዱስ
ዘይት ነበር ምግብም ((ለ3 ቀን አልበላችም ምግቧ ጸሎት
ነበር))ከዚያም አይኗ በራ እናቷ እና ባለቤቷ ተደሰቱ እልል
ብለዉ አመሰገኑ፡፡ወይዘሮ ሚሪና የምትኖርበት ቤት
ሐዋርያዉ ቅዱስ ጳውሎስ ለ3 ቀን ታውሮ ለተቀመጠበት
ቤት ቅርብ ነዉ ይህን ነገር ከሚሪና ጋር በመገጣጠሙ ካህናቱ
ተደሰቱ፡፡እመቤታችንም ለሚሪና ተገልጣላት ‹‹‹ልጄ አሁን
ከስህተትሽ ተምረሻል ስለዚህ ስጦታ እሰጥሻለሁ››› አለቻት
ይህ ነገር ሚሪና አልገባትም ነበር ነገር ግን ከጥቂት ወራት
በኋላ የአንዲት ቆንጆ ሴት ልጅ እናት ሆነች፡፡ከቀን ወደ
ቀንም የወይዘሮ ሚሪና መልክ እያማረ መሄድ ጀመረ፡፡
በቀጣዩ ቀን በሰማዕታት አለቃ በቅዱስ ጊዮርጊስ ካቴድራል
የሶርያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስትያነን እንደምትመጣ
ተነገረ 10,000 ያህል ሰዉ ተሰበሰበ በዚህም ሁኔታ ላይ
እያለች ከፊቷ ከእጇ ከአይኗ ዘይት መውጣት ጀመረ ከዚያም
የአምላክ እናት ድንግል ማርያም ተገለጠችላት መልዕክትም
ነገረቻት ‹‹‹‹‹‹‹‹ ቤተክርስትያን በምድር ላይ ያለች መንግስተ
ሰማያት ነች፡፡በህዝቡ መሰባሰብ ላይ አምላካችን
እግዚአብሔር በጣም ደስተኛ ነዉ በዚህ፡፡እኔም የኔ
ትውልዶች የሆኑትን ሁሉ ባንቺ ምሳሌነት
አስተምራቸዋለሁ፡፡›››› ›››› አለቻት ይህንን መልዕክት
ለሰዉ ሁሉ አባ ማሉሊ በተባለ ካህን አማካኝነት አስተላለፈች
ይህ አባት የምትናገራቸውንም መልዕክቶች በሙሉ ይጽፍ
ነበር፡፡ወይዘሮ ሚሪና ከንቱ ውዳሴ ስለመማትወድ ቶሎ ብላ
ወደ ቤቷ ትመለስ ነበር፡፡ከስር የምትመለከቱት ፎቶ የቅዱስ
ዘይቱ መፍሰስ ነዉ፡
No comments:
Post a Comment