=>+"+ እንኩዋን ለዕለተ "ማዕዶት" እና ለቅዱስ "ፃና
ሰማዕት" ዓመታዊ የዕረፍት በዓል በሰላም አደረሳችሁ +"+
+*" ማዕዶት "*+
=>ማዕዶት ማለት (ዐደወ-ተሻገረ) ከሚል የግእዝ ግስ
የተወረሰ ሲሆን በጥሬው "መሻገር" ማለት ነው:: ይሕም
በደመ ክርስቶስ ተቀድሰን: በትንሳኤውም ድኅነት ተደርጐልን
መከራን: መርገምን: የኃጢአትን ባሕር: አንድም ባሕረ እሳትን
መሻገራችንን ያመለክታል::
+ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በከበረ ደሙ
*ከባርነት ወደ ነጻነት
*ከጨለማ ወደ ብርሃን
*ከሞት ወደ ሕይወት
*ከኃጢአት ወደ ጽድቅ
*ከሲዖል ወደ ገነት
*ከገሐነመ እሳት ወደ መንግስተ ሰማያት
አዳምንና እኛን ልጆቹን አሸጋግሮናል::
+አባታችን አዳምና ልጆቹ ከሲዖል የወጡት በዕለተ ዐርብ
በሠርክ ቢሆንም ቅድስት ቤተ ክርስቲያን በዚሕ ዕለት
እዲታሰብ ታዛለች::
+ጌታችን ምርኮን ማርኮ: ጥጦስ መንገድ ጠራጊ ሆኖለት ወደ
ገነት ሲያስገባቸው ለድንግል ማርያም አሳይቷታል:: እመ
አምላክም በፍጹም ልቧ ደስ ተሰኝታለች:: አዳምና ልጆቹ
እመቤታችንን ከላይ ሆነው እጅ ነስተዋታል:: እርሷ
የድኅነታቸው ምክንያት ናትና::
=>አማናዊው ብርሃን መድኃኔ ዓለም ክርስቶስ ጨለማችንን
በምሕረቱ ያብራልን::
=>+"+ ክርስቶስም እኮ ስለ ሰው ኃጢአት አንድ ጊዜ
ሞቶአል:: ኃጢአት የሌለበት ክርስቶስ ጻድቁ ስለ እኛ ሞተ:: ስለ
ኃጢአታችን እኛን ወደ እግዚአብሔር ያቀርበን ዘንድ::
በሥጋ ሞተ: በመንፈስ ግን ሕያው ነው:: ነፍሳቸው ታስራ ወደ
ነበረችበት ሔደ:: ቀድሞ ክደውት ለነበሩት ነጻነትን
ሰበከላቸው:: +"+ (1ዼጥ. 3:18)
+*" ቅዱስ ፃና "*+
=>በቤተ ክርስቲያናችን በዚህ ስም የሚጠሩ ቅዱሳን አሉ:: ዛሬ
የምናከብረው ሰማዕቱ ቅዱስ ፃና:-
*በዘመነ ሰማዕታት የነበረ:
*ቅዱስ ኤስድሮስ የሚባል ደግ ጉዋደኛ የነበረው:
*ሁለቱንም እናቶቻቸው እንደሚገባ ያሳደጉዋቸው የ3ኛው መቶ
ክ/ዘመን ክርስቲያኖች ነበሩ::
+በወጣትነት ዘመናቸው በድንግልና: ቅዱስ ፃና የሠራዊት
አለቃ: ቅዱስ ኤስድሮስ ደግሞ የልብስ ዝግጅት ባለሙያ ነበሩ::
ከሚያገኙት ገቢ ለዕለት ጉርስ ብቻ እያስቀሩ ለነዳያን
ይመጸውቱ ነበር::
+በመከራ ዘመን (ዘመነ - ሰማዕታት) ቅዱሳኑ ያላቸውን ሁሉ
ለነዳያን አካፍለው በክርስቶስ ስም መሞትን መርጠዋል::
አስቀድሞ ቅዱስ ኤስድሮስ አንገቱን ተሰይፎ የክብርን አክሊል
ተቀዳጅቷል::
+ሰማዕቱ ቅዱስ ፃና ባልንጀራው ኤስድሮስ ከተገደለ በሁዋላ
ለ36 ቀናት በጨለማ እሥር ቤት ውስጥ ከብዙ ስቃይ ጋር
ቆይቷል:: መከራን ቢያፀኑበትም በሃይማኖቱ ጽኑ ነበርና
እርሱንም በዚሕች ቀን ገድለውታል::
+ደግ እናቱ በቦታው ነበረችና መላዕክት በክብር ነፍሱን
ሲያሳርጉ ተመልክታለች::
=>ፈጣሪ ከሰማዕቱ ክብር ያድለን::
=>ሚያዝያ 24 ቀን የሚከበሩ ዓመታዊ የቅዱሳን በዓላት=
1.ቅዱስ ፃና ሰማዕት
2.አባ ሱንቱዩ ሊቀ ዻዻሳት
3.አባ ይድራ
4.የደብረ ሲና ቅዳሴ ቤት
=>ወርኀዊ በዓላት
1.ቅዱስ አቡነ ተክለ ሃይማኖት
2.ቅዱስ አጋቢጦስ (ጻድቅ ኤዺስቆዾስ)
3.ቅድስት ክርስቶስ ሠምራ
4.ቅዱስ ሙሴ ፀሊም
5.ቅዱስ ቶማስ ዘመርዐስ
6.ቅዱስ አብላርዮስ ታላቁ
7."24ቱ" ካኅናተ ሰማይ (ሱራፌል)
8.አቡነ ዘዮሐንስ ጻድቅ (ኢትዮዽያዊ)
=>+"+ ልጆች ሆይ እናንተ ከእግዚአብሔር ናችሁ:
አሸንፋችሁአቸውማል:: በዓለም ካለው ይልቅ በእናንተ ያለው
ታላቅ ነውና:: እነርሱ ከዓለም ናቸው:: ስለዚህ ከዓለም
የሆነውን ይናገራሉ:: ዓለሙም ይሰማቸዋል:: እኛ
ከእግዚአብሔር ነን:: እግዚአብሔርን የሚያውቅ ይሰማናል::
ከእግዚአብሔር ያልሆነ አይሰማንም:: +"+ (1ዮሐ. 4:4)
<ወስብሐት ለእግዚአብሔር>
ሰማዕት" ዓመታዊ የዕረፍት በዓል በሰላም አደረሳችሁ +"+
+*" ማዕዶት "*+
=>ማዕዶት ማለት (ዐደወ-ተሻገረ) ከሚል የግእዝ ግስ
የተወረሰ ሲሆን በጥሬው "መሻገር" ማለት ነው:: ይሕም
በደመ ክርስቶስ ተቀድሰን: በትንሳኤውም ድኅነት ተደርጐልን
መከራን: መርገምን: የኃጢአትን ባሕር: አንድም ባሕረ እሳትን
መሻገራችንን ያመለክታል::
+ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በከበረ ደሙ
*ከባርነት ወደ ነጻነት
*ከጨለማ ወደ ብርሃን
*ከሞት ወደ ሕይወት
*ከኃጢአት ወደ ጽድቅ
*ከሲዖል ወደ ገነት
*ከገሐነመ እሳት ወደ መንግስተ ሰማያት
አዳምንና እኛን ልጆቹን አሸጋግሮናል::
+አባታችን አዳምና ልጆቹ ከሲዖል የወጡት በዕለተ ዐርብ
በሠርክ ቢሆንም ቅድስት ቤተ ክርስቲያን በዚሕ ዕለት
እዲታሰብ ታዛለች::
+ጌታችን ምርኮን ማርኮ: ጥጦስ መንገድ ጠራጊ ሆኖለት ወደ
ገነት ሲያስገባቸው ለድንግል ማርያም አሳይቷታል:: እመ
አምላክም በፍጹም ልቧ ደስ ተሰኝታለች:: አዳምና ልጆቹ
እመቤታችንን ከላይ ሆነው እጅ ነስተዋታል:: እርሷ
የድኅነታቸው ምክንያት ናትና::
=>አማናዊው ብርሃን መድኃኔ ዓለም ክርስቶስ ጨለማችንን
በምሕረቱ ያብራልን::
=>+"+ ክርስቶስም እኮ ስለ ሰው ኃጢአት አንድ ጊዜ
ሞቶአል:: ኃጢአት የሌለበት ክርስቶስ ጻድቁ ስለ እኛ ሞተ:: ስለ
ኃጢአታችን እኛን ወደ እግዚአብሔር ያቀርበን ዘንድ::
በሥጋ ሞተ: በመንፈስ ግን ሕያው ነው:: ነፍሳቸው ታስራ ወደ
ነበረችበት ሔደ:: ቀድሞ ክደውት ለነበሩት ነጻነትን
ሰበከላቸው:: +"+ (1ዼጥ. 3:18)
+*" ቅዱስ ፃና "*+
=>በቤተ ክርስቲያናችን በዚህ ስም የሚጠሩ ቅዱሳን አሉ:: ዛሬ
የምናከብረው ሰማዕቱ ቅዱስ ፃና:-
*በዘመነ ሰማዕታት የነበረ:
*ቅዱስ ኤስድሮስ የሚባል ደግ ጉዋደኛ የነበረው:
*ሁለቱንም እናቶቻቸው እንደሚገባ ያሳደጉዋቸው የ3ኛው መቶ
ክ/ዘመን ክርስቲያኖች ነበሩ::
+በወጣትነት ዘመናቸው በድንግልና: ቅዱስ ፃና የሠራዊት
አለቃ: ቅዱስ ኤስድሮስ ደግሞ የልብስ ዝግጅት ባለሙያ ነበሩ::
ከሚያገኙት ገቢ ለዕለት ጉርስ ብቻ እያስቀሩ ለነዳያን
ይመጸውቱ ነበር::
+በመከራ ዘመን (ዘመነ - ሰማዕታት) ቅዱሳኑ ያላቸውን ሁሉ
ለነዳያን አካፍለው በክርስቶስ ስም መሞትን መርጠዋል::
አስቀድሞ ቅዱስ ኤስድሮስ አንገቱን ተሰይፎ የክብርን አክሊል
ተቀዳጅቷል::
+ሰማዕቱ ቅዱስ ፃና ባልንጀራው ኤስድሮስ ከተገደለ በሁዋላ
ለ36 ቀናት በጨለማ እሥር ቤት ውስጥ ከብዙ ስቃይ ጋር
ቆይቷል:: መከራን ቢያፀኑበትም በሃይማኖቱ ጽኑ ነበርና
እርሱንም በዚሕች ቀን ገድለውታል::
+ደግ እናቱ በቦታው ነበረችና መላዕክት በክብር ነፍሱን
ሲያሳርጉ ተመልክታለች::
=>ፈጣሪ ከሰማዕቱ ክብር ያድለን::
=>ሚያዝያ 24 ቀን የሚከበሩ ዓመታዊ የቅዱሳን በዓላት=
1.ቅዱስ ፃና ሰማዕት
2.አባ ሱንቱዩ ሊቀ ዻዻሳት
3.አባ ይድራ
4.የደብረ ሲና ቅዳሴ ቤት
=>ወርኀዊ በዓላት
1.ቅዱስ አቡነ ተክለ ሃይማኖት
2.ቅዱስ አጋቢጦስ (ጻድቅ ኤዺስቆዾስ)
3.ቅድስት ክርስቶስ ሠምራ
4.ቅዱስ ሙሴ ፀሊም
5.ቅዱስ ቶማስ ዘመርዐስ
6.ቅዱስ አብላርዮስ ታላቁ
7."24ቱ" ካኅናተ ሰማይ (ሱራፌል)
8.አቡነ ዘዮሐንስ ጻድቅ (ኢትዮዽያዊ)
=>+"+ ልጆች ሆይ እናንተ ከእግዚአብሔር ናችሁ:
አሸንፋችሁአቸውማል:: በዓለም ካለው ይልቅ በእናንተ ያለው
ታላቅ ነውና:: እነርሱ ከዓለም ናቸው:: ስለዚህ ከዓለም
የሆነውን ይናገራሉ:: ዓለሙም ይሰማቸዋል:: እኛ
ከእግዚአብሔር ነን:: እግዚአብሔርን የሚያውቅ ይሰማናል::
ከእግዚአብሔር ያልሆነ አይሰማንም:: +"+ (1ዮሐ. 4:4)
<ወስብሐት ለእግዚአብሔር>
No comments:
Post a Comment