ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ነኝ

ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ነኝ
ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ነኝ

Monday, May 2, 2016

#ገድለ_ሊቀ_ሰማዕታት_ቅ ዱስ_ጊዮርጊስ

23 23 23 23 23
#ከገድለ_ሊቀ_ሰማዕታት_ቅ ዱስ_ጊዮርጊስ
23 23 23 23 23
እንኳን ለሰማዕቱ ቅዱስ ጊዮርጊስ ዓመታዊ በዓል አደረሳችሁ!!!
23
በጥር 20 ቀን በ277 ዓ.ም ተወለደ። ሀገሩ ፍልስጤም ሲሆን
ልዩ ስሟ ልዳ ይባላል። ጊዮርጊስ ማለት ኮከብ፣ ብሩህ፣
ሐረገወይን፣ ፀሐይ ማለት ነው። አባቱ ዘሮንቶስ (አንስጣስዮስ)
ይባላል ከልዳ መኳንንት ተሹሞ ይኖር ነበር፤ እናቱ ቴዎብስታ
(አቅሌስያ) ትባላለች። ማርታና እስያ የሚባሉ እህቶች ነበሩት።
10 ዓመት ሲሞላው አባቱ ስለሞተ ሌላ ደግ ክርስቲያናዊ
መስፍን ከቤቱ ወስዶ አሳደገው። በጦር ኃይልም አሠለጠነው።
20 ዓመት ሲሞላው የ15 ዓመት ልጅ ሊያጋቡት ሲሉ
እግዚአብሔር የመስፍኑን ነፍስ ወስደ፤ ቅዱስ ዮርጊስም ወደ
ቤሩት ሄደ።
በቤሩት ደራጎን ን ያመልኩና ሴት ልጃቸውን ይገብሩለት ነበርና
በኃይለ መስቀል ድል ነስቶት ህዝቡን ወደ አምልኮተ
እግዚአብሔር አስገብቷቸዋል።
23
ወደፋርስ ቢመለስ ዱድያኖስ ሰባ ነገሥታት ሰብስቦ ሰባ ጣዖታት
አቁሞ
ሲሰግድ ሲያሰግድ ቢያገኛቸው ለሃይማኖቱ ቀናዒ ነውና
ከቤተመንግስቱ
ገብቶ “እኔ ክርስቲያን ነኝ በኢየሱስ ክርስቶስ አምናለሁ”
አለው። እርሱም
ማንነቱን ከተረዳ በኋላ “አንተማ የኛ ነህ በ10 አህጉር ላይ
እሾምሃለሁ
የኔን አምላክ አጵሎንን አምልክ” አለው። ቅዱስ ጊዮርጊስም
“ሹመት
ሽልማትህ ለአንተ ይሁን እኔ አምላኬ ኢየሱስ ክርስቶስን
አልክድም”
አለ። በዚህ ጊዜ እጅግ ተናዶ መከራን አጸናበት እርሱ ግን “ይህን
ከሀዲ
እስካሳፍረው ድረስ ነፍሴን አትውሰድ” በማለት እግዚአብሔርን
የለመነና
እንደጸሎቱ የተደረገለት። በእምነቱም ጽናት የሰው ልጅ
ሊሸከም
የማይችለውን መከራ የተቀበለ ቅዱስ አባት ነው። ከእነዚህም
መከራዎች
ውስጥ:-
-
1. በእንጨት አስቀቅሎ ሥጋውን በመቃን አስፈተተው
2. ረጃጅም ችንካሮች ያሉበት የብረት ጫማ አጫምቶት ሂድ
አለው።
ቅዱስ ሚካኤልን ልኮለት ፈውሶታል።
3. በሰባ (70) ችንካር አስቸንክሮ በእሳት አስተኩሶ አናቱን
በመዶሻ
አስቀጥቅጦ በሆዱ ላይ የደንጊያ ምሰሶ አሳስሮ
እንዲያንከባልሉት
አደረገ።
4. ሥጋውን በመጋዝ አስተልትሎ ጨው ነስንሶበት ሥጋው
ተቆራርጦ
ወደቀ። ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በመንፈቀ
ሌሊት
በእጁ ዳስሶ “ገና 6 ዓመት ለስሜ ትጋደላለህ፣ 3 ጊዜ
ትሞታለህ፣ በ4ኛው ታርፋለህ።” አለው።
5. ዱድያኖስ ደንግጦ “የሚያሸንፍልኝ ቢኖር ወርቅ
እሰጠዋለሁ”
ቢል አትናስዮስ የተባለ መሰርይ ከንጉሱ ላምን በጆሮዋ
ሲያንሾካሹክባት ለሁለት ተሰንጥቃ ገድሏት ፈቃድን ተቀበለ።
ሆድ
በጥብጦ አንጀት ቆራርጦ የሚገድል መርዝ ቀምሞ አስማተ
ሰይጣን ደግሞ ሰጠው። ቅዱስ ጊዮርጊስ ግን ስመ
እግዚአብሔርን ጠርቶ ቢጠጣው እንደ ጨረቃ ደምቆ እንደ
አበባ
አሸብርቆ ተገኝቷል። ጠንቋዩም ማረኝ ብሎት ከመሬት ውሃን
አፍልቆ ወደ ጌታችን ቢያመለክት ሐዋርያው ቶማስን በመንፈስ
መጥቶ አጥምቆት በሰማዕትነት አርፏል።
6. በመንኮራኩር አስፈጭቶ ከትልቅ ጉድጓድ ጥሎት ደንጊያ
ዘግቶበት አትሞበት ሄዷል። ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ
ክርስቶስ የተፈጨውን ሥጋ በእጁ ዳስሶ መንፈሱን መልሶ
አንስቶታል፤ ተመልሶም “አምላኬ ከሞት አዳነኝ” ብሏቸዋል።
7. በብረት አልጋ አስቸንክሮ ከበታቹ እሳት አንድዶበታል።
እሳቱም
ደሙ ሲንጠባጠብ ጠፍቷል።
8. ዱድያኖስ “ኢየሱስ አምላክ መሆኑን አሳየኝ” ቢለው
የለመለሙትን ዕፅ አድርቆ፣ የደረቁትን አለምልሞ፣ ከሞቱ
430
ዓመት የሆናቸውን ሙታንን አስነስሰቶ አሳይቶታል። ነገር ግን
ልቡ
ክፉ ነውና በረሀብና በጽም ይሙት ብሎ ምንም ከሌላት መበለት
ቤት አሳስሮታል። እርሷም የሚቀመስ ስትፈልግ ቤቷን በእህል
አትረፍርፎ የታሰረበት ግንድ አፍርቶ ልጇ ጆሮው የማይሰማ
ነበርና
ፈውሶላት መበለቲቷን ከነልጆቿ አጥምቆ ቅዱስ ሚካኤል
ከእስራቱ
ፈትቶት ተመልሷል።
9. ዳግም በመንኩራኩር ፈጭታችሁ ደብረ ይድራስ ወስዳችሁ
ዝሩት
ብሎ አስፈጭቶ ሥጋውን ቢዘሩት ሥጋው ያረፈበት ሳር፣ ቅጠሉ፣
ደንጊያው፣ እንጨቱ ሁሉ “ጊዮርጊስ ቅዱሱ ለእግዚአብሔር፣
ጊዮርጊስ ሰማዕቱ ለእግዚአብሔር፣” እያሉ አመስግነዋል።
ጌታችን
መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስም ለሦስተኛ ጊዜ ከሞት
አስነስቶታል። ሔዶም “አምላኬ ከሞት አዳነኝ” አላቸው።
ጭፍሮቹ ደንግጸው ከእግሩ ስር ወደቁ። ከመሬት ውሃ
አመንጭቶ
ቅዱስ ዮሐንስ አጥምቋቸዋል።
10. “ንጉሡ ልሹምህ ለአጵሎን ስገድ” ብሎ ቢለምነው እሺ
ብሎ
ገብቶ ሲጸልይ የንጉሱ ሚስት እለእስክንድርያ “ምን እያልክ
ነው?”
ብትለው አስተምሯት አሳምኗታል። ሲነጋ ንጉሱ በአዋጅ ህዝብን
አሰብስቦ “ጊዮርጊስ ለጣዖቴ ሊሰግድ ነው’ ብሎ በተሰበሰበ
ህዝብ መካከል አንድን ብላቴና (የመበለቷን ልጅ) “የክርስቶስ
ኢየሱስ አገልጋይ ጊዮርጊስ ይጠራሃል” በል ብሎ ወደጣዖቱ
ቢልከው ጣዖቱ ላይ ያደረው ሰይጣን እየጮኸ ቅዱስ ጊዮርጊስ
ያለበት ቦታ መጣ፤ አምላክ አለመሆኑን አናዞት መሬት ተከፍታ
እንድትውጠው አደረገ። ብዙ ሰዎች ይህንን ተዓምር አይተው
አመኑ። ንጉሱን ሚስቱ እንዲመለስ ብትነግረው በአደባባይ
አሰቅሎ አሰይፏት ሞታለች ደሟን ጥምቀት አድርጎላት ሰማዕት
ሆናለች።
11. በመጨረሻም በሰይፍ እንዲመተር አስደረገ። ቅዱስ
ጊዮርጊስም
ከጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ቃልኪዳን
ተገብቶለታል።
። ። ። ። ። ። ።
- ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ: ሰባት አክሊላትን አቀዳጅቶታል።
- ጌታችን: አባቴ ስምህን በሠረገላ መንፈስ ቅዱስ ጽፎታልና
አምላከ ጊዮርጊስ እርዳኝ የሚለውን ሁሉ እኔ ፈጥኜ
እሰማዋለሁ አለው።
- ጌታችን ወንድም ሴትም ቢሆኑ በችግር ላይ ሆነው እጅግ
ተስፋ ቢቆርጡ: ይልቁንም የሰዎች ልጆች በሚያዙንበት በጽኑ
መከራ ቢወድቁ በቅዱስ ስምህ ተማጥነው:- ሦስት ጊዜ
አምላከ ጊዮርጊስ ርዳን:
አምላከ ጊዮርጊስ ርዳን:
አምላከ ጊዮርጊስ ርዳን: እያሉ ወደኔ ቢጮሁ ያን ጊዜ
ራራላቸዋለሁ ፈጥኜም ለጸሎታቸው መልስ እሰጣቸዋለሁ:
ከልባቸው የለመኑኝን ሁሉ እፈጽምላቸዋለሁ ከመከራቸውም
አድናቸዋለሁ አለው።
-ጌታችን: ስለ ስሜ የተቀበልከውን መከራ: ያገኘህን ድካም
ገድልህን የሚናገረውን መጽሐፍ የሚጽፈውን ሁሉ ስሙን
በሕይወት መጽሐፍ እጽፈዋለሁ ኃጢአቱንም አስተሰርይለታለሁ
በመንግሥተ ሰማያትም ያንተ ልጅ አደርገዋለሁ: ለዘለዓለም
በአንድነት ከአንተ ጋር አኖረዋለሁ አለው።
- ጌታችን: በሃይማኖት ወንድ ልጁን: ሴት ልጁን በስምህ
የጠራውን እኔ እባርከዋለሁ: ለዘለዓለም ከርሱ ጋር እኖራለሁ
ልቡን ደስ አሰኘዋለሁ አለው።
- ጌታችን: ለቤተክርስቲያን ዕጣን: መብራት: ስንዴ: ወይን
የሚሰጥ በስምህ ለተራበ የሚያበላ: ለተጠማ የሚያጠጣ
የከበረችውን የመታሰቢያህን ቀን የሚያከብረውን እኔ በዚህ
ዓለም እረዳዋለሁ: በሚመጣውም ዓለም ከአንተ ጋር
በመንግሥቴ ደስ እንዲለው አደርጋለሁ። በስምህ ለተራቆተ
የሚያለብሰውን እኔ የክብር ልብስ አለብሰዋለሁ:
ለቤተክርስቲያን በስምህ መብራት የሚያበራውን: ዕጣን
የሰጠውን መላእክት እንዲያበሩለት አደርጋለሁ: ወደ እኔም ደስ
ብሎት ይመጣል። በስምህ እንግዳ የሚቀበለውን እኔ ኃጢአቱን
አስተሰርይለታለሁ: ለዘለዓለም በመንግሥቴ እቀበለዋለሁ።
በስምህ ምጽዋት የመጸወተውን እኔ ከቅዱሳን ጋር
እቆጥረዋለሁ ከዚህ ዓለም ሀብትም ምንም እንዳያጣ
አደርገዋለሁ። እኔ ፈጣሪህ እግዚአብሔር ነኝ ከአንደበቴ
የወጣውን እፈጽማለሁ እንጂ አልለውጥም አለው።
- ሥሉስ ቅዱስ አብ ወልድ መንፈስ ቅዱስ ፈጥረው በሰባት
አክሊላት ከለሉት በቸርነታቸው የአመነች ነፍስ ሁሉ ከሥጋዋ
በተለየች ጊዜ አስቀድማ ለሥሉስ ቅዱስ ትስገድ ከዚህ በኋላ
ውሰዷትና ለወዳጃችን ለጊዮርጊስ እጅ ትንሣ ብለው ከፍ ከፍ
አደረጉት። ነገር ግን ይህ ሁሉ የተናገርነው ምስጋናው ከክብሩ
ያንሳል ከታላቅ ባሕር አንድ ጭልፋ እንደሚቀዳ ይሆናል የዚህ
ሰማዕት ምስጋናው ክብሩ ብዙ ነውና ጸሎቱና በረከቱ ከ..............
............... ... ለዘለዓለሙ ይኑር አሜን።
። ። ። ። ። ። ።
በ27 ዓመቱ በሚያዝያ 23 ቀን በ9፡00 ሰዓት ሰማዕት ሆኗል።
አንገቱ ሲቆረጥ ውሃ፣ ደም እና ወተት ወጥቷል። ከሊቀ
ሰማዕታት ቅዱስ ጊዮርጊስ ረድኤት በረከት ይክፈለን!!!
23 23 23
። ። ። ። ። ። ።
#የአድዋ_ድል_ከእግዚአብሔ ር #የተገኘ_ድል_ነው
-
አንድ አምላክ በሚሆን በአብ በወልድ በመንፈስ ቅዱስ ስም
አሜን የካቲት 23 ልመናው ጸሎቱ በረከቱ አማላጅነቱ
በዕውነት ይደረግልንና የልዳው ፀሐይ ፍጡነ ረድኤት ቅዱስ
ጊዮርጊስ በጦርነት ላይ ሳለ ሣህለ ማርያምን (ዐፄ ሚኒልክን)
በመርዳት ያደረገው ተአምር ይህ ነው፡
‹‹ከጌታችን ከኢየሱስ ክርስቶስ ልደት 1854 ዓመት በኋላ
የኢትዮጵያ ነጉሠ ነገሥት ዳግማዊ ምኒልክ በነገሠ በ26ኛ
ዓመት የምኒልክ የጦር አለቃ ገበየሁ ድል ካደረጋቸው በኋላ
እንደገና ምኒልክን ወግተው ኢትዮጵያን በቅኝ አገዛዝ ሊገዙ
የሮም ሰዎች መጡ፡፡
ከዚህም በኋላ የኢትዮጵያው ንጉሠ ነገሥት ዳግማዊ ዐፄ
ምኒልክ
‹አገሬ ኢትዮጵያን እወዳለሁ የሚል ኢትዮጵያዊ ሁሉ በአስቸኳይ
ይነሣ፣
መስቀለ ሞቱንም ተሸክሞ ይከተለኝ፡፡ እግዚአብሔር
የወሰነልንን የባሕር
ወሰን አልፎ አገር የሚያጠፋ፣ ሃይማኖት የሚለውጥ ጠላት
መጥቷልና›
ሲል አዋጅ አስነገረ፡፡ ዳግመኛም በፈረሶቻቸው መጣብር ላይ
በጦራቸው
ላይ በጋሻቸው ላይ የመስቀል ምልክት እንዲያደርጉ ወታደሮቹን
አዘዛቸው፡፡ መስቀል ጠላትን ድል አድራጊ እንደሆነ አስቀድሞ
ያውቅ
ነበርና፡፡ ከዚያም ተነሥቶ ወደ ትግራይ ክፍለ ሀገር ዘመተና
ከትግራይ
አውራጃዎች አንዷ የምትሆን አድዋ ከምትባል አገር ደረሰ፡፡
የሣህለ ማርያም (ዐፄ ሚኒልክ) ሚስት ወለተ ሚካኤል (እቴጌ
ጣይቱም) በንጉሡ ትእዛዝ ታቦተ ቅዱስ ጊዮርጊስን አሲዛ ከሊቀ
ጳጳሱ
ከአባ ማቴዎስ እንዲሁም ከቀሳውስቱና ከመነኮሳቱ ጭምር
ከንጉሡ ጋር
ወደ ጦርነቱ ተጓዘች፡፡ በዚያም ጊዜ የአክሱም ጽዮን መነኮሳትና
ካህናት
የእመቤታችንን ሥዕል ይዘው ወደ ንጉሡ ወደ ምኒልክ
መጥተው ከሊቀ
ጳጳሱ ከእነ አቡነ ማቴዎስ ጋር ተቀላቀሉ፡፡ ከዚያም ሌሊቱን
ሙሉ ጸሎተ
ምሕላ ሲያደርሱ አደሩ፡፡ ቅዳሜ ማታ ለእሑድ አጥቢያ
ይኸውም የካቲት
22 ቀን ነው ንጉሡ ሣህለ ማርያም (ዐፄ ሚኒልክ) የጦር
ልብሱን ለብሶ
ከሠራዊቱ ጋር ወደ ጦር ግንባር ሄደ፡፡ ከዚያም ከሮማውያን
የጠላት ጦር
ጋራ ተገናኝቶ ከሌሊቱ በዓሥራ አንድ ሰዓት ጦርነቱን ጀመረ፡፡
የንጉሥ ሣህለ ማርያምን ሚስት ወለተ ሚካኤል (እቴጌ
ጣይቱም) ሌሊት
በታቦተ ቅዱስ ጊዮርጊስና በእመቤታችን ሥዕል ፊት በጸሎትና
በስግደት
እያደረች ሲነጋ ወደ ጦርነቱ ቦታ በመሄድ እጅግ በሚያስደንቅ
የአነጋገሯ
ኃይለ ቃል በጦርነቱ መካከል እየተገኘች ለንጉሡ ወታደሮች
የሞራልና
የብርታት ድጋፍ ትሰጣቸው ነበር፡፡ በዕውነትም ለተመለከታት
ሁሉ
እንደኃይለኛ ተጋዳይ አርበኛ ትመስል ነበረ እንጂ የሴቶች
የተፈጥሮ
ባሕርይ በእርሷ ላይ አይታይባትም ነበር፡፡ የንጉሡም ወታደሮች
የንግሥቲቱን የጀግንነት አነጋገር በሰሙ ጊዜ በእሳት ላይ
እንደተጣደ
የብረት ምጣድ ልባቸው ጋለ፡፡ ይልቁንም ላም እንዳየ አንበሳና
ፍየል
እንዳየ ነብር እየተወረወሩ በጦርነቱ መካከል በመግባት
የጠላትን ጦር
በሰይፍ ይጨፈጭፉት ነበር፡፡ መጽሐፍ ‹ሹመቱን ሽልማቱን ያየ
አርበኛ
ከጦርነት ከሰልፍ ወደኋላ አያፈገፍግም› ብሎ ተናግሯልና፡፡
በዚያንም ጊዜ ንጉሡ ሣህለ ማርያም (ሚኒልክ) በጦርነቱ
መካከል ሳለ
ሊቀ ጳጳሱ አቡነ ማቴዎስ እንዲሁም የአክሱም መነኮሳት
ሌሎቹ ካህናት
በሙሉ ታቦተ ቅዱስ ጊዮርጊስንና ሥዕለ ማርያምን ይዘው
ከንጉሡ
በስተኋላ በደጀንነት ቆመው ጸሎተ ምሕላ ያደርሱ ነበር፡፡
ንግሥቲቱ
ወለተ ሚካኤል በጸሎት ጊዜ በመዓልትም በሌሊትም ከእነርሱ
አትለይም
ነበር፡፡ የጽዮን አገልጋዮችም በእግዚአብሔር በሕጉ ታቦት ፊት
መለከት
ይነፉ ነበር፡፡ በዚህም ዕለት ይኸውም የካቲት 23 ቀን
በሮማውያንና
በኢትዮጵያውያን መካከል ከፍተኛ ጦርነት ሆነ፡፡ ወዲያውም
በሰማይ
ታላቅ ተአምር ተደረገ፡፡ ይኸውም የቀስተ ደመና ምልክት
ታየ፡፡ ከዚያም
ቀስተ ደመና ውስጥ መልኩ አረንጓዴ የሚመስል ጢስ ይወጣ
ነበር፡፡
ከዚያም ጢስ ውስጥ እንደክረምት ነጎድጓድ ያለ ድምፅ ተሰማ፡፡
ከዚያም
የነጎድጓድ ድምፅ የተነሣ በሮማውያን ወታደሮች ዘንድ ከፍተኛ
ድንጋጤና
ሽብር ሆነ፡፡ ለመዋጋትም አልቻሉም፡፡ ይልቁንም ኃያሉ ገባሬ
ተአምር
ቅዱስ ጊዮርጊስ በአምባ ላይ ፈረስ ተቀምጦ ከነፋስ ሩጫ ይልቅ
እየተፋጠነ በአየር ላይ በተገለጠ ጊዜ በግንባራቸው ፍግም እያሉ
ወደቁ፡፡ ‹የኢትዮጵያ ሕዝብ አምላካቸው ሊረዳቸው መጣ፡፡
እንግዲህ
ማን ያድነናል› አሉ፡፡ ምድር ጠበበቻቸው፡፡ በዚህም ጊዜ
የአትዮጵያ
ሠራዊት የሮምን የጦር ሠራዊት ፈጁዋቸው፡፡ የተረፉትንም
ማረኳቸው፡፡
ፈጽመውም እስኪያጠፏቸው ድረስ በሮማውያን ላይ
በእግዚአብሔር
ሥልጣን የኢትዮጵያውያን እጅ እየበረታች ሄደች፡፡ ከዚህም በኋላ
ንጉሡ
ሣህለ ማርያም በእግዚአብሔር ኃይልና በተአምራት አድራጊው
በቅዱስ
ጊዮርጊስ ተራዳኢነት የሮማውያንን የጦር ሠራዊት በጦርነት
ድል አድርጎ
የድል አክሊል ተቀዳጀ፡፡
23
ስለዚህም ‹በዳዊት የምስጋና ቃል የድል ዘውድ ያቀዳጀኝን
እግዚአብሔርን ባለ ዘመኔ ሁሉ አመሰግነዋለሁ፡፡ ለፈጣሪዬም
እዘምራለሁ› አለ፡፡ ሕዝቡም ሁሉ ‹በክብር ከፍ ከፍ ያለ
እግዚአብሔርን
በፍጹም ምስጋና እናመሰግነዋለን የሮማውያንን ኃይል ቀጥቅጦ
አጥፍቷልና፣ ሠረገሎቻቸውንም ሰባብሯልና፣ ሠራዊቱንም ሁሉ
በምድር
ላይበትኗቸዋልና…› እያሉ አመሰገኑ፡፡ በፈጣሪው በኢየሱስ
ክርስቶስ ኃይል
በጦርነቱ መካከል የረዳቸውን ቅዱስ ጊዮርጊስንም በፍጹም
ማድነቅ
እያደነቁ አመሰገኑት፡፡ የሮማም የጦር ሠራዊት
በኢትዮጵያውያን ፊት
ተዋረዱ፡፡ ዳግመኛም በኢትዮጵያ ላይ እጃቸውን ከፍ ከፍ
አላደረጉም፡፡
በምኒልክም ዘመነ መንግሥት ኢትዮጵያ ከጦርነት ለ40 ዓመት
ያህል
አረፈች፡፡ የኢትዮጵያ ንጉሠ ነገሥት ምኒልክም ከአድዋ ጦርነት
ከተመለሰ
በኋላ አዲስ አበባ በምትባለው ከተማው መካከል በቅዱስ
ጊዮርጊስ
ስም የተዋበች ቤተ ክርስቲያን አሠራ፡፡ ስሟንም ‹ገነተ ጽጌ››
ብሎ
ሰየማት፡፡ ሰማዕት ቅዱስ ጊዮርጊስ በጦርነቱ ሁሉ ይረዳው
ነበርና፡፡
ረድኤት በረከቱ ይደርብን በጸሎቱ ይማረን፡፡››
‹‹እግዚአብሔር ከተማን ካልጠበቀ ጠባቂ በከንቱ ይተጋልና››
ዛሬም
የኢትዮጵያ ገበዝ የአድዋው አርበኛ ሊቀ ሰማዕታት ቅዱስ
ጊዮርጊስ
የዓሥራት አገሩን ቅድስት ኢትዮጵያን ይጠብቅል፡፡ መዝ 127፡
1፡፡ የሰማዕቱ የቅዱስ ጊዮርጊስ ተራዳኢነት ከሁላችን ጋር
ይሁን፡፡
23
ምንጭ፡- ገድለ ቅዱስ ጊዮርጊስ
23
የእግዚአብሔር ቸርነት፣ የድንግል ማርያም አማላጅነት፣
የቅዱሳን መላእክት ተራዳኢነት፣ የጻድቃን፣ የሰማዕታት፣
የቅዱሳን ሐዋርያት፣ የቅዱሳን አበው መነኮሳት፣ የቅዱሳት
አንስት፣ የደናግላንና የቅዱሳን ሁሉ ምልጃና ቃል-ኪዳናቸው
ባለንበት ከሁላችን ጋር ይሁን!!!
†† † ♥ † ††
ለአባ ሕርያቆስ ፤ለቅዱስ ኤፍሬም ፤ለቅዱስ ያሬድ ፤
ለአባ ጊዮርጊስ ዘጋስጫ የተገለጸች እመቤታችን እኛንም
በበረከት እና በረድኤት ትጎብኘን ፤ ከልጅዋ ከወዳጅዋ
ከመድኃኔዓለም ዘንድ ታማልደን ፤ አሜን!!!
†† † ♥ † ††
ከዋክብት የሚያመሰግኑት በስማቸውም የሚጠራቸው: የፀጋው
ብዛት
የማይታወቅ ጌታችን አምላካችንና መድኃኒታችን ኢየሱስ
ክርስቶስ ሆይ
ለሐዋሪያት እንዲሁም ለቀደሙ አባቶቻችን ምሥጢሩን
እንደገለጽክላቸው
ለእኛም ግለጽልን። አሜን አሜን አሜን!!!
†† † ♥ † ††
ወ ስ ብ ሐ ት ለ እ ግ ዚ አ ብ ሔ ር
ወ ለ ወ ላ ዲ ቱ ድ ን ግ ል
ወ ለ መ ስ ቀ ሉ ክ ቡ ር

No comments:

Post a Comment