ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ነኝ

ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ነኝ
ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ነኝ

Saturday, March 26, 2016

ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ነኝ: የማዕተብ ሥርዓት

ሃይማኖት የልብ ብቻ አይደለም!!
አንዳንድ ሰዎች የማዕተብ ሥርዓትን ለመቃወምና
ዘመናውያን መስለው ለመታየት ‹‹እምነት በልብ ነው››
ይላሉ፤ ተሳስተዋል!
ሃይማኖት የልብ ብቻ አይደለም፤ የጠቅላላው ሕዋሳት ሁሉ
ናት፡፡ እግዚአብሔርን ስንወደውና ስናመልከው በልባችን ብቻ
ሳይሆን በአፋችንም በአንገታችንም በጠቅላላው ሰብአዊ
ተፈጥሯችን ሁሉ መሆን ይገባዋል፤ ምክንያቱም
እግዚአብሔር የጠቅላላው ሰውነታችን አምላክና ፈጣሪ
ስለሆነ ነው፡፡ ‹‹ስለዚህ በሰው ፊት የሚመሰክርልኝ ሁሉ እኔ
ደግሞ በሰማያት ባለው በአባቴ ፊት እመሰክርለታለሁ፤ በሰው
ፊትም የሚክደኝን ሁሉ እኔ ደግሞ በሰማያት ባለው በአባቴ
ፊት እክደዋለሁ፡፡›› (ማቴ.10÷32÷33)
በዚህ ቃለ ወንጌል መሠረት በኢ-አማንያን ዘንድ ክርስቲያን
መሆናችንን የምንገልፀው በልባችን ብቻ ሳይሆን በቃላችንና
በሥራችንም ጭምር ነው፡፡ በአንገታችንስ እንዳንመሰክርለት
ማን ያግደናል? በአንገታችን ባለው ማዕተብም
ለእግዚአብሔር እንመሰክራለን፡፡
የስሙን ምልክት በአንገታችን እናኖራለን፤ አናፍርበትም!!
የክርስቶስን ሞትና ትንሣኤ በጥምቀታችን እንደምንመሰክር
የጥምቀታችንንም ዓርማ በማተባችን እናረጋግጣለን፡፡
(ሮሜ 16÷13፤ ኢዩኤ. 2÷32፤ ሮሜ 6÷1-5፤
ማቴ.5÷11-12፤ 1ኛጴጥ.3÷21-22፤ 4÷12-16)

No comments:

Post a Comment