ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ነኝ

ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ነኝ
ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ነኝ

Tuesday, September 6, 2016

=>+*"+<+>††† ጾመ ዮዲት - ጾመ ጳጉሜም †††<+>+"*

<< ጾመ ዮዲት - ጾመ ጳጉሜም >>
በቤተክርስቲያናችን የፈቃድ ጾም ተብለው የሚታወቁት ጾመ
ጽጌ እና ጾመ ዮዲት ናቸው። የዮዲት ጾም የሚባለውም እርሷ
ስለ ጾመችው ነው፡፡ ለፋርስ ንጉሥ ለናቡከደነፆር የጦር አበጋዝ
የነበረው ሆሎፎርኒስ ፈቃድ ተሰጥቶት እስራኤልን ለመውረር
ሲመጣ በሠራዊቱ (ዮዲ2፣2-7) የእሥራኤል ልጆችም
ሆሎፎርኒስ የአሕዛብን አገር እንዳጠፋና ንብረታቸውን
እንደዘረፈ ሰምተው ስለ ቤተ መቅደሱ መፍረስና ሰለ ንዋያተ
ቅድሳት መርከሰ ማቅ ለብሰው አመድ ነስንሰው ከቤተ
መቅደሱ በር ወድቀው አለቀሱ።(ዮዲ4፡2-15)
ሆሎፎርኒስ ግን የሚጠጡትን ምንጫቸውን በመያዙ ፣
የእሥራኤል ልጆች በውኃ ጥም ከመቸገርና ከመሞት ይልቅ
እጃቸውን ለጠላት ለመስጠት ወሰኑ፡፡ ነገር ግን ዖዝያን
የአባቶቻቸው አምላክ መልስ እስኪሰጣቸውና ቸርነቱን
እስኪመልስላቸው መከራውን በትዕግሥት እንዲቀበሉ
ስለመከራቸው ጸኑ፡፡ዮዲ7 ፣10-32)
፨ ፨ ፨ ፨ ፨ ፨ ፨ ፨ ፨
በዚያም ባሏ ምናሴ የሞቶባት፣ ከወንድ ርቃ ንጽሕናዋን
ጠብቃ በጾም፣ በቀኖና፣ በትኅርምት፣ በኀዘን፣ በጸሎት ተወስና
የምትኖር የሜራሪ ልጅ ዮዲት ማቅ ለብሳ በራስዋ ላይ ትቢያ
ነስንሳ፣ ሱባዔ ገባች! አምላክም ሕዝቡን የሚያድንበትን
ዕውቀትና ጥበብ ግብር በገባች በሦስተኛ ቀን ገለጸላት፡፡
(ዮዲ8፡2) ከዚያም “ወዴት ትሔጃለሽ አትበሉኝ አምላክ
እሥራኤል ይከተልሽ ብሉኝ” ብላ የኀዘን ልብሷን ጣለች፡፡
ሰውነቷን ታጠበችና ሽቱ ተቀባች፣ ባሏ በሕይወት ሳለ
የምትለብሰውን የክት ልብሷን ለበሰች፣ የጠላት ሰዎች ሁሉ
እስኪወዷት ድረስ ፈጽማ አጊጣ ሄደች፡፡(ዮዲ.10፡2-3 )
እነርሱም ለእኔ ትገባለች ለእኔ ትገባለች እያሉ ተሻሙባት፡፡
የንጉሥ ጃንደረባ ጋይ የሚባል ይህችስ ለጌታዬ ትገባለች አለ፣
ለምን እንደመጣች ጠይቀዋት ለመልካም ነገር እንደመጣች
ሲረዱ ከጦር አበጋዙ አደረሷት፡፡(ዮዲ10፡12 -22)
፨ ፨ ፨ ፨ ፨ ፨ ፨ ፨ ፨
በአንዲትም ዕለት ሆሎፎርኒስ የአሽከሮች የምሣ ግብዣ
አድርጎ ሲያበላ ሲያጠጣ ያችን እብራዊት ጥሩ ብሎ አስጠርቶ
ከፊቱ አስቀምጦ ሲበላ አብዝቶ ሲጠጣ ውሎ ሰከረ፡፡(ዮዲ12፡
1-20 ) ከዚያም አሽከሮችን ከሁሉ አስወጥቶ ድንኳኑን
ቆልፎ እንደተኛ ከባድ እንቅልፍ ያዘው ዮዲትም ከፀለየች
በኋላ ከራስጌው ያለውን ሰይፍ አንስታ የራስ ጠጉሩን ይዛ
አንገቱን ቆርጣ በድኑን ከመሬት ጥላ ቸብቸቦውን በአቁማዳ
ቋጥራ ለብላቴናዋ አሸክማ ግንዱን በታች ገልብጣ ዙፋኑን
በላይ አድርጋ ወደ ሃገሯ ተመለሰች፡፡ (ዮዲ13፡1-10) ሕዝበ
እሥራኤል በዚህ ድርጊቷ እጅግ ተደነቁ፣ ጠላታቸውን
በእጃቸው የጣለላቸውን አግዚአብሔር አምላካቸውንም
አመሰገኑ፡፡ በኋላም የሆሎፎርኒስን ራስ በተራራው ላይ
ሰቅለው መዋጋት ጀመሩ፡፡ እስከዮርዳኖስም እየተከተሉ
አጥፍተዋቸዋል፡፡ ቅድስት ቤ.ክንም እግዚአብሔር የዮዲት
ጾም ተቀብሎ ከጠላት እጅ እንዳዳናቸው፣ ለእኛም ከሰይጻም
ወጥመድ እናመልስ ዘንድ ይህንን ጾም እንጾመው
ታበረታታለች ( የፈቃድ ጾም ነውና)። ለእኛም ለሃገራችን
ፍቅር ሰላምና አንድነትን፣ የመከፋፈልን አዚም
የምንቆርጥበት ጾም ያድርግልን!

No comments:

Post a Comment