ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ነኝ

ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ነኝ
ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ነኝ

Wednesday, May 11, 2016

+*"የክርስቲያን ሁሉ ዓርማ ማዕተብ"*+

ማዕተብ በቤተክርስቲያን ምን ማለት ነው????
ማዕተብ የክርስቲያን ሁሉ ዓርማ
“ማህተብህን በአንገትህ እሰረው ስትሔድ ይመራሃል ስትተኛ
ይጠብቅሃል ” ምሳ 6÷21
ማተብ (አተበ፤ አመለከተ ፤ባረከ)
ከሚለው የግእዝ ቃል የተገኘ ነው፡፡ይህም ማለት መታወቂያ ፤
ምልክት ማለት ነው፡፡ይህም ያሙትንና የተጠመቁትን
ካላመኑትና ካልተጠመቁት የሚለዮበት የክርስቲያን መታወቂያ
ነው፡፡
የዚህ ምልክት መሠረቱና ምሳሌውም ጌታችን መድኀኒታችን
ኢየሱስ ክርስቶስ ከተቀበለው ጸዋትወ መከራ አንዱ በገመድ
ታሥሮ መጎተቱ መሆኑንየሚያመለክት ነው፡፡
ዮሐ19፤12 ቅዱስ ዳዊትም በመዝ59፤4 ላይ ”ወወሀብኮሙ
ትእምርተ ለእለ ይፈርሁከከመያምሥጡእምገጸ ቅስት ፤
ከቀስት ፊት ያመልጡ ዘንድ ለሚፈሩ ምልከትን ሰጠሃቸው”
ይላል፡፡
አጋንንት የክፋትን ቀስት በዚህ ዓለም በመወርወር የሰውን ልብ
ስለሚወጉ ከዚህ ለመዳን ማዕተብን ማድረግ ታላቅ መንፈሳዊ
እውቀት ነው፡፡ ኢትዮጵያዊው ሊቅ አባ ጊዮርጊስ ዘጋስጫ
ሲያስረዱ ሥላሴ ማዕተበ ብርሃን ኃይል ሃይማኖቶሙ
ለክርስቲያን፤ሥላሴ ለክርስቲያን ሁሉ የሃይማኖታቸው ጉልበት
መታወቂያ የብርሃን ማዕተብ (ምልክት) ናቸው ብለዋል፡፡
ማዕተብ ያላሠረ ኦርቶዶክሳዊ በውግዘት ከቤተክርስቲያኒቱ እንደ
መናፍቅ ተቆጥሮ ባይለይም ማዕተብ አለማሠሩ ግን የአባቶቹ
ትውፊት እንዳልተቀበለ ያስቆጥረዋል፡፡
በምሳሌያዊ አነጋገርም ሃይማኖት አልባውን ማለትም
ክርስቲያን ያልሆነውን ማዕተብ የለሽ ያልተጠመቀ
አረሚይሉታል ክርስቲያን በማተቡ መነኩሴ በቆቡ እንዲታወቅ
ማዕተብ አልባ መሆን። ደግሞ ክርስቲያን
ይሁን ያልተጠመቀ መሆኑ ለማወቅ ያስቸግራል፡፡
በመለዮዋቸው ሌሎች እንዲታወቁ ክርስቲያን በማዕተቡ
ክርስትናውን ሲያሳውቅኖሯል፡፡ በተለመደው አነጋገር እገሌ
ማዕተብ አለው ባለማዕተብ ነው ሲባል እገሌ ታማኝ ክርስቲያን
ነው።
እውነተኛ :ሐቀኛ ነው የሚል ትርጉምን ይሰጣል
“ባለማዕተቢቱ” ሲባል ከአሚን ባሏ የረጋች ከባሏ
ሌላ የማታውቅ እውነተኛ ታማኝ ክርስቲያን የማል ፍች
አለው፡፡በዚህ ምክንያት በክርስቲያኑ ኅብረተሰብ የማዕተብ
ትርጉም ከፍተኛ ቁም ነገርን አዝሎ ይገኛል፡፡ አንዲት ሀገር ነፃ
መሆኗ የሚታወቀው ወይም ራሷን የቻለች የራሷ መንግሥት
ያላት ከባዕድ ቀንበር ቅኝ ግዛትነፃየወጣችመሆኗየሚታ
ወቀውበባንዲራዋ ምልክትነት እንደሆነ እንደዚሁም አንድ
ክርስቲያን በክርስቶስ አምኖ በጥምቀት ከዲያብሎስ ቁራኝነት
ነፃ መውጣቱ ነፃነት ያለው አማኝ መሆኑ የሚታወቀው
በማዕተቡ ምልክት ነው፡፡
ለደብዳቤ ለጽሑፍ ዓርማ ማኅተም ፊርማ እንደሚያስፈልገው
ያም ለመተማመኛ እንደሚያገለግል ጥቅሙ ታውቆ
ይሠራበታል፡፡
የክርስቲያን ማዕተብም በዚሁ አንፃር ብዙ ኃይማኖታዊ
ጠቀሜታ ይኖረዋል፡፡
መጀመሪያ በልቡ የሚያምነው ሃይማኖት ክርስትናን ሳያፍርበት
በአንገቱ ባለው ማተብ መግለጹ በክርስትናው አለማፈሩን
ክርስትናህን ካድ ማተብህን በጥስ የሚል ዓላዊ ቢመጣና ያንን
ምልክት ዓይቶ
ቢሰዋው የሰማዕትነትን ክብር ያገኝበታል፡፡ ያም ባይሆን
በማተቡ ምልክትነት በመናፍቃንና በኢአማንያን የሚቀበለው
ዘለፋ ስለ ክርስቶስ መስቀል እንደተሸከመ ያስቆጥረዋል፡፡
ሁለተኛው ከክርስቲያን ወገኖች ጋር
ያለጥርጥርማለትምየክርስቲ ያንመሆኑታውቆለት በቀላሉ
ክርስቲያናዊ ተሳትፎውን ማከናወን ይችላል፡፡ ማተብ ከሌለው
ግን ክርስቲያን ይሁን ያልተጠመቀ ስለማይታወቅ በሃይማኖት
ዜጎች ዘንድ በቀላሉ ተቀባይነት ማግኘት አይችልምሦስተኛ
ከማይታወቅበት ሀገር በአደጋም ይሁን በበሽታ እንደወጣ ሞት
ቢደርስበት በማዕተቡ መታወቂያነት የክርስቲያን ሥርዓት
ተፈጽሞለት አስክሬኑ ተፈርቶ በቤተክርስቲን ሊቀበር ይችላል፡፡
ማተብ ከሌለው ምስከር በአካባቢው ለክርስቲያንነቱ
ማረጋገጫ የሰው ያውም በሰበካው ቤተክርስቲያን የሚታመን
ክርስቲያን ከሌለ እንደአልተጠመቀ ተቆጥሮ እንደ አሕዛብ
ሥጋው ዱር ከበረሃ ወድቆ ይቀራል፡፡
ዐራተኛ ማተብና መስቀል ያለው ክርስቲያን በውሃ ዋና ወይም
በበረሃ ጎዳና በውሃ የሚኖሩ ወይም በበረሃ ያሉ አጋንንት
በቀላሉ ሊለክፉት አይችሉም፡፡ ይህምበየጠበሉ ሥፍራ
በተአምራት ተረጋግጧል፡፡ አጋንንት የለከፋቸው ሰዎች ማተብና
መስቀል አይወዱም፡፡ የሠፈረባቸው ርኩስ መንፈስ ማተብ
እንዲበጥሱ መስቀል እንዲጥሉ ያደርጋቸዋል፡፡
ማተብ በሰይጣን ዘንድ ከተጠላ በአጋንንት ላለመለከፍ የማተቡ
መኖር ይጠቅማል ማለት ነው፡፡
አንዳንድ ሰዎች የማዕተብ ሥርዓትን ለመቃወምና ዘመናውያን
መስለው ለመታየት “ሃይማኖት በልብ ነው” ይላሉ
ተሳስተዋል፡፡ ሃይማኖት የልብ ብቻ አይደለም የጠቅላላው
ሕዋሳት ሁሉ ናት እግዚአብሔርን ስንወደውና ስናመልከው
በልባችን ብቻ ሳይሆን በአፋችንም በአንገታችንም በጠቅላላው
ሰብአዊ ተፈጥሮአችን ሁሉ መሆን ይገባዋል፡፡
ምክንያቱም እግዚአብሔር የጠቅላላው ሰውነታችን አምላክና
ፈጣሪ ስለሆነ ነው፡፡ “ስለዚህ በሰው ፊት ለሚመሰክርልኝvሁሉ
እኔ ደግሞ በሰማያት ባለው በአባቴ ፊት እመሰክርለታለሁ በሰው
ፊትም የሚክደኝን ሁሉ እኔ ደግሞ በሰማያት ባለው
በአባቴ ፊት እክደዋለሁ፡፡ “ማቴ ፲፤፴፪-፴፫በዚህ ቃል
መሠረት በኢአማንያን ዘንድ ክርስቲያን መሆናችንን
የምንገልፀው በልባችን ብቻ ሳይሆን በቃላችንና በሥራችንም
ጭምር ነው፡፡
በአንገታችንስ እንዳንመሰክርለት ማን ያግደናል? በአንገታችን
ባለው ማዕተብም ለእግዚአብሔር
እንመሰክራለን የስሙን ምልክት በአንገታችን እናኖራለን
አናፍርበትም ፡፡ የክርስቶስን ሞትና ትንሣኤ በጥምቀታችን
እንደምንመሰክር የጥምቀታችንንም አርማ በማተባችን
እናረጋግጣለን፡፡ (ሮሜ ፲፤፮-፲፫፡፡ ኢዮኤል ፪፤፴፪፡፡ ሮሜ
፮÷፩-፭ ፣ ማቴ ፭÷፲፩-፲፪፡፡ ፩ጴጥ ፫÷፳፩-፳፪ ፩ጴጥ ፬÷፲፪-
፲፮)ተመልከት፡፡
የማዕተብ ጥቅም
1. የክርስትናን ማዕተብ በአንገት ማሰር በልብ ያለውን እምነት
ሳያፍሩ በኃጢአተኛው ትውልድ መካከል ስለ ክርስቶስ
መመስከር እንዲሁም ለሰይፍ ለመከራ መዘጋጀትን ማመልከት
ነው፡፡
2. ክርስቲያን ከሆኑ ምእመናን ጋር ሃይማኖታዊ የሆነውን
ተሳትፎ በቀላሉ ለማከናወንና በክርስቲያን ወገኖች ዘንድ
ተቀባይነት ለማግኘ
3. በጉዞ ላይ ያልታሰበ አደጋ ቢያጋጥምና ሞት ቢደርስ አደጋው
ደርሶበት ያረፈው ክርስቲያን ቤተሰቦቹ ባይገኙ በቅርበት
በማዕተቡ ክርስትናው ተረጋግጦ ጸሎተ ፍትሐት ተደርጎለት
በእምነቱ ተከብሮ አስከሬኑ በክርስቲያኖች መካነ መቃበር
ያርፋል፡፡
ወስበሐት ለእግዚአብሔር!

No comments:

Post a Comment