ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ነኝ

ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ነኝ
ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ነኝ

Saturday, May 21, 2016

=>+*"+<+>◆ ቅዱስ ሩፋኤል + አቡነ ዘርዓ ብሩክ ◆<+>+"*+

◆ ቅዱስ ሩፋኤል + አቡነ ዘርዓ ብሩክ ◆
ፈታሄ ማህጸን ቅዱስ ሩፋኤል
ለዘጠና ዘጠኙ ነገደ መላእክት ሰባት አለቆች አሏቸዉ፡፡እነዚህ
የተመረጡ ሊቃነ መላእክት ለተልእኮ ፤ለምስጋና ፤ለማማለድ
በቧለማልነት ዘወትር በእግዚአብሔር ፊት የሚቆሙ
ናቸዉ፡፡‹‹‹ርኢኩ ሰብዐተ መላእክትተ እለ ይቀዉሙ ቅድመ
እግዚአብሐየር ሰባት ሊቃነ መላኢክት በእግዚአብሐየር ፊት
ቆመሁ አየሁ ››››እንዲል ራእ 8፡2፡፡ከእነዚህ ሊቃነ መላኢክት
አንዱ ቅዱስ ሩፋኤል ሲሆን በማእረግ ሦስተኛ ነዉ፡፡በሰዉ
ቁስል የተሸመ ፤በፈዉስ ላይ የተሸመ፤ ከከበሩ መላእክት አንዱ
ቅዱስ ሩፋኤል ነዉ፡፡ሄኖክ 6፡3 ፡፡ቅዱስ ሩፋኤል ራሱም
‹‹‹የቅዱሳንን ጸሎት ከሚያሳርጉ ወደ ከበረ ወደ ገነት ወደ
እግዚአብሐሔር ጌትነት ከሚያ...ስገቡ ሰባት አለቆች አንዱ
ቅዱስ ሩፋኤል ነኝ ብሎል፡፡ጦቢት 12፡15 እግዚአብሔርም
በሃያ ሦስቱ ነገደ መላእክትም ላይ ሾሞታል፡፡
ቅዱስ ሩፋኤል ሰማያዉያን መዛግብት በእጁ የሚጠበቁ
በመሆናቸዉ‹‹ዐቃቤ ኖኀቱ ለአምላክ ›››ይባላል፡፡እግዚአብሔ
ር እንዳዘዘዉ የሚከፍታቸዉ የሚዘጋጋቸዉ እርሱ ቅዱስ
ሩፋኤል ነዉ፡፡በዚያች በድህነትና በደስታ ቀን ለሕዝበ ክርስቲያን
ከዕፀ ህይወት ይሰጣቸዉ ዘንድ እግዚአብሔር ያዘዘዉ ቅዱስ
ሩፋኤልን ነዉ፡፡ይህ የከበረ መላእክት ‹‹‹ፈታሄ ማህጸን››››
ይባላል፡፡እናቶች ሲወልዱ ምጥ እንዳይበዛባቸዉ የሚራዳ
መልአክ ነዉ፡፡በመሆኑም አያሌ ክርስቲያኖች ማርገዛቸዉን
ካወቁ ጀምሮ ድርሳኑን በማንበብ መልኩን በመድገም ጠበሉን
በመጠጣት ሰዉነታቸዉን በመቀባት ይለምኑታል፡፡እንደ
እምነታቸዉ ጽናት ይደረገላቸዋል፡፡
◆◆◆+++ አቡነ ዘርዓ ብሩክ +++
የጻድቁ አባታችን የዘርዓ ብሩክ አባት እና እናት የተባረኩ
ከቅዱሳን ወገን የሚሆኑ ነበሩ የአባታቸው ስምም ቅዱስ ደመ
ክርስቶስ ሲባል እናታቸው ደግሞ ቅድስት ማርያም ሞገሳ
ትባላለች ጻድቁ አባታችን ገና በናታቸው ማህጸን እያሉ ነበር
ብዙ ተአምራት የሚያደርጉት እግዚአብሄር መርጡአቸዋልና
በሁአላም ከክርስቶስ ልደት በሁአላ በስምንተኛው መቶ ክ/
ዘመን መጨረሻ ላይ በነሃሴ 27 ጻድቁ አባታችን ተወለዱ
በ40ኛ ቀናቸውም ተጠምቀው በካህናት አፍ "ጸጋ ክርስቶስ"
ተባሉ ከዛም ቤተሰቦቻቸው በጥሩ እድገት አሳደጉአቸው 7
አመትም በሞላቸው ግዜ በልጅነቴ የዚን አለም ክፋቱን
እንዳላይ ብለው ቢጸልዩ አይናቸው ታውሩአል:ቤተሰቦቻቸውም
የዚን አለም ትምህርት ሊያስተምሩአቸው አስተማሪ ጋር
ቢወስዱአቸው ታመው ተመልሰዋል:የእግዚአብሄር ፈቃድ
አይደለምና ነገር ግን የሚያስፈልጋቸውን እውቀት ፈጣሪ
አምላክ ራሱ ገልጾላቸዋል:: ክህነትን እስከ ጵጵስና እራሱ
መድሃኒአለም ክርስቶስ ሰቶአቸዋል:12 አመትም በሞላቸው
ግዜ አይናቸው በርቶላቸው ታላላቅ ተጋድሎን ማድረግ ጀመሩ :
የሃጥያት ማሰርያን ያስሩና ይፈቱ ዘንድ ጵጵስናን በሾማቸው ግዜ
እግዚአብሄር ያወጣላቸው ሁለተኛ ስም "ዘርዓ ብሩክ" ይባል
ነበር 3ኛውም ስማቸው ደግሞ "ጸጋ እየሱስ"ይባላል:: ጻድቁ
አባታችን በዚ አለም በህይወተ ስጋ ሳሉ አቡቀለምሲስ
እንደሚባል እንደ ዮሃንስ ወልደነጎድጉአድ እግዚአብሄር እሱ
ወዳ...ለበት ወደ ሰማይ አውጥቶ በገነት መካከል ያኖራቸው
ነበር:: እግዚአብሄር አምላክ ለወዳጁ ለብጹዕ አባታችን ዘርዓ
ብሩክ በጎ ነገር እንዳደረገለትና ያለ ድምጽ የሰማይ ደጆችን
አልፎ የእሳት ባህርን ተሻግሮ ፈራሽ በስባሽ ሲሆን እንደ ህያዋን
መላእክት በፍጥነት ከጽንፍ እስከ ጽንፍ ከአድማስ እስከ አድማስ
ይደርስ ዘንድ 12 ክንፍን ሰጣቸው:መላእክትም ለሌሎች
ቅዱሳን ያልተሰጠ ይህንን ስልጣን አይተው ለምድራዊ ሰው ይህ
ነገር እንዴት ይቻላል እያሉ አደነቁ: ከዛም በሁአላ ጻድቁ
አባታችን ከፈጣሪ ዘንድ የመላእክትን አስኬማ,የሾህ አክሊል
አምሳያ የሆነውን መንፈሳዊ ቆብን,ሰማያዊ ቅናትን እና የደረት
ልብስን(ስጋ ማርያም) ተቀብሎ በጾም እና በጸሎት በልመና
እና በስግደት እግዚአብሄርን ሲያገለግል ኖረ ከዛም በላይ
ወንጌልን እጅግ ብዙ በማስተማር ደከመ ከኢትዮጵያም አልፎ
ግብጽ ድረስ ገባ የእስክንድርያውን ሊቀ ፓፓስ አባ ዮሃነስን
አገኘውና እርስ በርስ ሰላምታን ተለዋውጠው እጅ ተነሳሱ
ከዛም ተመልሶ ወደ ሃገሩ መጣ ከዛም ኢትዮጵያ ውስጥ
እየተመላለሰ ወንጌልን አስተማረ እጅግ ስጋን በሚያስጨንቅ
ትጋትም የኢትዮጵያን ህዝብ ማርልኝ እያለ እያለቀሰ ይጸልይ
ነበር: አንድ ቀን አባታችን በንጉስ ጭፍሮች ተይዘው ሲሄዱ
ዳዊታቸውን ለግዮን ወንዝ አደራ ሰተዋት ከ5 አመት በሁአላ
ሲመለሱ ግዮን ሆይ ዳዊቴን ግሺ መልሺሊን ቢሉአት አንድም
የውሃ ጠብታ ሳይኖርባት ዳዊታቸውን ብትመልስላቸው ለደቀ
መዝሙራቸው ዘሩፋኤል አሳዩትና ግዮንንም "ግሽ አባይ"
ብለውታል እስካሁንም በዚሁ ስም የሚጠራው ከዚ በመነሳት
ነው:: ከዚህም ሌላ ጻድቁ አባታችን በዚሁ ወንዝ አካባቢ ለ 30
አመት ሲጸልዩ ፈጣሪ አምላክ ጸሎታቸውን ሰምቶ እጅግ ልዩ
የሆነ ቃል ኪዳን ሰቶአቸዋል:በስተመጨረሻም የሚያርፉበት
እለት በደረሰ ሰአት መልአከ ሞት መቶ እስኪደነግጥ እና ወደ
ሁአላው እስኪያፈገፍግ ድረስ ነው ነው እግዚአብሄር ጸጋውንና
ክብሩን ያበዛላቸው: በስተመጨረሻም ጥር በገባ በ13 ቀን
በ482 አመታቸው ስጋቸው ከነፍሳቸው ተለይታ ገነትን
ወርሰዋል::ምንጭ ገድለ አቡነ ዘርዓ ብሩክ የጻድቁ አባታችን
ገድለ ዜና እንኩአን በዚች በምታህል ጽሁፍ አይደለም
የገድላቸውም መጽሃፍም አልበቃውም እንደው እግዚአብሄር
አምላክ ከበረከታቸው እንዲያሳትፈን አስቤ ይችን ጥቂት
የገድላቸውን ዜና ከገድላቸው መጽሃፍ ላይ
አስቀመጥኩ:ለእግዚአብሄር ምስጋና ይሁን እኛንም በኚህ
ጻድቅ ጸሎት ይማረን በረከታቸውንም ያድለን አሜን
የቅዱስ ሩፋኤል ልመናዉ በረከቱ ይደርብን ፡፡አሜን ፡

No comments:

Post a Comment