ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ነኝ

ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ነኝ
ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ነኝ

Monday, April 4, 2016

ሰኞ የሚፀለይ አምላክን የወለደች የድንግል ማርያም ምስጋና
ጌታ በልቡ ያዘነና የተከዘ አዳምን ነፃ ያወጣውና ወደ ቀድሞው
ቦታው ይመልሰው ዘንድ ወደደ ቅድስት ሆይ ለምኝልን።
ከድንግል ያለወንድ ዘር በሥጋ ተወለደና አዳነን። ከይሲ
(ዲያብሎስ) ያሳታት ሔዋንን እግዚአብሔር ምጥሽንና ጻርሽን
አበዛዋለው ቢሎ ፈረደባት ሰውን ወደደና ነፃ አደረጋት። ቅድስት
ሆይ ለምኝልን።
ሰው የሆነና በኛ ያደረ ቃል ኢየሱስ ክርስቶስ ነው። ክብሩንም
ለአባቱ አንደ እንደመሆኑ ክብር አየን። ይቅር ይለን ዘንድ
ወደደ። ቅድስት ሆይ ለምኝልን።
ነቢዩ ኢሳያስ በመንፈስ ቅዱስ የአማሩኤልን ምሥጢር አየ
ስለዚህም ሕፃን ተወለደልን ወልድም ተሰጠን ብሎ አሰምቶ
ተናገረ። ቅድስት ሆይ ለምኝልን።
ሰው ሆይ ፈጽመህ ደስ ይበልህ እግዚአብሔር ዓለሙን
ወዶታልና አንድ ልጁንም የሚያምንበት ሁሉ እስከ ዘለዓለም
ፈጽሞ ይድን ዘንድ አሳልፎ ሰጥቷልና ልዑል ክንዱን ሰደደልን።
ቅድስት ሆይ ለምኝልን።
የተበረው የሚኖረው የመጣው ዳግመኛ የሚመጣውም ቃል
ኢየሱስ ክርስቶስ ያለመለወጥ ፍጹም ሰው ሆነ አንዱ ወልድ
በሥራው ሁሉ አልተለየም የእግዚአብሔር ቃል መልኮት አንድ
ነው እንጂ ። ቅድስት ሆይ ለምኝልን።
የነቢያት ሀገራቸው ቤተልሔም ሆይ ደስ ይበልሽ ሁለተኛው
አዳም ክርስቶስ በአንቺ ዘንድ ተወልዷልና ከምድር (ከሲኦል)
ወደ ገነት ይመልሰው ዘንድ አዳም ሆይ መሬት ነበርክና ወደ
መሬት ትመለሳለህ ብሎ የፈረደበትንም የሞት ፍርድ ያጠፋለት
ዘንድ፤ ቡዙ ኃጢያት ባለችበት የእዚአብሔር ጸጋ ትበዛለች።
ቅድስት ሆይ ለምኝልን።
የሰው ሁሉ ሰውነት ደስ ይላታል በሰማይ ለእግዚአብሔር
ምስጋና ይሁን በምድርም ሰላም ለሰውም እርሱ በሚፈቅደው
እያሉ አሰምተው ንጉሥ ክስርቶስን ከመላእክት ጋር
ያመስግኑታል። የቀድሞውን እርግማን አጥፍቷልና የጠላትን
ምክሩን አፈረሰበት ለአዳምና ለሔዋን የዕዳ ደብዳቤያቸውን
ቀደደላቸው በዳዊት ሀገር የተወለደ መድኃኒታችን ኢየሱስ
ክርስቶስ አዳምና ሔዋንን ነፃ አደረጋቸው ።ቅድስት ሆይ
ለምኝልን።
በዚህ ዓለም ለሚኖሩ ሰዎች ሁሉ የምታበራ እውነትኛ ብርሃን
ስለሰው ፍቅር ወደ ዓለም የመጣው ፍጥረት ሁሉ በመጣትህ
ደስ አለው አዳምን ከስህተት አድረኸዋልና ሔዋንንም ከሞት
ጻዕረኝነት ነፃ አድርገኻታልና የምንወለድበትን መንፈስ (ረቂቁን
ልደት) ሰጠኸን ከመላእክት ጋርም አመስገንህ ቅድስት ሆይ
ለምኝልን።
ወስብሐት ለእግዚአብሔር ለወላዲቱ ድንግል ወለመስቀሉ

No comments:

Post a Comment