ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ነኝ

ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ነኝ
ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ነኝ

Tuesday, September 13, 2016

ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ነኝ: =>+*"+<+>††† መስከረም 1-ሊቀ መላእክት ቅዱስ ራጉኤል †††<+>+"*

አንድ አምላክ በሚሆን በአብ በወልድ በመንፈስ ቅዱስ ስም
አሜን
መስከረም 1-ሊቀ መላእክት ቅዱስ ራጉኤል የተሾመበት
ዕለት ነው፡፡
+ ዳግመኛም በዚኽች ዕለት ሐዋርያው ቅዱስ በርተሎሜዎስ
ዕረፍቱ ነው፡፡
+ ታላቁ አባት ጻድቁ አባ ሚልኪ ዕረፍቱ ነው፡፡
+ ጻዲቁ ኢዮብም ከበሽታው የዳነው በዚህች ዕለት ነው፡፡
ጻዲቁ ኢዮብ በፈሳሽ ውኃ ታጥቦ ከደዌው ሁሉ ስለተፈወሰ
ለሰዎች ልማዳቸው ሆኖ ዓመቱ ዞሮ ሲመጣ ፈሳሹ ውኃም
በመላ ጊዜ በአዲስ ውኃ ይጠመቃሉ፣ በእርሱም ይባረካሉ፡፡
ሐዋርያው በርተሎሜዎስ፡- ወንጌልን ይሰብክ ዘንድ ዕጣ
የደረሰው አልዋሕ በሚባል አገር ነው፡፡ ቅዱስ ጴጥሮስ
ሊያደርሰው አብረው ወደ አልዋሕ ሄዱ፡፡ ወደ ከተማው
ለመግባት ምክንያት ፈለጉና ቅዱስ ጴጥሮስ ቅዱስ
በርተሎሜዎስን ‹‹አትክልተኛ ባለሙያ ነው›› ብሎ የወይኑን
ቦታ እንዲጠብቅለት ለአንድ ባለጸጋ መኰንን ባሪያ አድርጎ
ሸጠው፡፡ ባለጸጋውም በርተሎሜዎስን በ30 እስቴታር
ገዝቶት ሄደ፡፡ ቅዱስ ጴጥሮስ ገንዘቡን ደብቆ ለቅዱስ
በርተሎሜዎስ በድብቅ ሰጥቶት እንዲመጸውተው ነግሮት
ወደ ኢየሩሳሌም ተመለሰ፡፡ አልዋሕ ከገባ በኋላ ቅዱስ
በርተሎሜዎስ የወይን ቦታው አለቃ ሆኖ 40 ቀን
ተቀመጠ፡፡ ወንጌሉን ባለመስበኩ በሀዘን እያለቀሰ ጌታችንን
በጸሎት ጠየቀው፡፡ በገንዘቡ ገዝቶት ባሪያው ያደረገው
ባለጸጋውም የወይኑን ቦታ ያይ ዘንድ እንደመጣ መርዘኛ እባብ
ነድፎት ሞተ፡፡ ሕዝቡም ተሰብስቦ ሲያለቅስ በርተሎሜዎስ
ግን ወደ ጌታችን ከጸለየ በኋላ ሄዶ ባለጸጋውን ሰው ከሞት
አስነሣው፡፡ በዚህም ሕዝቡ ሁሉ አምነው ተጠምቀዋል፡፡
በርተሎሜዎስም ወደ ሌሎች አገሮች ሄዶ አስተማረ፡፡
ጌታችን ወደ በርበሮች ዘንድ ሄዶ ወንጌልን እንዲሰብክ
አዘዘው፡፡ ረዳት እንዲሆነውም እንድርያስን ከደቀ መዝሙሩ
ጋር ላከለት፡፡ የሀገሪቱ ሰዎች ግን እጅግ ክፉዎች ነበሩ፡፡
በሐዋርያቱም ፊት በአስማት አስደናቂ ተአምራት እያሳዩ
ትምህርታቸውን የማይቀበሏቸው ሁኑ፡፡ ይህን ጊዜ ጌታችን
ሰውን ከሚበሉ አገር አንዱን ገጸ ከልብ ይታዘዝላቸው ዘንድ
በሚያዙትም ነገር ሁሉ ከትእዛዛቸው እንዳይወጣ አዘዘው፡፡
ሐዋርያትም ወደ በርበሮች አገር ዳግመኛ በገቡ ሰዓት
ይበሏቸው ዘንድ ኃይለኛ አራዊትን አውጥተው ለቀቁባቸው፡፡
ያ ገጸ ከልብም በአራዊቱ ላይ ተነሥቶ እየነጠቀ በላቸው፡፡
ይህንንም የተመለከቱት በርበሮች እጅግ ፈርተው በድንጋጤ
ብቻ የሞቱ አሉ፡፡ በሐዋርያቱም እግር ሥር ወደቁ፡፡
ሐዋርያቱም አስተምረው ካሳመኗቸው በኋላ
አጥምቀዋቸዋል፡፡ ከዚህ በኋላ ቅዱስ በርተሎሜዎስ
እግዚአብሔርን ወደማያውቁ አገሮች ሄዶ ብዙ ተአምራትን
እያደረገ አስተምሮ አጠመቃቸው፡፡ የከሃዲው ንጉሡ
የአግሪጳን ሚስትም ትምህርቱን ሰምታ በጌታችን አመነች፡፡
ንጉሡ አግሪጳም በዚህ እጅግ ተቆጥቶ ቅዱስ
በርተሎሜዎስን ብዙ ካሠቃየው በኋላ አሸዋ በተሞላ ትልቅ
ከረጢት ውስጥ ከቶ ከነሕይወቱ ባሕር ውስጥ እንዲጥሉት
አደረገ፡፡ ምእመናንም ሥጋውን አውጥተው በክብር
ቀብረውታል፡፡ ረድኤት በረከቱ ይደርብን፣ በጸሎቱ ይማረን፡፡
+ + + + + + + + + + + + + + +
አባ ሚልኪ ዘቁልዝም፡- በላይኛው ግብጽ የሚኖሩ ባለጸጋ
ወላጆቻቸው በስዕለት ወለዷቸው፣ ብሉይን ከሐዲስ አጠናቀው
ከተማሩ በኋላ የአባታቸውን ወርቅ ለድኆች ሰጥተው ገዳም
ገብተው መነኩሰው በታላቅ ተጋድሎ ኖሩ፣ የአገረ ገዥውልን
ልጅ ዘንዶ ውጦት ሳለ አባ ሚልኪ ዘንዶውን ጠርቶት ልጁን
ይተፋው ዘንድ አዘዘውና ልጁ ጤነኛ እንደሆነ ከዘንዶው ውስጥ
ወጣ፣ በውስጡ ያደረ ከይሲም በኖ ጠፋ፣ ጻድቁ ቤ/ክ ሲሠሩ
የመሠረቱ ድንጋይ ራሱ በተአምራት እየተፈነቀለ ይተከል
ነበር፣ ለ300 መነኮሳትም አባት ሆነው በተአምራታቸው
የፋርስንና የሮም ሰዎችን አሳመኗቸው፣ ዋሻ ዘግተው ሊኖሩ
በማሉ ጊዜ ሰይጣን መሀላቸውን ሊያፈርስ አስቦ በሮሙ ንጉሥ
ልጅ አድሮ አሳመማትና በአባ ሚልኪ ካልሆነ በቀር
አልወጣም አለ፣ ንጉሡም ልኮባቸው በደመና ተጭነው ሄደው
ልጅቷን ፈውሰው አድሮባት የነበረውን ሰይጣን ገዝተው
አሠሩትና ከንጉሡ ቤት 14 ሰው የማይሸከመውን ድንጋይ
በአንገቱ ላይ አሳስረው አስሸክመውት ሰው ሁሉ እያየው ወደ
ገዳማቸው አስመጡትና ድንጋዩን የበዓታቸው መዝጊያ
አደረጉት፤ ጻድቁ በብርቱ ሲጋደሉ ኖረው የሚያርፉበት ቀን
ከተነገራቸው በኋላ እነ እንጦንስ፣ መቃርስ፣ ሲኖዳ፣ ብሶይ፣
ጳኩሚስ ተገልጠውላቸው ወንድማችን ና ወደ እኛ ብለዋቸው
በሰላም ዐርፈዋል፡፡ ረድኤት በረከታቸው ይደርብን፣
በጸሎታቸው ይማረን፡፡
+ + + + + + + + + + + + + + +
ራጉኤል ሊቀ መላእክት:- ራጉኤል ማለት የብርሃናት አለቃ
ማለት ነው። የብርሃናት አለቃ ሲባል ፀሐይን፣ ጨረቃን እና
ከዋክብትን በማመላለስና ለሰው ልጆች፣ ለአዝርዕት፣
ለእንስሳት፣ ለአራዊት ሁሉ ብርሃንን የሚመግብ ነው ማለት
ነው። አንድም ራጉኤል ማለት የሚበቀል ማለት ነው።
የሚበቀል ነው ማለት በቀል የሚገባው ለጠላት ነው የሰው
ልጅ ጠላት ደግሞ ዲያብሎስ ነው፤ ስለሆነም ቅዱስ ራጉኤል
እግዚአብሔርን አምነው ሕገ እግዚአብሔርን ጠብቀው
በፍርሐተ እግዚአብሔር አምልኮቱን ለሚፈጽሙ ሁሉ ጠላት
ዲያብሎስን የሚያርቅላቸው ወደ እነርሱም ፈጥኖ በመድረስ
የሚታደጋቸው ነው ማለት ነው። ሔኖክ 6:4፡፡ አንድም
ራጉኤል ማለት የኃያላን ኃያል እግዚአብሔር ማለት ነው።
የኃያላን ኃያል ያለው የእግዚአብሔርን ኃያልነት ከምድር
ፍጥረታት ዘንድ ኃያል ከሚባሉት ሁሉ ሊገለጽ የማይችል
ኃያልነቱን ለመግለጽ ኃያልነቱም ከ እስከ የሌለው መሆኑን
ለመግለጽ የተቀመጠ ነው። ስለዚህ እግዚአብሔር ኃያል
የኃያላን ኃያል መሆኑን የሚገልጽ ትርጉም አለው።
አንድም ራጉኤል ማለት ጽኑ እግዚአብሔር ማለት ነው።
የእግዚአብሔር አምላክን ጽኑነት ለማጉላት ሲል ጽኑ አለው።
እግዚአብሔር የማይወላውል የማይዋዥቅ የማይከዳ ነው
ለማለትም ሲል ይህ ስያሜ ተሰጠው። የእግዚአብሔርን ጽናት
የሚያሳይ ትርጉም ያለው ስያሜ ነው። የሊቀ መላእክት
የቅዱስ ራጉኤል አገልግሎት እና ስልጣን፡- እመቤታችን
ቅድስት ድንግል ማርያም ከዚህ ዓለም በ64 ዓመቷ ካረፈች
በኋላ ሥጋዋ ወደ ዕፀ ሕይወት ሲነጠቅ (ሲያርፍ) አብሮ
ለሔደው እና ስጋዋን በእጣን ሲያጥን ለነበረው ለፍቁረ እግዚ
ለቅዱስ ዮሐንስ ኅብስትን የመገበ መልአክ ነው።
በብርሃናት ሁሉ ላይ የሰለጠነ መልአክ ነው። ከአዳም ሰባተኛ
ትውልድ የሆነ በእግዚአብሔር ፊት ግሩም ያማረ ሥራው
የሰመረ እስከዛሬ የሞት ወጥመድ ያልያዘው የሞት ጥላ
ያላረፈበት ነብዩ ሔኖክ "ከቅዱሳን መላእክት አንዱ የሆነ ጸላዒ
ዲያብሎስን የሚበቀለው ራጉኤል በብርሃናት ላይ የሰለጠነ
ነው" ሲል ስለ እርሱ ተናግሯል፡፡
እግዚአብሔር ዓለምን ይቆጣጠር ዘንድ የሾመው ታላቅና
ቅዱስ መልአክ ነው። (ድርሳነ ራጉኤል ዘ ጥቅምት ገጽ 23)
አዲስ ሰማይና አዲስ ምድር ለመተካት ዓለምን የመለወጥ
ሥልጣን የተሰጠው ቅዱስ መልአክ ነው። ከእግዚአብሔር
የጌትነቱ አዳራሽ ይገባና ይወጣ ዘንድ ስልጣን ያለው
ከኪሩቤልና ከሱራፌል ጋር ከፈጣሪ የጌትነት ዙፋን ፊት
የሚቆም ነው። ሎጥን ሚስቱንና ልጆቹን ከእሳተ ጎመራ
ያዳነ የበለአምን እርግማን ወደ በረከት የለወጠ እርሱ ነው።
በቅዱስ ራጉኤል ስነ ሥዕል ላይ የምናየው ይህ ባለ አራት
እራስ ንስር ከአርባእቱ ኪሩቤል አንዱ ገጸ ንስር ነው።
የሥላሴን የጌትነት ዙፋን የሚሸከሙ አርባዕቱ እንስሳት
ናቸው። የሚሸከሙት ሲባል ጫማ የሰውን ልጅ
እንደሚሸከመው እንጂ ችለውትስ አይደለም። እነርሱም
የሰው ገጽ፣ የእንስሳ ገጽ፣ የንስር ገጽ እና የአንበሳ ገጽ ያላቸው
ናቸው። ይህንንም ነብዩ ሕዝቅኤል "ለእያንዳንዱ እንስሳትም
የተለያዩ አራት ገጾች ነበሩት። ይህውም በስተቀኝ በኩል
የእንስሳ መልክ፣ በስተ ግራ የላም ገጽ፣ በበስተ ኋላም የንስር
ገጽ የሚመስሉ ነበሩ" ብሏል ሕዝ 1፡6-13፡፡ ከዚህ
የምንገነዘበው ነገር ቢኖር አራት ገጽ ካላቸው ኪሩቤል
መካከል አንዱ ንስር መሆኑን ነው። ቅዱስ ራጉኤል ደግሞ
የእነዚህ ኪሩቤል አለቃቸው (የጌትነቱ ዙፋን ጠባቂ) በመሆኑ
በዚህ ምክንያት ማለትም እነርሱ ዙፋኑን ተሸካሚ እርሱ
ደግሞ አጠገባቸው መቆሙ መንበሩን ጠባቂ በመሆኑ በዚህ
አይነት የአገልግሎት ድርሻ አብረው ሊሳሉ ችለዋል። ቅዱስ
ያሬድም በድጓው "አርባእቱ እንስሳ አልቄንጥሩ እንደሚባለው
ንስር ፊት ለፊት አይታዩም አንዱም በመራቸው ይሔዳሉ
እነርሱም እያንዳንዳቸው አራት ገጽ ሲኖራቸው ሳያርፉና
ሳይደክሙ የሚያመሰግኑ ናቸው" በማለት ጽፏል። አንድም
መላእክት ነገደ ሱራፌል እና ነገደ ኪሩቤል በመባል
ይከፈላሉ። በነገደ ሱራፌል እነ ቅዱስ ሚካኤል፣ ቅዱስ
ሩፋኤል ወዘተ ሲሆኑ በነገደ ኪሩቤል ደግሞ ቅዱስ ገብርኤል
ቅዱስ ራጉኤል ወዘተ ያጠቃልላል። ስለዚህ ቅዱስ ራጉኤል
ነገዱ ከነገደ ኪሩቤል ነው በዚህም ላይ የነገደ ኪሩቤል
አልቄንጡራ (አራት እራስ ንስር) አለቃቸው ቅዱስ ራጉኤል
ነው። በዚህም ምክንያት አብረው ሊሳሉ ችሏል። አንድም
መላእክትን ሁሉ እንደ እየስራቸው መለያ ስነ ሥዕላቸውን
መሳል ልማድ ነውና። ለምሳሌ ቅዱስ ሚካኤል ከቅድስት
አፎምያ ጋር፣ ቅዱስ ገብርኤል ከሠለስቱ ደቂቅ ጋር፣ ቅዱስ
ዑራኤል ከእዝራ ሱቱኤል ጋር እንደሚሳሉት ሁሉ ማለት
ነው። በዚህም መሰረት ቅዱስ ራጉኤልም ዐቃቤ መንበር
ነውና መንበሩን በሚሸከሙት ኪሩቤል ከሚመሰሉት ንስሮች
ጋር አብረው ሊሳሉ ችለዋል፡፡
ሊቀ መላእክት ቅዱስ ራጉኤል ከአምላክ የተሰጠው ቃል
ኪዳን እግዚአብሔር አምላክ በስሙ ለታመኑት ቅዱሳን፣
ጻድቃን፣ ሰማእታት፣ ሐዋርያት፣ ዘወትር ያለማቋረጥ ስሙን
ለሚጠሩት ቅዱሳን መላእክት ሁሉ ቃል ኪዳን ሰጥቷቸዋል።
የሰጣቸውም ቃል ኪዳን ዘላለማዊ እና ሊሻር የማይችል
ነው። ለመላእክት አለቃ ለቅዱስ ራጉኤልም ይህን ቃል ኪዳን
ሰጥቶታል "የራጉኤል አምላክ ይቅር በለኝ በማለት አንዲት
ቃልስ እንኳን ቢናገር እንደ ወዳጄ እንደ አብርሃም፣ እንደ
ባለሟሌም እንደ ይስሐቅ፣ እንደ አከበርኩትም እንደ ያዕቆብ
ክብርን ባለሟልነትን እሰጠዋለሁ በራሱ ላይም አክሊል
አቀዳጀዋለሁ እረጅም ዘመናት ሰፊ ወራትም እሰጠዋለሁ"
ሲል ቃሉን ሰጥቶታል፡፡ ሊቀ መላእክት ቅዱስ ራጉኤል
መስከረም 1 ቀን ከሊቃነ መላእክት በ4ተኛ ደረጃ
የተሾመበት ዕለት ነው። ግንቦት 1 ቀን ለታላቁ አባት ለሄኖክ
ምሥጢራትን የገለጸበት በዓሉ ነው፡፡ ጥበቃው አይለየን፣
በምልጃው ይማረን፡፡
የቅዱሳን አባቶቻችን አምላክ ሀገራችንን ይጠብቅልን፡፡

27 comments:

  1. smadav pro khokharpc Thanks for this post, I really found this very helpful. And blog about best time to post on cuber law is very useful.

    ReplyDelete
  2. norton antivirus farooqpc Thanks for sharing such great information, I highly appreciate your hard-working skills which are quite beneficial for me.

    ReplyDelete
  3. Thanks for sharing such great information, I highly appreciate your hard-working skills which are quite beneficial for me. eset-endpoint-security-crack

    ReplyDelete
  4. This article is so innovative and well constructed I got lot of information from this post. Keep writing related to the topics on your site. Winrar Crack

    ReplyDelete
  5. Hi, your article was best to read about. I am sharing some useful content related to law, justice, and jurisdiction. If you are searching about prosecutor or you want to consult some law firm then you can visit this weissman law firm. Check out k law too.

    This site contains information about the rights of different pople such as if people working abroad need suggestions about law, such as ofw. You can also get information here if you need any help regarding accident lawyers such as tractor trailer accident, or 18 wheeler accidents, then feel free to visit this best law site.
    Mesothelioma Law Firm help families nationwide and often travel to help to get compensation for asbestos patients.
    Asbestos lawyer specializes in lawsuits involving victims of asbestos exposure and help families suffering from a mesothelioma diagnosis.

    Are you there to search for mesothelioma lawyer or you want to learn about the types of law then you are at right place.

    ReplyDelete
  6. With your presentation, you make it appear so simple, but I find this subject to be one that I believe I will never understand.
    It appears to be far too sophisticated and vast for me.
    I'm looking forward to reading your future post,
    I'll make an effort to grasp it!
    pinnacle studio crack
    vso convertxtohd crack
    avast clear crack
    orifice design calculator crack

    ReplyDelete
  7. We’re fortunate to have an innovator and creative such as you in our midst. Congratulations for a job well done.
    avanquest inpixio photo clip professional crack
    coreldraw x8 free download full version crack
    windows 10 crack

    ReplyDelete
  8. Great, submit, very informative.
    I ponder why the opposite experts of this sector don’t realize this.
    You must proceed your writing.
    I’m confident, you have
    a great readers’ base already!
    tally erp crack
    vlc media player crack

    ReplyDelete
  9. Hello there, I just discovered your blog on Google, and I like it.
    is quite useful. I'll keep an eye out for brussels sprouts.
    If you keep doing this in the future, I will be grateful. A large number of people will profit.
    based on your writing Cheers!
    youtube movie maker crack
    driver genius pro crack
    fifa license key
    4ukey itunes backup crack

    ReplyDelete
  10. On the Internet, I was overjoyed to discover this establishment.
    This was a fantastic read, and I owe it to you at least once.
    It piqued my interest a little, and you were kind enough to keep it.
    Become a fan of a new item on your site.
    icecream screen recorder crack
    office timeline pro edition crack
    ableton live crack
    xsplit broadcaster crack

    ReplyDelete
  11. Such great and nice information about software. This site gonna help me a lot in finding and using much software. Kindly make this like of content and update us. Thanks for sharing us Toon Boom Storyboard Crack . Kindly click on here and visit our website and read more

    ReplyDelete
  12. Thanks for sharing this with us. I just loved your way of presentation. I enjoyed reading this .Thanks for sharing and keep writing.
    The Medium Crack
    unhackme pro crack
    Valheim Crack

    ReplyDelete
  13. I am very thankful for the effort put on by you, to help us, Thank you so much for the post it is very helpful, keep posting such type of Article.
    Wondershare MobileTrans Pro Crack
    Command and Conquer Generals Zero Hour Free Download
    DeskSoft EarthTime

    ReplyDelete
  14. Here at Karanpccrack, you will get all your favourite software. Our site has a collection of useful software. That will help for your, Visite here and get all your favourite and useful software free.
    beecut Crack

    ReplyDelete