ስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ ፡፡
አሜን ፡፡ ✞✞✞
❖መጋቢት ፯ (7) ቀን የሚከበሩ ዓመታዊ የቅዱሳን በዓላት
✞ ሰማዕትነት በቅዱስ ቴዎዶጦስ ሕይወት ✞
+*" ቅዱስ ቴዎዶጦስ "*+
=>በ3ኛው መቶ ክ/ዘመን ነው:: ጊዜው ለክርስቲያኖች
ሁሉ ፍጹም የመከራ ከመሆኑ የተነሳ "ዘመነ-ሰማዕታት"
ሲባል በወቅቱ ከ47 ሚሊዎን በላይ ክርስቲያኖች
ተጨፍጭፈዋል::
+የዘመኑ ክርስቲያኖች ለመሞት የሚያደርጉትን
እሽቅድምድም እያዩ አሕዛብ "ወፈፌዎች" እያሉ
ይጠሯቸው ነበር:: (ዓለም እንዲህ ናትና!) እብዶቹ
ጤነኞችን "እብድ" ማለታቸውኮ ዛሬም አለ::
(ለነገሩ "ግደልና ጽደቅ" ከሚል መመሪያ በላይ ጤና
ማጣት አይኖርም)
=>ታዲያ በወቅቱ አንድ #ቴዎዶጦስ የሚሉት ወጣት
በምድረ ግብጽ ይኖር ነበር:: ወጣቱ እጅግ ብርቱ
ክርስቲያን ነበርና እንደ ዘመኑ ልማድ ተከሦ በነፍሰ
ገዳዮች ፊት ቀረ:: ክሱ አንድ ብቻ ነው:: "ክርስቶስን
አምልከሃል" የሚል::
+ከሥጋ ሞት ለማምለጥ ደግሞ መንገዱ ያው አንድ ብቻ
ነው:: ፈጣሪውን ክርስቶስን ክዶ ለአሕዛብ አማልክት
(አጋንንት) መገዛት:: #ቅዱስ_ቴዎዶጦስ በገዳዮቹ ፊት
ቆሞ ተናገረ:-
" #እኔ_ክርስቲያን_ክርስቶሳ ዊ_የክርስቶስ_ነኝ:: ምንም
ብታደርጉኝ ከክርስቶስ ፍቅር ልትለዩኝ አትችሉም"(ሮሜ.
8:35) አላቸው::
+እነሱ ግን ነገሩ እውነት አልመሰላቸውምና ሊያሰቃዩት
ጀመሩ::
*ገረፉት
*አቃጠሉት
*ደበደቡት
*ሌላም ሌላም ማሰቃያዎችን በእርሱ ላይ ተጠቀሙ::
የሚገርመው ግን እሱ ሁሉን ሲታገሥ ገዳዮቹ ግን
ደከሙ::
+በመጨረሻም ወደ ገዢው ዘንድ አቅርበው "ብዙ
አሰቃይተነዋል:: ግን ሊሳካልን አልቻለም" በሚል ሰይፍ
(ሞት) ተፈረደበት:: በአደባባይ ሊሰይፉት ሲወስዱት ግን
ትንሽ አዘኑለት መሰል ጨርቅ አምጥተው "ፊትህን ሸፍን"
አሉት:: (ያኔ ትንሽም ቢሆን ሰብአዊነት ሳይኖር አይቀርም)
+ቅዱስ ቴዎዶጦስ ግን ገዳዮቹን በመገረም
እየተመለከታቸው ተናገረ:- "እኛ ክርስቲያኖች ሞትን
አንፈራም:: ሞት ለእኛ ወደ ክርስቶስ መሸገጋገሪያ
ድልድያችን ነውና የምንፈራው ሳይሆን የምንናፍቀው
ነው::" "ኢትፍርሕዎሙ
(አትፍሯቸው)"
(ማቴ. 10:28)
+ይህን ብሎ ወደ ሰማይ ቀና ብሎ ጌታውን አመሰገነ::
ፊቱ ላይ ደስታ እየተነበበ ጨካኞቹ አንገቱን ሰየፉት::
በብርሃን አክሊልም ቅዱሳን መላእክት ከለሉት::
*መሠረታዊው ነገር ቅዱስ ቴዎዶጦስ ለምን አልፈራም?
ነው::
+አጭር መልስ ካስፈለገን ቅዱሱ ያልፈራው ከልቡ
ክርስቶሳዊ በመሆኑ ነው:: ትኩረት እንድንሰጠው
የሚያስፈልገው ግን የሰማዕታት ምስጢራቸው:-
1.በጽኑ የክርስትና መሠረት ላይ መመሥረታቸው
2.ዕለት ዕለት የክርስቶስን ፍቅር መለማመዳቸው
3.ከወሬ (ንግግር) ይልቅ ተግባርን መምረጣቸው
4.በንስሃ ሕይወት መመላለሳቸው
5.ሥጋ ወደሙን የሕይወታቸው ዋና አካል ማድረጋቸው
6.ከእነሱ የቀደሙ ቅዱሳንን ዜና ሕይወት ከልብ
ማንበባቸው
7.በቃለ እግዚአብሔር መታነጻቸው . . . መጠቀስ
የሚችሉ መገለጫዎቻቸው ናቸው::
<+>" ዛሬስ "<+>
=>ዓለማችን ከጠበቅነው በላይ ነፍሰ በላነቷ እየጨመረ
ነው:: ዛሬ የክርስትና ጠላቶች ከጉንዳን በዝተዋል::
*የራሳችን ማንነት
*ክርስትናችን በአፋችን ላይ ብቻ መሆኑ
*እረኞችና በጐች መለያየታቸው . . . ሁሉ እኛ ልናርማቸው
የሚገቡ ናቸው::
*አሸባሪዎች
*አሕዛብ
*የመዝናኛው ዓለም
*ሰይጣን አምላኪ ዝነኞች (Celebrities)
*ሚዲያው
*ማሕበራዊ ድረ ገጾችና መሰል ነገሮች ደግሞ
ልንጠነቀቅባቸው የሚገቡና እኛን ውስጥ ለውስጥ
በልተው የፈጁን የሰይጣን መሣሪያዎች ናቸው::
+ስለዚህም ከዛሬ ጀምረን ባለ መታወክ ክርስትናችንን
ከአፋችን ወደ ልባችን: ከብዕራችን ወደ አንጀታችን
እንድናወርደው ቅድስት ቤተ ክርስቲያን አደራ ትላለች::
+ዛሬ ነገሮችን ረስተን ሌሎች አላስፈላጊ ነገሮችን
ከጀመርን እጅግ አሳፋሪ መሆኑ አይቀርም:: በጐውን
ጐዳና ተከትለን በሃይማኖትና በፍቅረ ክርስቶስ ከጸናን ግን
ማንም ቢመጣም ፈጽሞ አንናወጥም::
+ይልቁኑ
"አምላካችን መጠጊያችንና ኃይላችን:
ባገኘን በታላቅ መከራም ረዳታችን ነው::
ስለዚህም ምድር ብትነዋወጥ: ተራሮችም ወደ ባሕር ልብ
ቢወሰዱ አንፈራም::" (መዝ. 46:1) እያልን ከቅዱስ
ዳዊት ጋር እንዘምራለን::
<< ለዚህ ደግሞ ደመ ሰማዕታት ይርዳን:: በረከታቸው
ይድረሰን:: የጌታ ፍቅርም አይለየን >>
+*" ጻድቁ ንጉሥ ቴዎድሮስ "*+
=>በሃገራችን ታሪክ በጣም ተወዳጅ ከነበሩ ነገሥታት
ጻድቁ ቴዎድሮስ ቅድሚያውን ይወስዳል:: በርግጥ
በርካቶቻችን የምናውቀው ስለ ሃገሩ ፍቅር ራሱን የሰዋውን
ዳግማዊ ዐፄ ቴዎድሮስን (1845-1860) ነው:: በበጎ
ሥራውና በቅድስና ሕይወቱ የተመሠከረለት ግን ዛሬ
የምናስበው ቀዳማዊው ነው::
+ቀዳማዊ ዐፄ ቴዎድሮስ የደጉ ዐፄ ዳዊት (ግማደ
መስቀሉን ያመጡት) እና የተባረከችው ሚስታቸው ፅዮን
ሞገሳ ልጅና የጻድቁ ዐፄ ዘርዐ ያዕቆብ ታላቅ ወንድም
ነው:: በኢትዮዽያ ለ3 ዓመታት (ከ1396-1399) ብቻ
ነግሦ እያለ እንደ ንጉሥ ሳይሆን-
*ከጠዋት እስከ ማታ ድሃ እንዳይበደል ፍርድ
እንዳይጉዋደል ይታትር የነበር::
*ጾምና ጸሎትን የሚያዘወትር::
*ወገቡን ታጥቆ ነዳያንን የሚያበላ::
*ለአብያተ ክርስቲያናትም የሚጨነቅ ደግ ሰው ነበር::
+ስለዚህም በሕዝቡ እጅግ ተወዳጅ ነበር:: በነገሠ በ3
ዓመቱ ዐርፎ በዝማሬና በለቅሦ ሥጋውን ተሸክመው
ሲሔዱ ወንዝ ተከፍሎላቸዋል:: ከመቃብሩም ላይ ጸበል
ፈልቁዋል::
=>ዘለዓለም ሥላሴ ደግ መሪና ሰላማዊ ዘመንን ያድሉን::
=>መጋቢት 7 ቀን የሚከበሩ ዓመታዊ የቅዱሳን በዓላት=
1.ጻድቁ ኢትዮዽያዊ ንጉሥ ዐፄ ቴዎድሮስ
2.ቅዱስ ቴዎዶጦስ ሰማዕት
3.ቅዱስ ፊልሞን ሰማዕት
4.ቅዱስ አብላንዮስ ሰማዕት
=>ወርሐዊ በዓላት
1.ሥሉስ ቅዱስ (አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ)
2.አባ ጊዮርጊስ ዘጋስጫ
3.አባ ሲኖዳ (የባሕታውያን አለቃ)
4.አባ ዳንኤል ዘገዳመ ሲሐት
5.አባ ባውላ ገዳማዊ
6.ቅዱስ አትናቴዎስ ሐዋርያዊ
7.ቅዱስ አግናጥዮስ (ለአንበሳ የተሰጠ)
=>+"+ ነፍስ ሁሉ በበላይ ላሉት ባለ ሥልጣኖች ይገዛ::
ከእግዚአብሔር ካልተገኘ በቀር ሥልጣን የለምና::
ያሉትም ባለ ሥልጣኖች በእግዚአብሔር የተሾሙ ናቸው::
ስለዚህ ባ ለሥልጣንን የሚቃወም የእግዚአብሔርን
ሥርዓት ይቃወማል:: . . . ለሁሉ እንደሚገባው አስረክቡ::
ግብር ለሚገባው ግብርን: ቀረጥ ለሚገባው ቀረጥን:
መፈራት ለሚገባው መፈራትን: ክብር ለሚገባው ክብርን
ስጡ:: +"+ (ሮሜ. 13:1-8)
<<< ወስብሐት ለእግዚአብሔር >>>
ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ነኝ
ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ነኝ
Friday, March 17, 2017
ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ነኝ:=>+*"+<+>††በቤተክርስቲያናችን ስርአት መሰረት 7 ጊዜ እንፀልያለን ። የእነሱም ትርጉም ††
~በቤተክርስቲያናችን ስርአት መሰረት 7 ጊዜ እንፀልያለን ።
የእነሱም ትርጉም
1= ጠዋት 12:00 ሰአት፡- አንድ ክርስቲያን እግዚአብሔርን
አምላክን በፀሎት የሚያመሰግንበት ምክንያት (ሚስጥር)
እግዚአብሔር አምላክ ሌሊቱንና ጨለማውን አሳልፎ ብርሀን
እንድናይ ስላበቃን በዚህ ሰአት እግዚአብሔር አምላካችንን
እንድናመሰግን ታዝዝዋል። አንድም በዚህ ሰአት ጌታችን
ለክስ ከጲላጦ ፊት ቆሞ የተወቀሰበት ሰአት ስለሆነ አንድም
በዚ ሰአት አባታችን አዳም ያልተፈቀደለትን እፅ በልቶ ከገነት
የተባረረበት ሰአት ስለሆነ ነው። አንድ ክርስቲያን ይህን ሁሉ
እያሰበ ወደ አምላኩ እንዲፀልይ ታዝዋል
2=ከጠዋቱ 3:00 ሰአት፡- አንድ ክርስቲያን እንዲፀልይ
የታዘዘበት ምክንያት (ሚስጥር)
በዚህ ሰአት እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ብስራተ
ገብርኤልን የሰማችበት ሰአት ስለሆነ ነው አንድም በዚህ
ሰአት እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ጌታችንን
የፀነሰችበት ሰአት ስለሆነ ነው አንድም ጌታችን መድሀኒታችን
ኢየሱስ ክርስቶስ ከ ጲላጦስ ፊት ቀርቦ የተገረፈበት ሰአት
ስለሆነ ዮሐ 19 ፥1 ሐዋ ስራ 2፥15 እያንዳንዱ ክርስቲያን
ይሔንን የመሳሰሉ ሁሉ እያሰበ እግዚአብሔር አምላኩን
እንዲያመሰግን ታዝዋል
3= 6:00 ሰአት፡-አንድ ክርስቱያን እኩለ ቀን (ከ ቀኑ
6ሰአት) ሲሆን እንዲፀልይ የታዘዘበት ምክንያት ወይም
(ሚስጥር )
ጌታችን በቀራኔዎ አደባባይ በመስቀል ተሰቅሎበታልና
አንድም ልብሱን ተገፎበታል አንድም ሳዶር አላዶር ዳናት
ሮዳስ በተባሉ ችንካሮች ተቸንክሮበታል አንድ ክርስቲያን ይህን
ሁሉ እያሰበ በዚህ ሰአት እንዲፀልይ ታዞበታል
4= ከቀኑ 9:00 ሰአት፡- አንድ ክርስቲያን የሚፀልይበት
ምክንያት (ሚስጥር)
አይሁዶች ጌታችን መድሀኒታችን ኢየ�ሱስ ክርስቶስን መራራ
ሐሞት አጠጥተውበታል አንድም ቅድስት ነፍሱን ከ ክቡር
ስጋው የለየበት ሰአት ነውና አንድም በመስቀል እንዳለ 7ቱን
አፅርሀ መስቀል የተናገረበት ማር 15፥34 ማቴ 27፥50
አንድ በዚህ ሰአት ይህንን እያሰበ እንዲፀልይ ታዝዋል
5= ከቀኑ 11፡00 ሰአት፡- አንድ ክር�ቲያን እንዲፀልይበት
የታዘዘበት ምክንያት ወይም (ሚስጥር)
ጌታችን መድሀኒታችን እየሱስ ክርስቶስ ወደ ከርሰ መቃብር
የወረደበት ሰአት ስለሆነ አንድም ቀኑን በሰላም አሳልፎ ወደ
ምሽት በሰላም ያደረሰን አምላክ ምስጋ ስለሚገባው ነው
ይህንን የመሳሰሉ ሁሉ ሕዝበ ክርስቲያን እንዲያስቡ ታዘዋል
6= ከምሽቱ 3:00 ሰአት፡- በዚህ ሰአት አንድ ክርስቲያን
እንዲያመሰግን የታዘዘበት ምክንያት (ሚስጥር)
በዚህ ሰአት እራሱ ጌታችን መድሀኒታችን እየሱስ ክርስቶስ
ስርአተ ፀሎት አሳይቶበታል አንድም በዚህ ሰአት ጌታችንን
አይሁድ በይሁዳ ጠቁዋሚነት ተረበርበው የያዙበት ሰአት
ስለሆነ ነው አንድም በዚህ ሰአት አንድ ክርስቲያን ከመተኛቱ
በፊት በሰላም ያዋለንንና ያስመሸንን አምላክ አመስግኖ
መተኛት አለበት ይህን ሁሉ እያሰበ እንዲፀልይ ታዝዋል
7= መንፈቀ ሌሊት ከሌሊቱ 6 :00 ሰአት:- በዚህ ሰአት አንድ
ክርስቲያን እግዚአብሔር አምላኩን እንዲያመሰግንበት
የታዘዘበት ምክንያት (ሚስጥር)
በዚህ ሰአት ጌታችን መድሀኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ
ተወልዶበታልና ነው አንድም ጌታችን መድሀኒታችን ኢየሱስ
ክርስቶስ ሙስና መቃብርን ድል አድርጎበታልና(ተነስቶበታ
ል) በመዝሙረ ዳዊት አመሰግንህ ዘንድ በመንፈቀ ሌሊት
እነሳለው ባለው መሰረት ጳውሎስ ሲላስ በእስር ቤት ሆነው
ወደ እግዚአብሔር የፀለዩበት ስለሆነ ነው አንድም የሰው ልጅ
የሚመጣበት ጊዜ ማታ ይሁን መንፈቀ ሌሊት ይሁን ዶሮ
ሲጮህም ይሁን ሲነጋም ቢሆን አይታወቅምና ባለው
አምላካዊ ቀል መሰረት በመንፈቀ ሌሊት አንድ ክርስቲያን
እንዲፀልይ ታዝዋል
የቅዱሳን ሁሉ ጸሎት እና ምልጃ አክሊልና ጉልላት በሆነው
በእናታችን በወላዲተ አምላክ ቅድስት ድንግል ማርያም
ጸሎት ሁላችንንም ይማረን፡፡
የእነሱም ትርጉም
1= ጠዋት 12:00 ሰአት፡- አንድ ክርስቲያን እግዚአብሔርን
አምላክን በፀሎት የሚያመሰግንበት ምክንያት (ሚስጥር)
እግዚአብሔር አምላክ ሌሊቱንና ጨለማውን አሳልፎ ብርሀን
እንድናይ ስላበቃን በዚህ ሰአት እግዚአብሔር አምላካችንን
እንድናመሰግን ታዝዝዋል። አንድም በዚህ ሰአት ጌታችን
ለክስ ከጲላጦ ፊት ቆሞ የተወቀሰበት ሰአት ስለሆነ አንድም
በዚ ሰአት አባታችን አዳም ያልተፈቀደለትን እፅ በልቶ ከገነት
የተባረረበት ሰአት ስለሆነ ነው። አንድ ክርስቲያን ይህን ሁሉ
እያሰበ ወደ አምላኩ እንዲፀልይ ታዝዋል
2=ከጠዋቱ 3:00 ሰአት፡- አንድ ክርስቲያን እንዲፀልይ
የታዘዘበት ምክንያት (ሚስጥር)
በዚህ ሰአት እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ብስራተ
ገብርኤልን የሰማችበት ሰአት ስለሆነ ነው አንድም በዚህ
ሰአት እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ጌታችንን
የፀነሰችበት ሰአት ስለሆነ ነው አንድም ጌታችን መድሀኒታችን
ኢየሱስ ክርስቶስ ከ ጲላጦስ ፊት ቀርቦ የተገረፈበት ሰአት
ስለሆነ ዮሐ 19 ፥1 ሐዋ ስራ 2፥15 እያንዳንዱ ክርስቲያን
ይሔንን የመሳሰሉ ሁሉ እያሰበ እግዚአብሔር አምላኩን
እንዲያመሰግን ታዝዋል
3= 6:00 ሰአት፡-አንድ ክርስቱያን እኩለ ቀን (ከ ቀኑ
6ሰአት) ሲሆን እንዲፀልይ የታዘዘበት ምክንያት ወይም
(ሚስጥር )
ጌታችን በቀራኔዎ አደባባይ በመስቀል ተሰቅሎበታልና
አንድም ልብሱን ተገፎበታል አንድም ሳዶር አላዶር ዳናት
ሮዳስ በተባሉ ችንካሮች ተቸንክሮበታል አንድ ክርስቲያን ይህን
ሁሉ እያሰበ በዚህ ሰአት እንዲፀልይ ታዞበታል
4= ከቀኑ 9:00 ሰአት፡- አንድ ክርስቲያን የሚፀልይበት
ምክንያት (ሚስጥር)
አይሁዶች ጌታችን መድሀኒታችን ኢየ�ሱስ ክርስቶስን መራራ
ሐሞት አጠጥተውበታል አንድም ቅድስት ነፍሱን ከ ክቡር
ስጋው የለየበት ሰአት ነውና አንድም በመስቀል እንዳለ 7ቱን
አፅርሀ መስቀል የተናገረበት ማር 15፥34 ማቴ 27፥50
አንድ በዚህ ሰአት ይህንን እያሰበ እንዲፀልይ ታዝዋል
5= ከቀኑ 11፡00 ሰአት፡- አንድ ክር�ቲያን እንዲፀልይበት
የታዘዘበት ምክንያት ወይም (ሚስጥር)
ጌታችን መድሀኒታችን እየሱስ ክርስቶስ ወደ ከርሰ መቃብር
የወረደበት ሰአት ስለሆነ አንድም ቀኑን በሰላም አሳልፎ ወደ
ምሽት በሰላም ያደረሰን አምላክ ምስጋ ስለሚገባው ነው
ይህንን የመሳሰሉ ሁሉ ሕዝበ ክርስቲያን እንዲያስቡ ታዘዋል
6= ከምሽቱ 3:00 ሰአት፡- በዚህ ሰአት አንድ ክርስቲያን
እንዲያመሰግን የታዘዘበት ምክንያት (ሚስጥር)
በዚህ ሰአት እራሱ ጌታችን መድሀኒታችን እየሱስ ክርስቶስ
ስርአተ ፀሎት አሳይቶበታል አንድም በዚህ ሰአት ጌታችንን
አይሁድ በይሁዳ ጠቁዋሚነት ተረበርበው የያዙበት ሰአት
ስለሆነ ነው አንድም በዚህ ሰአት አንድ ክርስቲያን ከመተኛቱ
በፊት በሰላም ያዋለንንና ያስመሸንን አምላክ አመስግኖ
መተኛት አለበት ይህን ሁሉ እያሰበ እንዲፀልይ ታዝዋል
7= መንፈቀ ሌሊት ከሌሊቱ 6 :00 ሰአት:- በዚህ ሰአት አንድ
ክርስቲያን እግዚአብሔር አምላኩን እንዲያመሰግንበት
የታዘዘበት ምክንያት (ሚስጥር)
በዚህ ሰአት ጌታችን መድሀኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ
ተወልዶበታልና ነው አንድም ጌታችን መድሀኒታችን ኢየሱስ
ክርስቶስ ሙስና መቃብርን ድል አድርጎበታልና(ተነስቶበታ
ል) በመዝሙረ ዳዊት አመሰግንህ ዘንድ በመንፈቀ ሌሊት
እነሳለው ባለው መሰረት ጳውሎስ ሲላስ በእስር ቤት ሆነው
ወደ እግዚአብሔር የፀለዩበት ስለሆነ ነው አንድም የሰው ልጅ
የሚመጣበት ጊዜ ማታ ይሁን መንፈቀ ሌሊት ይሁን ዶሮ
ሲጮህም ይሁን ሲነጋም ቢሆን አይታወቅምና ባለው
አምላካዊ ቀል መሰረት በመንፈቀ ሌሊት አንድ ክርስቲያን
እንዲፀልይ ታዝዋል
የቅዱሳን ሁሉ ጸሎት እና ምልጃ አክሊልና ጉልላት በሆነው
በእናታችን በወላዲተ አምላክ ቅድስት ድንግል ማርያም
ጸሎት ሁላችንንም ይማረን፡፡
ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ነኝ:=>+*"+<+>††ቅዱስ ዮሐንስ ወልደ ነጎድጓድ††
ዮሐንስ ማለት ፍሰሓ ወሐሴት ሠላም ርህራሄ ወሳህል
ማለት ነው። ወልደ ነጎድጓድ፣ አቡቀለምሲስ፣ ነባቤ መለኮት፣
ታዖሎጎስ ይለዋል፡፡ “ቃዳሚሁ ቃል ውእቱ” ብሎ ምስጢረ
ሥላሴን አምልቶ አስፍቶ ይናገራልና፡፡ ፍቁረ እግዚእ
ይለዋል፡፡ “ዝኩ ካልዕ ረድዕ ዘያፈቅሮ እግዚእ ኢየሱስ”
ይለዋልና፡፡ ዮሐንስ 21፡7 መውደድንስ ሁሉንም ይወዳቸው
የለምን ቢሉ የርሱ የተለየ ነውና፡፡ ከቶማስም የሱ መወደድ
ይበልጣል፡፡ ቶማስ በጦር የተወጋ ጎኑን ቢዳስሰው እጁ ከእሳት
እንደገባ ጅማት ተኮማትሯል፡፡ እርሱን ግን በከናፍሩ ቢስመው
በጭኑ ቢያስቀምጠው ምንም ምን አልሆነም ::
ንጹህ ወድንግል ይለዋል፡፡ ጌታን ከመውደዱ የተነሳ ጌታም
እናቱን እነዃት እናትህ ሲል ድንግል ማርያምን በሱ በኩል
ተሰታናለች፡፡ እኛም ዛሬ ልጆቿ ነንና ደስ ይበለን ይበላችሁ
የድንግል ማርያም የአስራት፣ የተስፋና የስስት ልጆች፡፡ ዮሐንስ
19፡26፡፡ ዮሐንስ ሀገሩ ገሊላ አውራጃ ሲሆን ከታላቅ
ወንድሙ ከያዕቆብና ከአባቱ ከዘብድዮስ ጋር ዓሣ እያጠመደ
ይኖር ነበር። እናቱ ከ36ቱ ቅዱሳት አንስት አንዷ ስትሆን
ማርያም ትባላለች።
ዮሐንስ ከ12ቱ ሐዋርያት አንዱ ሲሆን በሕይትም በኑሮም
ጌታ ስለሚመስል (ፍቁረ እግዚእ) ይባለል። ነገረ መለኮትን
በበለጠ ከሌሎች አምልቶ አስቶ በጥልቀት በማስተማሩ ነባቤ
መለኮት (ታዖሎጎስ)ተሰኝቷል። ስለጌታም ባለው ቅናት ባሳየው
የሀይል ሥራ በኦኔርጌስ (ወልደ ነጎድጓድም) ተብሏል። ፍጥሞ
በምትባል ደሴት በራዕይ መጻእያትን በመግለጡ ባለራዕይ
(በግሪክ አቡቀለምሲስ) ይባለል። በዕለተ ዓርብ በመስቀል ሥር
ተገኝቶ የጌታን መከራ መስቀል በማየቱ ፊቱ በሀዘን
ስለተቋጠረ ቁጽረ ገጽ (ፊቱ በሀዘነ የተቋጠረ) ስምም
ተሰቶታል። ከቅዱስ ጴጥሮስ ጋር የፋሲካን እራት ያዘጋጀ
አንካሳን የፈወሰ ታለቅ ሐዋርያ ነው። (ሊቃስ 22፡8) እስከ
መስቀል አምላኩን ተከትሎ እመቤታችንን በአደራ የተረከበ
ባለአደራ ሐዋርያ ሲሆን ከጰራቅሊጦስ በዓል በኋላ ከቅዱስ
ጴጥሮስ ጋራ በኢየሩሳሌም በአንጾኪያ በሎዶቅያ በእስያ
ከተሞች በተለይ በኤፌሶን በአሁኑ ቱርክ አስተምሯል።
(ዮሐ.19፡26) በወጣትነት ዕድሜው ተጠርቶ በዕለተ ዓርብ
የጌታን መከራ እያሰበ ያነባ የነበረ በፍቅር በታማኝነት
እስከመጨረሻ ድረስ የጸና ከጌታ ያልተለየ ወንጌላዊ ሲሆን
ወንጌልን ጨምሮ 3 መልዕክታትን የጻፈ እንዲሁም ሐዋርያው
ዩሐንስ በፍጥሞ ደሴት በዛሬቱ ቱርክ ለሰባት አመታት ታስሮ
በነበረበት ወቅት ወንጌሉንና ራዕዩን ጽፏል። አይገርምህም
ሐዋርያው ዩሐንስ በእስር እያለ ነው ራዕዩን የጻፈው!!!
ሐዋርያው ቅ/ጳውሎስ ደግሞ በቀዝቃዛ እስር ቤት እያለ ብዙ
መልእክታቱን ጻፈ!!! ሐዋርያቱ በእስር ቢሆኑ እንኳን
ስለቅድስት ቤተክርስቲያን አገልግሎት አብዝተው ያስቡ ነበር።
የሐዋርያቱ ብርታት ያበርታን።
ዩሐንስ ወንጌሉን በፍጥሞ ደሴት ሲጽፍ እንዲህ ብሎ ጀመረ፦
ዩሐንስ 1:1
+++ በመጀመሪያ ቃል ነበረ; ቃልም በእግዚአብሔር ዘንድ
ነበረ ቃልም እግዚአብሔር ነበረ።እኛም በቅዳሴ ላይ ሁሌ
የዩሐንስ ወንጌል ሲነበብ ቀዳሚሁ ቃል ሥጋ ኾነ ወሃደረ
ላዕሌነ ብለን እንቀበላለን። ግሩም ዜማ ከግሩም ሚስጢር
ጋር አባቶቻችን አወረሱን።
እስቲ ሚስጢሩን እንይ፦
በመጀመሪያ ቃል ነበረ፦ እንደምናውቀው ቃል ኢየሱስ
ክርስቶስ ነው። ኢየሱስ ክርስቶስ አልፋና ዖሜጋ መጀመሪያና
መጨረሻ ነውና ራዕ 22:12። ቃልም እግዚአብሔር ነበር፦
መጽሃፍ አንባቢው ያስተውል ይላል; ምን እንደሚል ልብ
እንበል “ቃልም እግዚአብሔር ነበር” ሐዋርያው በመጀመሪያ
ቃል ነበር ብሎን ነበር; ያ ቃል እግዚአሔር እንደሆነ
አስረዳን!!! በዚሁ ምዕራፍ ላይ ወረድ ብሎ /ዩሐንስ 1:14/
“ያ ቃል ሥጋ ሆነ ይለናል” እስቲ ጥያቄ እንጠያየቅ; ሐዋርያው
ያ ቃል ሥጋ ሆነ ብሏል ከማን? ከማን ሥጋን ነሳ?
ከእመቤታችን ከቅድስት ድንግል ማርያም ከሥጋዋ ሥጋ ከነፍሷ
ነፍስ ነስቶ በኤፍራታ በቤቴልሔም ተወለደ።
+++ የፍጥሞ ደሴት ታሪክ እነሆ፦ ሐዋርያው ዩሐንስ በፍጥሞ
ደሴት ወንጌሉን መጻፍ ሲጀምር የመለኮትን ነገር ጽፎ
የሚጨርስ መስሎት ብእሩን አነሳ። በመጀመሪያ ቃል ነበረ
አለና ሊጨርስ አሰበ፤ ያኔ መልአኩ ቅ/ሚካኤል ተገልጦ
በፍጥሞ ደሴት ያለችውን ባህር በእንቁላል ቅርፊት እየቀዳ
ወደ መሬት ሲያፈስ አየው; ሐዋርያው ዩሐንስም እንዴት ይህ
ታላቅ ባሕር በእንቁላል ቅርፊት ያልቃል ብሎ ጠየቀው;
መልአኩም እኔስ ብሞክር ፍጥረትን ነው አንተስ የፈጣሪን
ባሕርይ የሚያልቅ መስሎህ ትሞክር አይደለምን አለው። ያኔ
ሐዋርያው ዩሐንስ ይህን ተረድቶ ወዲያው ከእግዚአብሔር
የተላከ ስሙ ዩሐንስ የሚባል አንድ ሰው አውቃለሁ ብሎ
ስለመጥምቁ ዩሐንስ ታሪክ የቀጠለውም በዚሁ ምክንያት
ነበር። ዩሐንስ 1:19
ከሐዋርያው፣ ከዮሐንስ ወልደ ነጎድጓድ ረድኤትና በረከት
ይክፈለን ምልጃና ጸሎት ከሁላች ጋር ይሁን አሜን !!!
ወስብሐት ለእግዚአብሔር ወለወላዲቱ ድንግል ወለመስቀሉ
ክቡር ይቆየን አሜን።
ማለት ነው። ወልደ ነጎድጓድ፣ አቡቀለምሲስ፣ ነባቤ መለኮት፣
ታዖሎጎስ ይለዋል፡፡ “ቃዳሚሁ ቃል ውእቱ” ብሎ ምስጢረ
ሥላሴን አምልቶ አስፍቶ ይናገራልና፡፡ ፍቁረ እግዚእ
ይለዋል፡፡ “ዝኩ ካልዕ ረድዕ ዘያፈቅሮ እግዚእ ኢየሱስ”
ይለዋልና፡፡ ዮሐንስ 21፡7 መውደድንስ ሁሉንም ይወዳቸው
የለምን ቢሉ የርሱ የተለየ ነውና፡፡ ከቶማስም የሱ መወደድ
ይበልጣል፡፡ ቶማስ በጦር የተወጋ ጎኑን ቢዳስሰው እጁ ከእሳት
እንደገባ ጅማት ተኮማትሯል፡፡ እርሱን ግን በከናፍሩ ቢስመው
በጭኑ ቢያስቀምጠው ምንም ምን አልሆነም ::
ንጹህ ወድንግል ይለዋል፡፡ ጌታን ከመውደዱ የተነሳ ጌታም
እናቱን እነዃት እናትህ ሲል ድንግል ማርያምን በሱ በኩል
ተሰታናለች፡፡ እኛም ዛሬ ልጆቿ ነንና ደስ ይበለን ይበላችሁ
የድንግል ማርያም የአስራት፣ የተስፋና የስስት ልጆች፡፡ ዮሐንስ
19፡26፡፡ ዮሐንስ ሀገሩ ገሊላ አውራጃ ሲሆን ከታላቅ
ወንድሙ ከያዕቆብና ከአባቱ ከዘብድዮስ ጋር ዓሣ እያጠመደ
ይኖር ነበር። እናቱ ከ36ቱ ቅዱሳት አንስት አንዷ ስትሆን
ማርያም ትባላለች።
ዮሐንስ ከ12ቱ ሐዋርያት አንዱ ሲሆን በሕይትም በኑሮም
ጌታ ስለሚመስል (ፍቁረ እግዚእ) ይባለል። ነገረ መለኮትን
በበለጠ ከሌሎች አምልቶ አስቶ በጥልቀት በማስተማሩ ነባቤ
መለኮት (ታዖሎጎስ)ተሰኝቷል። ስለጌታም ባለው ቅናት ባሳየው
የሀይል ሥራ በኦኔርጌስ (ወልደ ነጎድጓድም) ተብሏል። ፍጥሞ
በምትባል ደሴት በራዕይ መጻእያትን በመግለጡ ባለራዕይ
(በግሪክ አቡቀለምሲስ) ይባለል። በዕለተ ዓርብ በመስቀል ሥር
ተገኝቶ የጌታን መከራ መስቀል በማየቱ ፊቱ በሀዘን
ስለተቋጠረ ቁጽረ ገጽ (ፊቱ በሀዘነ የተቋጠረ) ስምም
ተሰቶታል። ከቅዱስ ጴጥሮስ ጋር የፋሲካን እራት ያዘጋጀ
አንካሳን የፈወሰ ታለቅ ሐዋርያ ነው። (ሊቃስ 22፡8) እስከ
መስቀል አምላኩን ተከትሎ እመቤታችንን በአደራ የተረከበ
ባለአደራ ሐዋርያ ሲሆን ከጰራቅሊጦስ በዓል በኋላ ከቅዱስ
ጴጥሮስ ጋራ በኢየሩሳሌም በአንጾኪያ በሎዶቅያ በእስያ
ከተሞች በተለይ በኤፌሶን በአሁኑ ቱርክ አስተምሯል።
(ዮሐ.19፡26) በወጣትነት ዕድሜው ተጠርቶ በዕለተ ዓርብ
የጌታን መከራ እያሰበ ያነባ የነበረ በፍቅር በታማኝነት
እስከመጨረሻ ድረስ የጸና ከጌታ ያልተለየ ወንጌላዊ ሲሆን
ወንጌልን ጨምሮ 3 መልዕክታትን የጻፈ እንዲሁም ሐዋርያው
ዩሐንስ በፍጥሞ ደሴት በዛሬቱ ቱርክ ለሰባት አመታት ታስሮ
በነበረበት ወቅት ወንጌሉንና ራዕዩን ጽፏል። አይገርምህም
ሐዋርያው ዩሐንስ በእስር እያለ ነው ራዕዩን የጻፈው!!!
ሐዋርያው ቅ/ጳውሎስ ደግሞ በቀዝቃዛ እስር ቤት እያለ ብዙ
መልእክታቱን ጻፈ!!! ሐዋርያቱ በእስር ቢሆኑ እንኳን
ስለቅድስት ቤተክርስቲያን አገልግሎት አብዝተው ያስቡ ነበር።
የሐዋርያቱ ብርታት ያበርታን።
ዩሐንስ ወንጌሉን በፍጥሞ ደሴት ሲጽፍ እንዲህ ብሎ ጀመረ፦
ዩሐንስ 1:1
+++ በመጀመሪያ ቃል ነበረ; ቃልም በእግዚአብሔር ዘንድ
ነበረ ቃልም እግዚአብሔር ነበረ።እኛም በቅዳሴ ላይ ሁሌ
የዩሐንስ ወንጌል ሲነበብ ቀዳሚሁ ቃል ሥጋ ኾነ ወሃደረ
ላዕሌነ ብለን እንቀበላለን። ግሩም ዜማ ከግሩም ሚስጢር
ጋር አባቶቻችን አወረሱን።
እስቲ ሚስጢሩን እንይ፦
በመጀመሪያ ቃል ነበረ፦ እንደምናውቀው ቃል ኢየሱስ
ክርስቶስ ነው። ኢየሱስ ክርስቶስ አልፋና ዖሜጋ መጀመሪያና
መጨረሻ ነውና ራዕ 22:12። ቃልም እግዚአብሔር ነበር፦
መጽሃፍ አንባቢው ያስተውል ይላል; ምን እንደሚል ልብ
እንበል “ቃልም እግዚአብሔር ነበር” ሐዋርያው በመጀመሪያ
ቃል ነበር ብሎን ነበር; ያ ቃል እግዚአሔር እንደሆነ
አስረዳን!!! በዚሁ ምዕራፍ ላይ ወረድ ብሎ /ዩሐንስ 1:14/
“ያ ቃል ሥጋ ሆነ ይለናል” እስቲ ጥያቄ እንጠያየቅ; ሐዋርያው
ያ ቃል ሥጋ ሆነ ብሏል ከማን? ከማን ሥጋን ነሳ?
ከእመቤታችን ከቅድስት ድንግል ማርያም ከሥጋዋ ሥጋ ከነፍሷ
ነፍስ ነስቶ በኤፍራታ በቤቴልሔም ተወለደ።
+++ የፍጥሞ ደሴት ታሪክ እነሆ፦ ሐዋርያው ዩሐንስ በፍጥሞ
ደሴት ወንጌሉን መጻፍ ሲጀምር የመለኮትን ነገር ጽፎ
የሚጨርስ መስሎት ብእሩን አነሳ። በመጀመሪያ ቃል ነበረ
አለና ሊጨርስ አሰበ፤ ያኔ መልአኩ ቅ/ሚካኤል ተገልጦ
በፍጥሞ ደሴት ያለችውን ባህር በእንቁላል ቅርፊት እየቀዳ
ወደ መሬት ሲያፈስ አየው; ሐዋርያው ዩሐንስም እንዴት ይህ
ታላቅ ባሕር በእንቁላል ቅርፊት ያልቃል ብሎ ጠየቀው;
መልአኩም እኔስ ብሞክር ፍጥረትን ነው አንተስ የፈጣሪን
ባሕርይ የሚያልቅ መስሎህ ትሞክር አይደለምን አለው። ያኔ
ሐዋርያው ዩሐንስ ይህን ተረድቶ ወዲያው ከእግዚአብሔር
የተላከ ስሙ ዩሐንስ የሚባል አንድ ሰው አውቃለሁ ብሎ
ስለመጥምቁ ዩሐንስ ታሪክ የቀጠለውም በዚሁ ምክንያት
ነበር። ዩሐንስ 1:19
ከሐዋርያው፣ ከዮሐንስ ወልደ ነጎድጓድ ረድኤትና በረከት
ይክፈለን ምልጃና ጸሎት ከሁላች ጋር ይሁን አሜን !!!
ወስብሐት ለእግዚአብሔር ወለወላዲቱ ድንግል ወለመስቀሉ
ክቡር ይቆየን አሜን።
ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ነኝ:=>+*"+<+>††መጋቢት 5 ፃድቁ አቡነ ገ/መንፈስ ቅዱስ ዓመታዊ ክብረ በዓል ††
መጋቢት 5 ፃድቁ አቡነ ገ/መንፈስ ቅዱስ ዓመታዊ ክብረ
በዓል በደመቀ ሁኔታ ተከብሮ ይውላል ።
በዚህ እለት እምናከብረው የእረፍት መታሰቢያቸውን ሲሆን
ከገድላቸውም እንዲህ ተፅፎ እናገኘዋለን ።
ፃድቁ አቡነ ገብረ መንፈስ ቅዱስ የተወለዱት ግብፅ ንሂሳ
በምትባል ቦታ ከአባታቸው ስምዖን ከእናታው አቅሌስያ ነው።
በአጠቃላይ የኖሩበት ዕድሜ 562 አመት ሲሆን 300
ዓመቱን በግብጽ 262 ቱን በኢትዮጵያ 100 ዓመት በዝቋላ
በተጋድሎ ያሳለፉ ታላቅ አባት ናቸው።
መጋቢት 5 በገድለ አቡነ ገ/መንፈስ ቅዱስ
ዕለቱ ቅዳሜ ለእሁድ አጥቢያ ሰዓቱ ከሌሊቱ ስድስት ሰዓት
ሆኗል፤ አሁንም ህማሙን እየታገለ እያላበው በድካም
ለፍጥረቱ ሁሉ ይለምናል፤ “አቤቱ ህዝብህን አድን ርስትህን
ኢትዮጰያንም ባርክ” ይላል። ህመም የጀመረው መጋቢት 3
ዓርብ ቀን ነው፤መታመሙን የሰሙ እንደርሱ ቅዱሳን የሆኑት
ዘርአ ቡሩክ፤ ፍሬ ቅዱስ፤ያዕቆብ፤ብንያምና ዮሴፍ እንዲሁም
በወቅቱ የኢትዮጰያ ንጉስ የነበረው እንድርያስ ሊጠይቁት
ተሰብስበዋል ወደ አጠገቡ መድረስ ግን አልተቻላቸውም
አባታችን ገብረመንፈስ ቅዱስ የሚጋርደው እንጨት ዛፍ
በሌለበት በርሃ እንደ አንበሳ ተኝቶ አዩት በላዩ ያረፈው
የእግዚያብሔር ጸጋ ከፊቱ የሚወጣው ብርሃን ቀይ መልኩ
ረዥም የራስ ጠጉሩ እንደ ነጭ ሐር የሚሆን ጽሕሙ
አስደነቃቸው። ከሌሊቱ ሰባት ሰዓት ሲሆን ከሰማይ ታላቅ
ነጎድጓድ ድምጽ ተሰማ ጌታችን መላአክትን አስከትሎ ወደ
አባታችን ወረደ፤ ከሰማይ ወደ ምድር ህብሩ አምሳያው ልዩ
ልዩ የሆነ እንደ ጸሐይና እንደ ጨረቃ የሚያበራ እንደ
ወንጪፍ ድንጋይ ይወረወር ነበር ከዚያ የነበሩ ሁሉ ፈሩ ወደ
ኃላም ሸሹ ምድር ራደች ተራሮች ኮረብቶች ተናወጡ ብርቱ
ጩኸት
ንውጽውጽታ ሆነ። “ወዳጄ ገብረመንፈስ ቅዱስ ሰላም ላንተ
ይሁን” እነሆ የማይታበል ቃል ኪዳን እገባልኃለው ስምህን
የጠራ መታሰቢያህን ያደረገውን፤ እጣን ቋጥሮ ግብር ሰፍሮ
መባ ይዞ ቤትህ የመጣውን እምርልኃለው አንተ ከገባህበት
ገነት መንግስተ ሰማያት አገባዋለሁ አለው፤ አባታችንም
“አቤቱ ጌታ ሆይ የኢትዮጰያን ህዝብ ማርልኝ” አለው፤ እነሆ
ምሬልኃለው አስራት በኩራት አድርጌም ሰጥቼሃለው፤
ከመጋቢት አምስት ቀን ጀምሮ ዝክርህን ያድርጉ
በአማላጅነትህም ይማጸኑ አለው። ከዚህ በኃላ ሰባቱ ሊቃነ
መላእክት የአባታችንን ነፍስ ሊቀበሉ ወረዱ በታላቅ
ምስጋናም ወደ ሰማይ አሳረጉት ስጋውንም ይዘውት ሄዱ የት
እንደተቀበረ ግን እስካሁን አይታወቅም አንዳንዱ
በእየሩሳሌም ነው ይላሉ፤ ሌላው በምድረ ከብድ ነው ይላል
ግን እስካሁን ልክ እንደ ሊቀ ነብያት ሙሴ ስጋ የት
እንደተቀበረ አይታወቅም። ገድሉ ትሩፋቱ ከሰማይ ከዋክብት
ከምድር አሸዋ ይበዛል ኢትዮጰያን አብዝቶ ይወዳታል፤
ምድራዊ ምግብ አልተመገበም የእናቱን ጡት እንኳን
አልጠባም፤ ልብስ፤ መጠለያ አልፈለገም፤ የክረምት ቁር የበጋ
ሐሩር እየተፈራረቀበት በተጋድሎ 562 ዓመት ኖረ፤ በዛሬዋ
ቀን ሩጫውን ጨረሰ። ለእግዚያብሔር ምስጋና ይሁን
እኛንም ከአባታችን በረከት ያሳትፈን።
አምላከ ገ/መንፈስ ቅዱስ መንገዱን ያብራልን ። ገድሉንም
ሰሚወች ብቻ ሳንሆን እምንማርበት ያድርግልን ።
በዓል በደመቀ ሁኔታ ተከብሮ ይውላል ።
በዚህ እለት እምናከብረው የእረፍት መታሰቢያቸውን ሲሆን
ከገድላቸውም እንዲህ ተፅፎ እናገኘዋለን ።
ፃድቁ አቡነ ገብረ መንፈስ ቅዱስ የተወለዱት ግብፅ ንሂሳ
በምትባል ቦታ ከአባታቸው ስምዖን ከእናታው አቅሌስያ ነው።
በአጠቃላይ የኖሩበት ዕድሜ 562 አመት ሲሆን 300
ዓመቱን በግብጽ 262 ቱን በኢትዮጵያ 100 ዓመት በዝቋላ
በተጋድሎ ያሳለፉ ታላቅ አባት ናቸው።
መጋቢት 5 በገድለ አቡነ ገ/መንፈስ ቅዱስ
ዕለቱ ቅዳሜ ለእሁድ አጥቢያ ሰዓቱ ከሌሊቱ ስድስት ሰዓት
ሆኗል፤ አሁንም ህማሙን እየታገለ እያላበው በድካም
ለፍጥረቱ ሁሉ ይለምናል፤ “አቤቱ ህዝብህን አድን ርስትህን
ኢትዮጰያንም ባርክ” ይላል። ህመም የጀመረው መጋቢት 3
ዓርብ ቀን ነው፤መታመሙን የሰሙ እንደርሱ ቅዱሳን የሆኑት
ዘርአ ቡሩክ፤ ፍሬ ቅዱስ፤ያዕቆብ፤ብንያምና ዮሴፍ እንዲሁም
በወቅቱ የኢትዮጰያ ንጉስ የነበረው እንድርያስ ሊጠይቁት
ተሰብስበዋል ወደ አጠገቡ መድረስ ግን አልተቻላቸውም
አባታችን ገብረመንፈስ ቅዱስ የሚጋርደው እንጨት ዛፍ
በሌለበት በርሃ እንደ አንበሳ ተኝቶ አዩት በላዩ ያረፈው
የእግዚያብሔር ጸጋ ከፊቱ የሚወጣው ብርሃን ቀይ መልኩ
ረዥም የራስ ጠጉሩ እንደ ነጭ ሐር የሚሆን ጽሕሙ
አስደነቃቸው። ከሌሊቱ ሰባት ሰዓት ሲሆን ከሰማይ ታላቅ
ነጎድጓድ ድምጽ ተሰማ ጌታችን መላአክትን አስከትሎ ወደ
አባታችን ወረደ፤ ከሰማይ ወደ ምድር ህብሩ አምሳያው ልዩ
ልዩ የሆነ እንደ ጸሐይና እንደ ጨረቃ የሚያበራ እንደ
ወንጪፍ ድንጋይ ይወረወር ነበር ከዚያ የነበሩ ሁሉ ፈሩ ወደ
ኃላም ሸሹ ምድር ራደች ተራሮች ኮረብቶች ተናወጡ ብርቱ
ጩኸት
ንውጽውጽታ ሆነ። “ወዳጄ ገብረመንፈስ ቅዱስ ሰላም ላንተ
ይሁን” እነሆ የማይታበል ቃል ኪዳን እገባልኃለው ስምህን
የጠራ መታሰቢያህን ያደረገውን፤ እጣን ቋጥሮ ግብር ሰፍሮ
መባ ይዞ ቤትህ የመጣውን እምርልኃለው አንተ ከገባህበት
ገነት መንግስተ ሰማያት አገባዋለሁ አለው፤ አባታችንም
“አቤቱ ጌታ ሆይ የኢትዮጰያን ህዝብ ማርልኝ” አለው፤ እነሆ
ምሬልኃለው አስራት በኩራት አድርጌም ሰጥቼሃለው፤
ከመጋቢት አምስት ቀን ጀምሮ ዝክርህን ያድርጉ
በአማላጅነትህም ይማጸኑ አለው። ከዚህ በኃላ ሰባቱ ሊቃነ
መላእክት የአባታችንን ነፍስ ሊቀበሉ ወረዱ በታላቅ
ምስጋናም ወደ ሰማይ አሳረጉት ስጋውንም ይዘውት ሄዱ የት
እንደተቀበረ ግን እስካሁን አይታወቅም አንዳንዱ
በእየሩሳሌም ነው ይላሉ፤ ሌላው በምድረ ከብድ ነው ይላል
ግን እስካሁን ልክ እንደ ሊቀ ነብያት ሙሴ ስጋ የት
እንደተቀበረ አይታወቅም። ገድሉ ትሩፋቱ ከሰማይ ከዋክብት
ከምድር አሸዋ ይበዛል ኢትዮጰያን አብዝቶ ይወዳታል፤
ምድራዊ ምግብ አልተመገበም የእናቱን ጡት እንኳን
አልጠባም፤ ልብስ፤ መጠለያ አልፈለገም፤ የክረምት ቁር የበጋ
ሐሩር እየተፈራረቀበት በተጋድሎ 562 ዓመት ኖረ፤ በዛሬዋ
ቀን ሩጫውን ጨረሰ። ለእግዚያብሔር ምስጋና ይሁን
እኛንም ከአባታችን በረከት ያሳትፈን።
አምላከ ገ/መንፈስ ቅዱስ መንገዱን ያብራልን ። ገድሉንም
ሰሚወች ብቻ ሳንሆን እምንማርበት ያድርግልን ።
Friday, March 3, 2017
ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ነኝ:=>+*"+<+>††የአብይ ጾም ሦስተኛ ሳምንት ምኩራብ††+<+>
ምኩራብ (የዐቢይ ጾም ሦስተኛ ሳምንት)
(ዮሐ. 2÷12-ፍጻ.)፡- ከዚህም በኋላ እርሱና እናቱ÷
ወንድሞቹና ደቀ መዛሙርቱም ወደ ቅፍርናሆም ወረዱ፤
በዚያም ብዙ ያይደለ ጥቂት ቀን ተቀመጡ፡፡ የአይሁድም
የፋሲካቸው በዓል ቀርቦ ነበር፤ ጌታችን ኢየሱስም ወደ
ኢየሩሳሌም ወጣ፡፡ በቤተ መቅደስም በሬዎችንና በጎችን÷
ርግቦችንም የሚሸጡትን÷ገንዘብ ለዋጮችንም ተቀምጠው
አገኘ፡፡ የገመድም ጅራፍ አበጀ፤ በጎችንና በሬዎችን÷ ሁሉንም
ከቤተ መቅደስ አስወጣ፤ የለዋጮችንም ገንዘብ በተነ፤
ገበታዎቻቸውንም ገለበጠ፡፡ ርግብ ሻጮችንም÷ “ይህን
ከዚህ አውጡ፤ የአባቴን ቤት የንግድ ቤት አታድርጉ”
አላቸው፡፡ ደቀ መዛሙርቱም÷ “የቤትህ ቅናት በላኝ” የሚል
ቃል ተጽፎ እንዳለ ዐሰቡ፡፡ አይሁድም መልሰው÷ “ይህን
የምታደርግ ምን ምልክት ታሳያለህ?” አሉት፡፡ ጌታችን
ኢየሱስም÷ “ይህን ቤተ መቅደስ አፍርሱት፤ በሦስተኛውም
ቀን አነሣዋለሁ” ብሎ መለሰላቸው፡፡ አይሁድም÷ “ይህ ቤተ
መቅደስ በአርባ ስድስት ዓመት ተሠራ፤ አንተስ በሦስት ቀኖች
ውስጥ ታነሣዋለህን?” አሉት፡፡ እርሱ ግን ይህን የተናገረው
ቤተ መቅደስ ስለ ተባለ ሰውነቱ ነበር፡፡ ከሙታን በተነሣ
ጊዜም ደቀ መዛሙርቱ ስለዚህ እንደ ነገራቸው ዐሰቡ፤
በመጻሕፍት ቃልና ጌታችን ኢየሱስ በነገራቸውም ነገር
አመኑ፡፡ ጌታችን ኢየሱስም በፋሲካ በዓል በኢየሩሳለም ሳለ
ብዙ ሰዎች ያደረገውን ተአምራት ባዩ ጊዜ በስሙ አመኑ፡፡
እርሱ ጌታችን ኢየሱስ ግን አያምናቸውም ነበር፤ ሁሉን
እያንዳንዱን ያውቀዋልና፡፡ የሰውንም ግብሩን ሊነግሩት
አይሻም፤ እርሱ በሰው ያለውን ያውቅ ነበርና፡፡(ዮሐ. 2÷12-
ፍጻ.)
የዕለተ ሰንበት መዝሙር (ከጾመ ድጓ)
ቦአ ኢየሱስ ምኩራበ አይሁድ ወመሐረ ቃለ ሃይማኖት
ወይቤሎሙ ምጽዋተ አበድር እመሥዋዕት አነ ውእቱ እግዚኣ
ለሰንበት ወአቡሃ ለምሕረት እግዚኣ ውእቱ ለሰንበት ወልደ
እጓለ እመሕያው ኢትግበሩ ቤተ አቡየ ቤተ ምስያጥ ቤትየሰ
ቤተ ጸሎት ይሰመይ ቦአ ምኩራቦሙ ወገሠፆሙ ያርምሙ
አንከሩ ምህሮቶ ሞገስ ቃሉ ወጣዕመ ነገሩ ወሣዕሣዓ አፉሁ፡፡
ትርጉም:- ጌታችን ኢየሱስ ወደ አይሁድ ምኩራብ ገባ፤
የሃይማኖት ቃልን አስተማረ፤ ከመሥዋዕት ይልቅ ምሕረትን
እወዳለሁ፤የሰንበት ጌታዋ የምሕረት አባቷም እኔ ነኝ፤ የሰው
ልጅም የሰንበት ጌታዋ ነው ፡፡ያባቴን ቤት የንግድ ቦታ
አታድርጉት፤ቤቴስ የጸሎት ቤት ይባላል (እያለ የሃይማኖትን
ቃል አስተማራቸው፡)፡ ወደ ምኩራባቸውም ገብቶ ዝም ይሉ
ዘንድ ገሠፃቸው፤ እነርሱም ትምህርቱን፣ የቃሉን ግርማ፣
የአነጋገሩን ጣዕምና፣ የአንደበቱን ቅልጥፍና አደነቁ።
እንደ ቤተክርስቲያናችን ሥርዓትና ትውፊት መሠረት በዐቢይ
ጾም ስምንቱ ሰንበታት ሊዘመር የተዘጋጀው የጾመ ድጓው
መዝሙር ነው፡፡ በየሰንበቱ የሚነበቡት የመጽሐፍ ቅዱስ
ምንባባት ፣ የሚዘመረው የዳዊት መዝሙር (ምስባክ)
ከሰንበቱ ስያሜ ጋር የሚያያዙና የሚዛመዱ ናቸው፡፡
በሰንበታቱ ውስጥ የሚነበበውና የሚዘመረውም ጌታችን
በመዋዕለ ስብከቱ ያስተማራቸውን ትምህርቶችና የሠራቸውን
ዋና ዋና ተዓምራትና መንክራት የሚመለከቱ ናቸው፡፡ ጾሙ
የጌታ ጾም ስለሆነ ሁሉም መዝሙራትና ምንባባት ከጌታ
ትምህርትና ሥራ ጋር የተያያዙ ናቸው፡፡ በዚህ መሠረት
ሦስተኛው ሰንበት ምኩራብ ተብሎ ተሰይሟል፡፡
ምኩራብ ማለት ሰቀላ መሰል አዳራሽ ማለት ነው። አይሁድ
ስግደትና መሥዋዕታቸውን የሚያቀርቡት በኢየሩሳሌም
ባለው መቅደስ ብቻ ነው ብለው ቢያምኑም (ዮሐ 4፥20)
፤በየተበተኑበት ቦታ ምኩራብ እየሠሩ ትምህርተ ኦሪትን
በመማር ሃይማኖታቸውን ያፀኑ ነበር። ምኲራብ የአይሁድ
የጸሎት ቤት ሲሆን በብሉይ ኪዳን ዘመን የአይሁድ አምልኮ
በኢየሩሳሌም በነበረው ቤተ መቅደስና በሥርዓቱ የተመሠረተ
ነበር፡፡ የመጽሐፍ ቅዱስ መዝገበ ቃላት እንደሚገልጸው
ናቡከደነጾር የአይሁዳውያንን ቤተ መቅደሱን አፍርሶ
ሕዝቡንም ወደባቢሎን ካፈለሰ ጊዜ ጀምሮ አይሁድ
በሚገኙባቸው ሥፍራዎች ሁሉ ለጸሎትና ለማኅበረተኛነት ልዩ
ቤት ሊሠሩ እንደጀመሩ ይገልጻል፡፡
አይሁድ በምኲራቦቻቸው የሕግንና የነቢያትን መጻሕፍት /
የብራና ጥቅሎች/ በአንድ ሣጥን ውስጥ ያስቀምጣሉ፡፡
በመሆኑ የጸሎት ሥፍራዎቻቸውን ለትምህርትና ለአምልኮ
ይጠቀሙባቸዋል፡፡ በሕገ ኦሪት የአይሁዳውያን ወደ ቤተ
መቅደስ መሄድ ሕግ ነበር፡፡ በተለያዩ ጊዜያት ለተለያዩ
ተግባራት ከሚሄዱበትም ይልቅ በዓመት አንዴ የሚቀርበውን
መሥዋዕትና መብዓ ለመስጠት ወደ ቤተ መቅደስ ይወጡ
ነበር፡፡ ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስም ሕግ ሊፈጽም ወደ ቤተ
መቅደስ ይሔድ ነበር፡፡ “ዐሥራ ሁለት ዓመትም በሞላው
ጊዜ እንዳስለመዱ ወደ ኢየሩሳሌም ለበዓል ወጡ” እንዲል /
ሉቃ.2፥42/ “ዕለት ዕለትም በቤተ መቅደስ /ምኩራብ/
ያስተምር ነበር፡፡” /ሉቃ.19፥47/ ፡፡
በዚሁ ዕለት የሚዘመረው ጾመ ድጓ ከዋዜማው ጀምሮ እስከ
ሰላሙ ድረስ በዕለተ ሰንበት “ቦአ ኢየሱስ ምኩራበ አይሁድ
ኢየሱስ በሰንበት ቀን ወደ አይሁድ ምኩራብ ገባ” እያለ
ኢየሱስ በአይሁድ ምኩራብ ማስተማሩን እያነሳ ስለሚዘምር
ይህን ሰንበት ለዚህ ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በምኩራብ
እየገባ ለማስተማሩና በምኩራብ የሚሸጡ የሚለውጡ
ነጋዴዎችን ስለማስወጣቱ ቤተ መቅደሱን ስለማስከበሩ
መታሰቢያ ሆኖ ነው፡፡ማቴ21፡12
ጌታችን በምኩራብ እየተገኘ ሲያስተምር ትምህርቱን ሕግን
አውቆ እንደሚያሳውቅ ሠራዔ ሕግ ስለሆነ በሙሉ ሥልጣንና
ኃይል ያስተምር ነበር፡፡“ቦአ ኢየሱስ ምኩራበ አይሁድ
ወመሐረ ቃለ ሃይማኖት ወይቤሎሙ ምጽዋተ አበድር
እመሥዋዕትአነ ውእቱ እግዚኣ ለሰንበት ወአቡሃ ለምሕረት
እግዚኣ ውእቱ ለሰንበት ወልደ እጓለ እመሕያውኢትግበሩ ቤተ
አቡየ ቤተ ምስያጥ ቤትየሰ ቤተ ጸሎት ይሰመይ ቦአ
ምኩራቦሙ ወገሠፆሙያርምሙ አንከሩ ምህሮቶ ሞገስ ቃሉ
ወጣዕመ ነገሩ ወሣዕሣዓ አፉሁ፡፡ ጌታችን ኢየሱስ ወደ
አይሁድ ምኩራብ ገባ፤ የሃይማኖት ቃልን
አስተማረ፤ከመሥዋዕት ይልቅ ምሕረትን እወዳለሁ፤የሰንበት
ጌታዋ የምሕረት አባቷም እኔ ነኝ፤ የሰው ልጅምየሰንበት
ጌታዋ ነው ፡፡ያባቴን ቤት የንግድ ቦታ አታድርጉት፤ቤቴስ
የጸሎት ቤት ይባላል (እያለየሃይማኖትን ቃል አስተማራቸው)
፤ ወደ ምኩራባቸውም ገብቶ ዝም ይሉ ዘንድ
ገሠፃቸው፤እነርሱም ትምህርቱን፣ የቃሉን ግርማ፣ የአነጋገሩን
ጣዕምና፣ የአንደበቱን ቅልጥፍና አደነቁ። የዕለተ ሰንበት
መዝሙር (ከጾመ ድጓ)
ቅዱስ ዳዊትም አስቀድሞ በተናረው ትንቢት መሠረት ጌታ
ለቤተመቅደሱ ቀንቶ አጽድቶት ነበር፡፡
መዝ 68፡9
እስመ ቅንዐተ ቤትከ በልዐኒ
ትዕይርቶሙ ለእለ ይትዔየሩከ ወድቀ ላዕሌየ
ወቀጻዕክዋ በጾም ለነፍስየ፡፡
ትርጉም፦የቤትህ ቅንዓት በልታኛለችና
የሚሰድቡህም ስድብ በላዬ ወድቆአልና
ነፍሴን በጾም አስመረርሁአት፡፡
በነብዩ በኢሳይያስ እንደተጻፈ ጌታ በአይሁድ ምኩራብ ገብቶ
መጽሐፍ እንዲሰጡት ጠይቆ የሚሰሙት ቃል ዛሬ በጆሯቸው
እንደተፈጸመ እንዲህ ሲል እንደነገራቸው፡፡ “ኢየሱስም
በመንፈስ ኃይል ወደ ገሊላ ተመለሰ፤ ስለ እርሱም በዙሪያው
ባለችው አገር ሁሉ ዝና ወጣ። እርሱም በምኵራባቸው
ያስተምር ሁሉም ያመሰግኑት ነበር። ወዳደገበትም ወደ
ናዝሬት መጣ፤ እንደ ልማዱም በሰንበት ቀን ወደ ምኵራብ
ገባ ሊያነብም ተነሣ። የነቢዩንም የኢሳይያስን መጽሐፍ ሰጡት
መጽሐፉንም በተረተረ ጊዜ። “የጌታ መንፈስ በእኔ ላይ ነው
ለድሆች ወንጌልን እሰብክ ዘንድ ቀብቶኛልና ለታሰሩትም
መፈታትን ለዕውሮችም ማየትን እሰብክ ዘንድ የተጠቁትንም
ነጻ አወጣ ዘንድ የተወደደችውንም የጌታን ዓመት እሰብክ
ዘንድ ልኮኛል፡፡” ተብሎ የተጻፈበትን ስፍራ አገኘ።
መጽሐፉንም ጠቅልሎ ለአገልጋዩ ሰጠውና ተቀመጠ
በምኵራብም የነበሩት ሁሉ ትኵር ብለው ይመለከቱት ነበር።
እርሱም። “ዛሬ ይህ መጽሐፍ በጆሮአችሁ ተፈጸመ ”ይላቸው
ጀመር። ሁሉም ይመሰክሩለት ነበር ከአፉም ከሚወጣው
ከጸጋው ቃል የተነሣ እየተደነቁ። “ይህ የዮሴፍ ልጅ
አይደለምን? ”ይሉ ነበር። እርሱም። ያለ ጥርጥር ይህን
ምሳሌ። “ባለ መድኃኒት ሆይ ራስህን ፈውስ፤ በቅፍርናሆም
እንዳደረግኸው የሰማነውን ሁሉ በዚህ በገዛ አገርህ ደግሞ
አድርግ ትሉኛላችሁ” አላቸው። ሉቃ.4፡14
“ከዚህ በኋላ ከእናቱና ከወንድሞቹ ከደቀመዛሙርቱም ጋር
ወደ ቅፍርናሆም ወረደ፣ በዚያም ጥቂት ቀን ኖሩ፡፡ የአይሁድ
ፋሲካም ቀርቦ ነበር ኢየሱስም ወደ ኢየሩሳሌም ወጣ፡፡ ወደ
መቅደስም በሬዎችንና በጎችን ርግቦችንም የሚሸጡትን
ገንዘብ ለዋጮችንም ተቀምጠው አገኘ፤ የገመድም ጅራፍ
አበጅቶ ሁሉን በጎችንም በሬዎችንም ከመቅደስ አወጣቸው፣
የለዋጮችንም ገንዘብ አፈሰሰ፣ ገበታዎቻቸውንም ገለበጠ፣
ርግብ ሻጪዎችንም ይህን ከዚህ ውሰዱ፡፡ የአባቴን ቤት
የንግድ ቤት አታድርጉት አላቸው፡፡ ደቀ መዛሙርቱም የቤትህ
ቅናት ይበላኛል ተብሎ እንደተጻፈ አሰቡ፡፡
አይሁድ መልሰው ይህን ስለምታደርግ ምን ምልክ ት
ታሳየናለህ አሉት፡፡ ኢየሱስም መልሶ ይህን ቤተመቅደስ
አፍርሱት በሦስት ቀንም አነሣዋለሁ አላቸው ስለዚህ አይሁድ
ይህ ቤተ መቅደስ ከአርባ ስድስት ዓመት ጀምሮ ይሠራ ነበር፣
አንተስ በሦስት ቀን ታነሣዋለህን አሉት፡፡ እርሱ ግን ስለ
ሰውነቱ ቤተመቅደስ ይል ነበር፡፡”ዮሐ 2፡12-25 ስለዚህ
ከሙታን ከተነሣ በኋላ ደቀመዛሙርቱ ይህን እንደተናገረ
አሰቡና መጽሐፍንና ኢየሱስ የተናገረውን ቃል አመኑ፡፡
በፋሲካ በዓልም በኢየሩሳሌም ሳለ፣ ያደረገውን ምልክት ባዩ
ጊዜ ብዙ ሰዎች በስሙ አመኑ ነገር ግን ኢየሱስ ሰዎችን ሁሉ
ያውቅ ነበር፤ ስለ ሰውም ማንም ሊመሰክር አያስፈልገውም
ነበርና አይተማመናቸውም ነበር፣ ራሱ በሰው ያለውን ያውቅ
ነበርና፡፡
(ዮሐ. 2÷12-ፍጻ.)፡- ከዚህም በኋላ እርሱና እናቱ÷
ወንድሞቹና ደቀ መዛሙርቱም ወደ ቅፍርናሆም ወረዱ፤
በዚያም ብዙ ያይደለ ጥቂት ቀን ተቀመጡ፡፡ የአይሁድም
የፋሲካቸው በዓል ቀርቦ ነበር፤ ጌታችን ኢየሱስም ወደ
ኢየሩሳሌም ወጣ፡፡ በቤተ መቅደስም በሬዎችንና በጎችን÷
ርግቦችንም የሚሸጡትን÷ገንዘብ ለዋጮችንም ተቀምጠው
አገኘ፡፡ የገመድም ጅራፍ አበጀ፤ በጎችንና በሬዎችን÷ ሁሉንም
ከቤተ መቅደስ አስወጣ፤ የለዋጮችንም ገንዘብ በተነ፤
ገበታዎቻቸውንም ገለበጠ፡፡ ርግብ ሻጮችንም÷ “ይህን
ከዚህ አውጡ፤ የአባቴን ቤት የንግድ ቤት አታድርጉ”
አላቸው፡፡ ደቀ መዛሙርቱም÷ “የቤትህ ቅናት በላኝ” የሚል
ቃል ተጽፎ እንዳለ ዐሰቡ፡፡ አይሁድም መልሰው÷ “ይህን
የምታደርግ ምን ምልክት ታሳያለህ?” አሉት፡፡ ጌታችን
ኢየሱስም÷ “ይህን ቤተ መቅደስ አፍርሱት፤ በሦስተኛውም
ቀን አነሣዋለሁ” ብሎ መለሰላቸው፡፡ አይሁድም÷ “ይህ ቤተ
መቅደስ በአርባ ስድስት ዓመት ተሠራ፤ አንተስ በሦስት ቀኖች
ውስጥ ታነሣዋለህን?” አሉት፡፡ እርሱ ግን ይህን የተናገረው
ቤተ መቅደስ ስለ ተባለ ሰውነቱ ነበር፡፡ ከሙታን በተነሣ
ጊዜም ደቀ መዛሙርቱ ስለዚህ እንደ ነገራቸው ዐሰቡ፤
በመጻሕፍት ቃልና ጌታችን ኢየሱስ በነገራቸውም ነገር
አመኑ፡፡ ጌታችን ኢየሱስም በፋሲካ በዓል በኢየሩሳለም ሳለ
ብዙ ሰዎች ያደረገውን ተአምራት ባዩ ጊዜ በስሙ አመኑ፡፡
እርሱ ጌታችን ኢየሱስ ግን አያምናቸውም ነበር፤ ሁሉን
እያንዳንዱን ያውቀዋልና፡፡ የሰውንም ግብሩን ሊነግሩት
አይሻም፤ እርሱ በሰው ያለውን ያውቅ ነበርና፡፡(ዮሐ. 2÷12-
ፍጻ.)
የዕለተ ሰንበት መዝሙር (ከጾመ ድጓ)
ቦአ ኢየሱስ ምኩራበ አይሁድ ወመሐረ ቃለ ሃይማኖት
ወይቤሎሙ ምጽዋተ አበድር እመሥዋዕት አነ ውእቱ እግዚኣ
ለሰንበት ወአቡሃ ለምሕረት እግዚኣ ውእቱ ለሰንበት ወልደ
እጓለ እመሕያው ኢትግበሩ ቤተ አቡየ ቤተ ምስያጥ ቤትየሰ
ቤተ ጸሎት ይሰመይ ቦአ ምኩራቦሙ ወገሠፆሙ ያርምሙ
አንከሩ ምህሮቶ ሞገስ ቃሉ ወጣዕመ ነገሩ ወሣዕሣዓ አፉሁ፡፡
ትርጉም:- ጌታችን ኢየሱስ ወደ አይሁድ ምኩራብ ገባ፤
የሃይማኖት ቃልን አስተማረ፤ ከመሥዋዕት ይልቅ ምሕረትን
እወዳለሁ፤የሰንበት ጌታዋ የምሕረት አባቷም እኔ ነኝ፤ የሰው
ልጅም የሰንበት ጌታዋ ነው ፡፡ያባቴን ቤት የንግድ ቦታ
አታድርጉት፤ቤቴስ የጸሎት ቤት ይባላል (እያለ የሃይማኖትን
ቃል አስተማራቸው፡)፡ ወደ ምኩራባቸውም ገብቶ ዝም ይሉ
ዘንድ ገሠፃቸው፤ እነርሱም ትምህርቱን፣ የቃሉን ግርማ፣
የአነጋገሩን ጣዕምና፣ የአንደበቱን ቅልጥፍና አደነቁ።
እንደ ቤተክርስቲያናችን ሥርዓትና ትውፊት መሠረት በዐቢይ
ጾም ስምንቱ ሰንበታት ሊዘመር የተዘጋጀው የጾመ ድጓው
መዝሙር ነው፡፡ በየሰንበቱ የሚነበቡት የመጽሐፍ ቅዱስ
ምንባባት ፣ የሚዘመረው የዳዊት መዝሙር (ምስባክ)
ከሰንበቱ ስያሜ ጋር የሚያያዙና የሚዛመዱ ናቸው፡፡
በሰንበታቱ ውስጥ የሚነበበውና የሚዘመረውም ጌታችን
በመዋዕለ ስብከቱ ያስተማራቸውን ትምህርቶችና የሠራቸውን
ዋና ዋና ተዓምራትና መንክራት የሚመለከቱ ናቸው፡፡ ጾሙ
የጌታ ጾም ስለሆነ ሁሉም መዝሙራትና ምንባባት ከጌታ
ትምህርትና ሥራ ጋር የተያያዙ ናቸው፡፡ በዚህ መሠረት
ሦስተኛው ሰንበት ምኩራብ ተብሎ ተሰይሟል፡፡
ምኩራብ ማለት ሰቀላ መሰል አዳራሽ ማለት ነው። አይሁድ
ስግደትና መሥዋዕታቸውን የሚያቀርቡት በኢየሩሳሌም
ባለው መቅደስ ብቻ ነው ብለው ቢያምኑም (ዮሐ 4፥20)
፤በየተበተኑበት ቦታ ምኩራብ እየሠሩ ትምህርተ ኦሪትን
በመማር ሃይማኖታቸውን ያፀኑ ነበር። ምኲራብ የአይሁድ
የጸሎት ቤት ሲሆን በብሉይ ኪዳን ዘመን የአይሁድ አምልኮ
በኢየሩሳሌም በነበረው ቤተ መቅደስና በሥርዓቱ የተመሠረተ
ነበር፡፡ የመጽሐፍ ቅዱስ መዝገበ ቃላት እንደሚገልጸው
ናቡከደነጾር የአይሁዳውያንን ቤተ መቅደሱን አፍርሶ
ሕዝቡንም ወደባቢሎን ካፈለሰ ጊዜ ጀምሮ አይሁድ
በሚገኙባቸው ሥፍራዎች ሁሉ ለጸሎትና ለማኅበረተኛነት ልዩ
ቤት ሊሠሩ እንደጀመሩ ይገልጻል፡፡
አይሁድ በምኲራቦቻቸው የሕግንና የነቢያትን መጻሕፍት /
የብራና ጥቅሎች/ በአንድ ሣጥን ውስጥ ያስቀምጣሉ፡፡
በመሆኑ የጸሎት ሥፍራዎቻቸውን ለትምህርትና ለአምልኮ
ይጠቀሙባቸዋል፡፡ በሕገ ኦሪት የአይሁዳውያን ወደ ቤተ
መቅደስ መሄድ ሕግ ነበር፡፡ በተለያዩ ጊዜያት ለተለያዩ
ተግባራት ከሚሄዱበትም ይልቅ በዓመት አንዴ የሚቀርበውን
መሥዋዕትና መብዓ ለመስጠት ወደ ቤተ መቅደስ ይወጡ
ነበር፡፡ ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስም ሕግ ሊፈጽም ወደ ቤተ
መቅደስ ይሔድ ነበር፡፡ “ዐሥራ ሁለት ዓመትም በሞላው
ጊዜ እንዳስለመዱ ወደ ኢየሩሳሌም ለበዓል ወጡ” እንዲል /
ሉቃ.2፥42/ “ዕለት ዕለትም በቤተ መቅደስ /ምኩራብ/
ያስተምር ነበር፡፡” /ሉቃ.19፥47/ ፡፡
በዚሁ ዕለት የሚዘመረው ጾመ ድጓ ከዋዜማው ጀምሮ እስከ
ሰላሙ ድረስ በዕለተ ሰንበት “ቦአ ኢየሱስ ምኩራበ አይሁድ
ኢየሱስ በሰንበት ቀን ወደ አይሁድ ምኩራብ ገባ” እያለ
ኢየሱስ በአይሁድ ምኩራብ ማስተማሩን እያነሳ ስለሚዘምር
ይህን ሰንበት ለዚህ ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በምኩራብ
እየገባ ለማስተማሩና በምኩራብ የሚሸጡ የሚለውጡ
ነጋዴዎችን ስለማስወጣቱ ቤተ መቅደሱን ስለማስከበሩ
መታሰቢያ ሆኖ ነው፡፡ማቴ21፡12
ጌታችን በምኩራብ እየተገኘ ሲያስተምር ትምህርቱን ሕግን
አውቆ እንደሚያሳውቅ ሠራዔ ሕግ ስለሆነ በሙሉ ሥልጣንና
ኃይል ያስተምር ነበር፡፡“ቦአ ኢየሱስ ምኩራበ አይሁድ
ወመሐረ ቃለ ሃይማኖት ወይቤሎሙ ምጽዋተ አበድር
እመሥዋዕትአነ ውእቱ እግዚኣ ለሰንበት ወአቡሃ ለምሕረት
እግዚኣ ውእቱ ለሰንበት ወልደ እጓለ እመሕያውኢትግበሩ ቤተ
አቡየ ቤተ ምስያጥ ቤትየሰ ቤተ ጸሎት ይሰመይ ቦአ
ምኩራቦሙ ወገሠፆሙያርምሙ አንከሩ ምህሮቶ ሞገስ ቃሉ
ወጣዕመ ነገሩ ወሣዕሣዓ አፉሁ፡፡ ጌታችን ኢየሱስ ወደ
አይሁድ ምኩራብ ገባ፤ የሃይማኖት ቃልን
አስተማረ፤ከመሥዋዕት ይልቅ ምሕረትን እወዳለሁ፤የሰንበት
ጌታዋ የምሕረት አባቷም እኔ ነኝ፤ የሰው ልጅምየሰንበት
ጌታዋ ነው ፡፡ያባቴን ቤት የንግድ ቦታ አታድርጉት፤ቤቴስ
የጸሎት ቤት ይባላል (እያለየሃይማኖትን ቃል አስተማራቸው)
፤ ወደ ምኩራባቸውም ገብቶ ዝም ይሉ ዘንድ
ገሠፃቸው፤እነርሱም ትምህርቱን፣ የቃሉን ግርማ፣ የአነጋገሩን
ጣዕምና፣ የአንደበቱን ቅልጥፍና አደነቁ። የዕለተ ሰንበት
መዝሙር (ከጾመ ድጓ)
ቅዱስ ዳዊትም አስቀድሞ በተናረው ትንቢት መሠረት ጌታ
ለቤተመቅደሱ ቀንቶ አጽድቶት ነበር፡፡
መዝ 68፡9
እስመ ቅንዐተ ቤትከ በልዐኒ
ትዕይርቶሙ ለእለ ይትዔየሩከ ወድቀ ላዕሌየ
ወቀጻዕክዋ በጾም ለነፍስየ፡፡
ትርጉም፦የቤትህ ቅንዓት በልታኛለችና
የሚሰድቡህም ስድብ በላዬ ወድቆአልና
ነፍሴን በጾም አስመረርሁአት፡፡
በነብዩ በኢሳይያስ እንደተጻፈ ጌታ በአይሁድ ምኩራብ ገብቶ
መጽሐፍ እንዲሰጡት ጠይቆ የሚሰሙት ቃል ዛሬ በጆሯቸው
እንደተፈጸመ እንዲህ ሲል እንደነገራቸው፡፡ “ኢየሱስም
በመንፈስ ኃይል ወደ ገሊላ ተመለሰ፤ ስለ እርሱም በዙሪያው
ባለችው አገር ሁሉ ዝና ወጣ። እርሱም በምኵራባቸው
ያስተምር ሁሉም ያመሰግኑት ነበር። ወዳደገበትም ወደ
ናዝሬት መጣ፤ እንደ ልማዱም በሰንበት ቀን ወደ ምኵራብ
ገባ ሊያነብም ተነሣ። የነቢዩንም የኢሳይያስን መጽሐፍ ሰጡት
መጽሐፉንም በተረተረ ጊዜ። “የጌታ መንፈስ በእኔ ላይ ነው
ለድሆች ወንጌልን እሰብክ ዘንድ ቀብቶኛልና ለታሰሩትም
መፈታትን ለዕውሮችም ማየትን እሰብክ ዘንድ የተጠቁትንም
ነጻ አወጣ ዘንድ የተወደደችውንም የጌታን ዓመት እሰብክ
ዘንድ ልኮኛል፡፡” ተብሎ የተጻፈበትን ስፍራ አገኘ።
መጽሐፉንም ጠቅልሎ ለአገልጋዩ ሰጠውና ተቀመጠ
በምኵራብም የነበሩት ሁሉ ትኵር ብለው ይመለከቱት ነበር።
እርሱም። “ዛሬ ይህ መጽሐፍ በጆሮአችሁ ተፈጸመ ”ይላቸው
ጀመር። ሁሉም ይመሰክሩለት ነበር ከአፉም ከሚወጣው
ከጸጋው ቃል የተነሣ እየተደነቁ። “ይህ የዮሴፍ ልጅ
አይደለምን? ”ይሉ ነበር። እርሱም። ያለ ጥርጥር ይህን
ምሳሌ። “ባለ መድኃኒት ሆይ ራስህን ፈውስ፤ በቅፍርናሆም
እንዳደረግኸው የሰማነውን ሁሉ በዚህ በገዛ አገርህ ደግሞ
አድርግ ትሉኛላችሁ” አላቸው። ሉቃ.4፡14
“ከዚህ በኋላ ከእናቱና ከወንድሞቹ ከደቀመዛሙርቱም ጋር
ወደ ቅፍርናሆም ወረደ፣ በዚያም ጥቂት ቀን ኖሩ፡፡ የአይሁድ
ፋሲካም ቀርቦ ነበር ኢየሱስም ወደ ኢየሩሳሌም ወጣ፡፡ ወደ
መቅደስም በሬዎችንና በጎችን ርግቦችንም የሚሸጡትን
ገንዘብ ለዋጮችንም ተቀምጠው አገኘ፤ የገመድም ጅራፍ
አበጅቶ ሁሉን በጎችንም በሬዎችንም ከመቅደስ አወጣቸው፣
የለዋጮችንም ገንዘብ አፈሰሰ፣ ገበታዎቻቸውንም ገለበጠ፣
ርግብ ሻጪዎችንም ይህን ከዚህ ውሰዱ፡፡ የአባቴን ቤት
የንግድ ቤት አታድርጉት አላቸው፡፡ ደቀ መዛሙርቱም የቤትህ
ቅናት ይበላኛል ተብሎ እንደተጻፈ አሰቡ፡፡
አይሁድ መልሰው ይህን ስለምታደርግ ምን ምልክ ት
ታሳየናለህ አሉት፡፡ ኢየሱስም መልሶ ይህን ቤተመቅደስ
አፍርሱት በሦስት ቀንም አነሣዋለሁ አላቸው ስለዚህ አይሁድ
ይህ ቤተ መቅደስ ከአርባ ስድስት ዓመት ጀምሮ ይሠራ ነበር፣
አንተስ በሦስት ቀን ታነሣዋለህን አሉት፡፡ እርሱ ግን ስለ
ሰውነቱ ቤተመቅደስ ይል ነበር፡፡”ዮሐ 2፡12-25 ስለዚህ
ከሙታን ከተነሣ በኋላ ደቀመዛሙርቱ ይህን እንደተናገረ
አሰቡና መጽሐፍንና ኢየሱስ የተናገረውን ቃል አመኑ፡፡
በፋሲካ በዓልም በኢየሩሳሌም ሳለ፣ ያደረገውን ምልክት ባዩ
ጊዜ ብዙ ሰዎች በስሙ አመኑ ነገር ግን ኢየሱስ ሰዎችን ሁሉ
ያውቅ ነበር፤ ስለ ሰውም ማንም ሊመሰክር አያስፈልገውም
ነበርና አይተማመናቸውም ነበር፣ ራሱ በሰው ያለውን ያውቅ
ነበርና፡፡
Saturday, February 25, 2017
ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ነኝ:=>+*"+<+>†† የዐቢይ ጾም ሁለተኛ ሳምንት ቅድሰት ††+*"+<+>
ቅድስት ( የዐቢይ ጾም ሁለተኛ ሳምንት )
«ቅድስት» ማለት የዘይቤ ፍችው « የተቀደሰች የተለየች »
ማለት ነው፡፡ ምስጢራዊ መልእክቱ ግን የምስጢረ አድኅኖት
ታላላቅ ሥራውን ለመጀመር መድኀኒታችን ኢየሱስ ክርስቶሰ
በገዳመ ቆሮንቶስ ገብቶ ከቆመ ሳያርፍ፣ ከዘረጋ ሳያጥፍ
የጾማት የአርብዓው ቀንና ሌሊት ልዩ የሆነችና ክብርት ጾም
የምትጀመርበትን ሁለተኛ ሳምንት ከልብ ያሳስበናል፡፡ ማቴ.
4-2
ቅድሰት የዐቢይ ጾም ሁለተኛ ሰንበት ስያሜ ነው፡፡
ስያሜውም
ከኢትዮያዊው የዜማ ሊቅ ከቅዱስ ያሬድ የተገኘ ነው፡፡ ከዚህ
ሰንበት ዋዜማ ጀምሮ ስለ ዕለተ ሰንበት ቅድስና ይዘመራል፡፡
ቅድስት ቤተ ክርስቲያናችንም ሰንበቱን ስለ ቅድስና ልጆቿን
ታስተምርበታለች ፡፡ በቅዳሴ ጊዜ የሚሰበከው ምስባክ ፤
የሚነበቡ መልዕክታት ፤የሐዋርያት ሥራ ና ወንጌል ስለ
ቅድስት
የሚያስተምሩ ናቸው፡፡
‹‹ቅዱስ›› ማለት ልዩ፤ክቡር ማለት ነው፡፡ እግዚአብሔር
አምላካችን በባሕርዩ ቅዱስ ነው፡፡ ይህም ቅድስና ከማንም
ያላገኘው የባሕርይ ገንዘቡ ነው፡፡ መጻሕፍትም የባሕርይ
ቅድስናውን ተባብረው መስክረዋል፡፡ ባባሕርዩ ቅዱስ ስለሆነ
‹‹ቅዱስ፡ቅዱስ፡ቅዱስ›› እየተባለ ይመሰገናል፡፡( ኢሳ 6፡
1-3፤40፡25 ራዕ 15፡4 ፤ 1ሳሙ2፡2-3፡፡) እኛም ቅዱስ
ልጁ
በሥጋ ተገልጦ እንዳስተማረን በየዕለት ጸሎታችን ‹‹ስምህ
ይቀደስ›› እንለዋለን፡፡ የቅድስና ምንጭ ፡ ቅድስናን የሚሰጥ
እርሱ ብቻ ነው፡፡ ‹‹ ቅዱስ›› የሚለው ቃል ለሰዎች ፡
ለመላእክት ፡ ለቦታ ፡ለዕቃ፡ ለዕለታት … ቢቀጸልም
ቅድስናቸው
በባሕርይው ቅዱስ ከሆነው ከእግዚአብሔር የተገኘ ነው፡፡
ይህም
የጸጋ ቅድስና ይባላል፡፡
እግዚአብሔር ቅዱስ ስለሆነ በመልኩና በምሳሌው አክብሮ
የፈጠረንን እኛም ቅዱሳን እንድንሆን ይፈለጋል፡፡ቅዱስ
ጴጥሮስ
‹‹ዳሩ ግን እኔ ቅዱስ ነኝና ቅዱሳን ሁን›› ተብሎ ስለተጻፈ
የጠራቸው ቅዱስ እንደሆነ እናንተ ደግሞ በኑሮአችሁ ሁሉ
ቅዱሳን ሁኑ ›› ያለንም ይህንን ሲያስተምረን ነው፡፡
ከመፈጠራችን አስቀድሞ መጠን በሌለው ፍቅር የወደደን
እግዚአብሔር ካለመኖር ወደ መኖር ያመጣን ፤ለውርደት
ሳይሆን ለክብር፤ለርኩሰት ሳይሆን ለቅድስና፤ለሞት ሳይሆን
ለሕይወት ነው፡፡የመፈጠራችንም ዓላማ በፊቱ በፍጹም
ምግባርና ሃማኖት በመመላለስ ከእርሱ ጋር እንድንኖር ነው፡፡
ብርሃን ከጨለማ፡ ጽድቅ ከኃጢአት፡ጋር ኅብረት የለውምና
ከእርሱ ጋር ለዘላለም ነግሰን ለመኖር በቅድስና መኖር
ይጠበቅብናል፡፡ ቅዱስ ጳውሎስም ‹‹ እግዚአብሔር ለቅድስና
እንጂ ለርኩሰት አልጠራንምና ›› ያለንም ለዚህ ነው፡፡/1ተሰ
4*7/ እግዚአብሔር እኛን የፈጠረበትን አላማ ለኤፌሶን
ክርስቲያኖች እንዲህ ገልጾላቸዋል ‹‹ በክርስቶስ ኢየሱስ
ሰማያዊ ሥፍራ በመንፈሳዊ በረከት ሁሉ የባረከን የጌታችን
የኢየሱስ ክርስቶስ አባት እግዚአብሔር ይመስገን፡፡ ብሎ
ካመሰገነ በኋላ ‹‹ ዓለም ሳይፈጠር በፊቱ ቅዱሳን ፡ንጹሐንና
ያለነውር በፍቅር ያደርገን ዘንድ ለእርሱ መረጠን›› ኤፌ 1፡
3-4
አስቀድሞ ስለወደደንና ስላከበረንም ከሌሎች ፍጥረታት
በተለየ
መልኩ የሚያስፈልገንን ሁሉ አዘጋጅቶ በእጆቹ ካበጀን በኋላ
የሥነ ፍጥረት ዘውድ አድርጎ በገነት አኖረን ፡፡( ዘፍ 1፡26
፤መዝ 8፡1)
የቀደመው አዳም አታድርግ የተባለውን በማድረጉ
በንዝህላልነትና በስንፍና በከይሲ ዲያብሎስም ምክር
ተዋረደ፡፡
በሞተ ሥጋ ላይም ሞተ ነፍስ ፤በርዕደተ መቃብር ላይ ርዕደተ
ሲኦል ተፈረደበት፡ በባሕርዩ ሞት ገባበት፡ተዳደፈ፡፡ ክፉ
ፍትወታት የሚያጠቁትና የሚያሸንፉት የዲያብሎስና የኃጢአት
ባርያ ሆነ፡፡ በማይለወጥ ፍቅር የወደደን እግዚአብሔር ግን
ጠፍተን እንድንቀር አልተወንም፡፡ በሰጠን ተስፋ፡በተቆጠረው
ሱባኤና በተነገረው ትንቢት መሰረት ዘመኑ ሲደርስ በተዋህዶ
ሰው ሆነ፤ የተዋረደ ሥጋችንን አከበረ፡፡ በከበረ ደሙ
ዋጀን፤ከኃጢአታችን አጠበን፡፡ በእርሱ ምክንያት
የእግዚአብሔር
ልጆች ተባልን ፡፡ጌታችንና መድኃኒታችን ሰው የሆነውና
ለመዳናችን የሆነውን ዋጋ ሁሉ የከፈለው ለእኛ ያለውን
ፍቅርና
ለኃጢአት ያለውን ጥላቻ ለእኛ ለማሳየት ነው፡፡ ‹‹ ነገር ግን
የኃጢአትን ሥራ ይሽር ዘንድ ከእርሱ ጋር የተሰቀለውን
አሮጌውን ሰውነታችን እንደሆነ ይህን እናውቃለን ››
የተባለውም
ለዚህ ነው፡፡ (ሮሜ 6፡6) እኛን ወደ ቀደመ ክብራችን
ለመመለስ የተከፈለውም ዋጋ ታላቅ ከሆነው የጋብቻ
ምስጢር
ጋር በማያያዝ እንዲህ ገልፆታል ‹‹ ክርስቶስ አካሉ ለሆነችው
ቤተ ክርሰቲያን ራስዋ አዳኝዋም እንደሆነ ወንድ ለሴት ራስዋ
ነውና … ወንዶችም ክርስቶስ ቤተ ክርስቲያንን እንደወደዳት
ራሱንም ስለእርስዋ ቤዛ አድርጎ እንደሰጠላት ሚስቶቻቸውን
ይውደዱ፡፡ በውኃ ጥምቀትና በቃሉ ይቀድሳትና ያነጻት ዘንድ
የነጻችና የተቀደሰች ትሆን ዘንድ እንጂ በላይዋ እድፈት ወይም
ርኩሰት እንዳይገኝባት ቤተ ክስቲያኑን ለእርሱ የከበረች
ያደርጋት ዘንድ…›› ኤፌ 5፡23-28
ስለዚህ ጌታችን በደሙ ኃጢአታችንን እንደ ቸርነቱ ይቅር
ብሎናል፡፡ኤፌ 1፡7 ከእንግዲህ የራሳችን አይደለንም ፡፡
በሰውነታችንም ኃጢአትና ዐመፃን ልናደርግበት አይገባም
፡፡‹‹በዚህ በሚሞት ሥጋችሁ ኃጢአት አታንግሷት፤ለምኞቱ
እሺ
አትበሉት፡፡ ከሙታን ተለይቶ እንደተነሳ ራሳችሁን
ለእግዚአብሔር
መሥዋዕት አድርጉ እንጂ ሰውነታችሁን ለኃጢአት የዐመፅ
የጦር መሣሪያ አታድርጉት፤ ሰውነታችሁንም ለእግዚአብሔር
የጽድቅ የጦር መሣሪያ አድርጉ››ተብለናል፡፡ (ሮሜ6፡
12-13)
የተወደዳችሁ ምዕመናን እግዚአብሔር ደስ ብሎት
የሚቀበለውን ህይወት ለመኖር አንፈልጋለን ፡፡ ለመሆኑ ይህ
ሊሆን የሚችለው እንዴት ብንመላለስ ነው? መልሱን
ሐዋርያው
ቅዱስ ያዕቆብ ‹‹አንደበቱን ሳይገታ ልቡን እያሳተ
እግዚአብሔርን የሚያመልክ የሚመስለው ማንም ቢኖር
የእርሱ
አምልኮቱ ከንቱ ነው፡፡ ንጹሕ የሆነ ነውርም የሌለበት
አምልኮ
በእግዚአብሔር አብ ዘንድ ይህ ነው፤ወላጆች የሌሉአቸውን
ልጆች ባልቴቶችንም በችግራቸው መጠየቅ በዓለምም
ከሚገኝ
ርኩሰት ሰውነትን መጠበቅ ነው፡፡››በማለት ይመልስልናል
( ያዕ
1፡26-27)፡፡ በክርስቶስ ደም የተቀደሰና የእግዚአብሔር
ማደሪያ የሆነውን ሰውነታችንን በዓለም ከሚገኝ ርኩሰት
መጠበቅ የሰማያዊ ርስት ወራሾች ያደርገናል፡፡ በዓለም
የሚገኘውን ርኩሰትም ሐዋርያው ቅዱስ ጳውሎስ ‹‹የሥጋ
ሥራ
›› በማለት ገልጾታል፡፡‹‹እርሱም ዝሙት
፣ርኩሰት፣መዳራት፣ጣዖት ማምለክ፣ሥራይ ማድረግ፣መጣላት፣
ኩራት፣የምንዝር ጌጥ ፣ቅናት፣ቁጣ ፣ጥርጥር፣ፉክክር፣
ምቀኝነት፣ መጋደል፣ ስካር ፣ይህንም የመሰለ ሁሉ
ነው፡፡››እነዚህን የሚያደርጉ ሰዎችም ከመንግስተ
እግዚአብሔር
በአፍአ ወይም በውጭ እንደሚቀሩ ሲያስረዳ‹‹አስቀድሜ
እንደነገርኋችሁ ይህን የሚያደርግ የእግዚአብሔርን መንግስት
አያይም›› ብሏል ( ገላ5፡19)።
በሕይወታችን ሁሉ የምግባርና የሃይማኖት ፍሬ አፍርተን
መገኘት ለቅድስና የጠራንን እግዚአብሔርን ደስ ማሰኘት
ነው፡፡
እነዚህንም ነገሮች ቅዱስ ጳውሎስ ‹‹የመንፈስ ፍሬዎች ››
ብሏቸዋል፡፡ እነርሱም ‹‹ፍቅር፣ደስታ
፣ሰላም፣ትዕግስት፣ምጽዋት ፣ቸርነት ፣እምነት ፣ገርነት ንጽሕና
››ናቸው፡፡ገላ 5፡22 እግዚአብሔር ማደርያው ይሆን ዘንድ
የመረጠውን ሰውነታችንን እርሱ የሚከብርበትን ሥራ
ልናደርግበት ያስፈልጋል፡፡ ‹‹በሕይወት የሚኖሩትም ስለ
እነርሱ
ቤዛ ሆኖ ለሞተውና ለተነሣውም እንጂ ወደ ፊት ለራሳቸው
የሚኖሩ እንዳይሆኑ እርሱ ስለሁሉ ቤዛ ሆኖ ሞተ›› እንደተባለ
በሕይወታችን ሁሉ ፋቃዱን በመመርመርና በመፈጸም
በቅድስና
ልንኖር ይገባናል፡፡2ቆሮ 5፡15
ቅድስናችን በኑሮአችን ሁሉ እንዲሆን ታዘናል (1ጴጥ1፡15)
፡፡
ስለዚህ በተሰማራንበት የሥራ መስክ ፣በማኅበራዊ ኑራአችን
፣በምንበላው ምግብ ፣በምንለብሰው ልብስ ፣በንግግራችንና
በመሳሰለው ሁሉ ለእግዚአብሔር ደስ የሚያሰኘውን
በማድረግ
እግዚአብሔርን በሚሞት ሥጋችን እናክብረው፡፡ ‹‹እኛ ደግሞ
ሸክምን ሁሉ የኃጢአትንም ጭንቀት ከእኛ አስወግደን
በፊታችን
ያለውን ሩጫ በትዕግስት እንሩጥ፡፡ የእምነታችንንም ራስና
ፈጻሚውን ኢየሱስን እንከተለው፤ እርሱ ነውርን ንቆ ፣
በፊቱም
ስላለው ደስታ በመስቀል ታግሦ በእግዚአብሔር ዙፋን ቀኝ
ተቀምጧል ›› ተብሎ እንደተጻፈ ደምን እስከ ማፍሰስ ድረስ
ተጋድሎ አድርገን ከኃጢአት ርቀት በቅድስና እንድንኖር
ይገባናል(ዕብ 12፡1)። ሥጋዊ ምኞታችንንና መሻታችንን
ሰቅለን አሮጌው ሰዋችንን አስወግደን ንስሐ ገብተን ቅዱስ
ሥጋውንና ክቡር ደሙን ተቀብለን በቅድስና እንድናኖር
ረድኤተ
እግዚአብሔር አይለየን፡፡
ወስብሐት ለእግዚአብሔር
«ቅድስት» ማለት የዘይቤ ፍችው « የተቀደሰች የተለየች »
ማለት ነው፡፡ ምስጢራዊ መልእክቱ ግን የምስጢረ አድኅኖት
ታላላቅ ሥራውን ለመጀመር መድኀኒታችን ኢየሱስ ክርስቶሰ
በገዳመ ቆሮንቶስ ገብቶ ከቆመ ሳያርፍ፣ ከዘረጋ ሳያጥፍ
የጾማት የአርብዓው ቀንና ሌሊት ልዩ የሆነችና ክብርት ጾም
የምትጀመርበትን ሁለተኛ ሳምንት ከልብ ያሳስበናል፡፡ ማቴ.
4-2
ቅድሰት የዐቢይ ጾም ሁለተኛ ሰንበት ስያሜ ነው፡፡
ስያሜውም
ከኢትዮያዊው የዜማ ሊቅ ከቅዱስ ያሬድ የተገኘ ነው፡፡ ከዚህ
ሰንበት ዋዜማ ጀምሮ ስለ ዕለተ ሰንበት ቅድስና ይዘመራል፡፡
ቅድስት ቤተ ክርስቲያናችንም ሰንበቱን ስለ ቅድስና ልጆቿን
ታስተምርበታለች ፡፡ በቅዳሴ ጊዜ የሚሰበከው ምስባክ ፤
የሚነበቡ መልዕክታት ፤የሐዋርያት ሥራ ና ወንጌል ስለ
ቅድስት
የሚያስተምሩ ናቸው፡፡
‹‹ቅዱስ›› ማለት ልዩ፤ክቡር ማለት ነው፡፡ እግዚአብሔር
አምላካችን በባሕርዩ ቅዱስ ነው፡፡ ይህም ቅድስና ከማንም
ያላገኘው የባሕርይ ገንዘቡ ነው፡፡ መጻሕፍትም የባሕርይ
ቅድስናውን ተባብረው መስክረዋል፡፡ ባባሕርዩ ቅዱስ ስለሆነ
‹‹ቅዱስ፡ቅዱስ፡ቅዱስ›› እየተባለ ይመሰገናል፡፡( ኢሳ 6፡
1-3፤40፡25 ራዕ 15፡4 ፤ 1ሳሙ2፡2-3፡፡) እኛም ቅዱስ
ልጁ
በሥጋ ተገልጦ እንዳስተማረን በየዕለት ጸሎታችን ‹‹ስምህ
ይቀደስ›› እንለዋለን፡፡ የቅድስና ምንጭ ፡ ቅድስናን የሚሰጥ
እርሱ ብቻ ነው፡፡ ‹‹ ቅዱስ›› የሚለው ቃል ለሰዎች ፡
ለመላእክት ፡ ለቦታ ፡ለዕቃ፡ ለዕለታት … ቢቀጸልም
ቅድስናቸው
በባሕርይው ቅዱስ ከሆነው ከእግዚአብሔር የተገኘ ነው፡፡
ይህም
የጸጋ ቅድስና ይባላል፡፡
እግዚአብሔር ቅዱስ ስለሆነ በመልኩና በምሳሌው አክብሮ
የፈጠረንን እኛም ቅዱሳን እንድንሆን ይፈለጋል፡፡ቅዱስ
ጴጥሮስ
‹‹ዳሩ ግን እኔ ቅዱስ ነኝና ቅዱሳን ሁን›› ተብሎ ስለተጻፈ
የጠራቸው ቅዱስ እንደሆነ እናንተ ደግሞ በኑሮአችሁ ሁሉ
ቅዱሳን ሁኑ ›› ያለንም ይህንን ሲያስተምረን ነው፡፡
ከመፈጠራችን አስቀድሞ መጠን በሌለው ፍቅር የወደደን
እግዚአብሔር ካለመኖር ወደ መኖር ያመጣን ፤ለውርደት
ሳይሆን ለክብር፤ለርኩሰት ሳይሆን ለቅድስና፤ለሞት ሳይሆን
ለሕይወት ነው፡፡የመፈጠራችንም ዓላማ በፊቱ በፍጹም
ምግባርና ሃማኖት በመመላለስ ከእርሱ ጋር እንድንኖር ነው፡፡
ብርሃን ከጨለማ፡ ጽድቅ ከኃጢአት፡ጋር ኅብረት የለውምና
ከእርሱ ጋር ለዘላለም ነግሰን ለመኖር በቅድስና መኖር
ይጠበቅብናል፡፡ ቅዱስ ጳውሎስም ‹‹ እግዚአብሔር ለቅድስና
እንጂ ለርኩሰት አልጠራንምና ›› ያለንም ለዚህ ነው፡፡/1ተሰ
4*7/ እግዚአብሔር እኛን የፈጠረበትን አላማ ለኤፌሶን
ክርስቲያኖች እንዲህ ገልጾላቸዋል ‹‹ በክርስቶስ ኢየሱስ
ሰማያዊ ሥፍራ በመንፈሳዊ በረከት ሁሉ የባረከን የጌታችን
የኢየሱስ ክርስቶስ አባት እግዚአብሔር ይመስገን፡፡ ብሎ
ካመሰገነ በኋላ ‹‹ ዓለም ሳይፈጠር በፊቱ ቅዱሳን ፡ንጹሐንና
ያለነውር በፍቅር ያደርገን ዘንድ ለእርሱ መረጠን›› ኤፌ 1፡
3-4
አስቀድሞ ስለወደደንና ስላከበረንም ከሌሎች ፍጥረታት
በተለየ
መልኩ የሚያስፈልገንን ሁሉ አዘጋጅቶ በእጆቹ ካበጀን በኋላ
የሥነ ፍጥረት ዘውድ አድርጎ በገነት አኖረን ፡፡( ዘፍ 1፡26
፤መዝ 8፡1)
የቀደመው አዳም አታድርግ የተባለውን በማድረጉ
በንዝህላልነትና በስንፍና በከይሲ ዲያብሎስም ምክር
ተዋረደ፡፡
በሞተ ሥጋ ላይም ሞተ ነፍስ ፤በርዕደተ መቃብር ላይ ርዕደተ
ሲኦል ተፈረደበት፡ በባሕርዩ ሞት ገባበት፡ተዳደፈ፡፡ ክፉ
ፍትወታት የሚያጠቁትና የሚያሸንፉት የዲያብሎስና የኃጢአት
ባርያ ሆነ፡፡ በማይለወጥ ፍቅር የወደደን እግዚአብሔር ግን
ጠፍተን እንድንቀር አልተወንም፡፡ በሰጠን ተስፋ፡በተቆጠረው
ሱባኤና በተነገረው ትንቢት መሰረት ዘመኑ ሲደርስ በተዋህዶ
ሰው ሆነ፤ የተዋረደ ሥጋችንን አከበረ፡፡ በከበረ ደሙ
ዋጀን፤ከኃጢአታችን አጠበን፡፡ በእርሱ ምክንያት
የእግዚአብሔር
ልጆች ተባልን ፡፡ጌታችንና መድኃኒታችን ሰው የሆነውና
ለመዳናችን የሆነውን ዋጋ ሁሉ የከፈለው ለእኛ ያለውን
ፍቅርና
ለኃጢአት ያለውን ጥላቻ ለእኛ ለማሳየት ነው፡፡ ‹‹ ነገር ግን
የኃጢአትን ሥራ ይሽር ዘንድ ከእርሱ ጋር የተሰቀለውን
አሮጌውን ሰውነታችን እንደሆነ ይህን እናውቃለን ››
የተባለውም
ለዚህ ነው፡፡ (ሮሜ 6፡6) እኛን ወደ ቀደመ ክብራችን
ለመመለስ የተከፈለውም ዋጋ ታላቅ ከሆነው የጋብቻ
ምስጢር
ጋር በማያያዝ እንዲህ ገልፆታል ‹‹ ክርስቶስ አካሉ ለሆነችው
ቤተ ክርሰቲያን ራስዋ አዳኝዋም እንደሆነ ወንድ ለሴት ራስዋ
ነውና … ወንዶችም ክርስቶስ ቤተ ክርስቲያንን እንደወደዳት
ራሱንም ስለእርስዋ ቤዛ አድርጎ እንደሰጠላት ሚስቶቻቸውን
ይውደዱ፡፡ በውኃ ጥምቀትና በቃሉ ይቀድሳትና ያነጻት ዘንድ
የነጻችና የተቀደሰች ትሆን ዘንድ እንጂ በላይዋ እድፈት ወይም
ርኩሰት እንዳይገኝባት ቤተ ክስቲያኑን ለእርሱ የከበረች
ያደርጋት ዘንድ…›› ኤፌ 5፡23-28
ስለዚህ ጌታችን በደሙ ኃጢአታችንን እንደ ቸርነቱ ይቅር
ብሎናል፡፡ኤፌ 1፡7 ከእንግዲህ የራሳችን አይደለንም ፡፡
በሰውነታችንም ኃጢአትና ዐመፃን ልናደርግበት አይገባም
፡፡‹‹በዚህ በሚሞት ሥጋችሁ ኃጢአት አታንግሷት፤ለምኞቱ
እሺ
አትበሉት፡፡ ከሙታን ተለይቶ እንደተነሳ ራሳችሁን
ለእግዚአብሔር
መሥዋዕት አድርጉ እንጂ ሰውነታችሁን ለኃጢአት የዐመፅ
የጦር መሣሪያ አታድርጉት፤ ሰውነታችሁንም ለእግዚአብሔር
የጽድቅ የጦር መሣሪያ አድርጉ››ተብለናል፡፡ (ሮሜ6፡
12-13)
የተወደዳችሁ ምዕመናን እግዚአብሔር ደስ ብሎት
የሚቀበለውን ህይወት ለመኖር አንፈልጋለን ፡፡ ለመሆኑ ይህ
ሊሆን የሚችለው እንዴት ብንመላለስ ነው? መልሱን
ሐዋርያው
ቅዱስ ያዕቆብ ‹‹አንደበቱን ሳይገታ ልቡን እያሳተ
እግዚአብሔርን የሚያመልክ የሚመስለው ማንም ቢኖር
የእርሱ
አምልኮቱ ከንቱ ነው፡፡ ንጹሕ የሆነ ነውርም የሌለበት
አምልኮ
በእግዚአብሔር አብ ዘንድ ይህ ነው፤ወላጆች የሌሉአቸውን
ልጆች ባልቴቶችንም በችግራቸው መጠየቅ በዓለምም
ከሚገኝ
ርኩሰት ሰውነትን መጠበቅ ነው፡፡››በማለት ይመልስልናል
( ያዕ
1፡26-27)፡፡ በክርስቶስ ደም የተቀደሰና የእግዚአብሔር
ማደሪያ የሆነውን ሰውነታችንን በዓለም ከሚገኝ ርኩሰት
መጠበቅ የሰማያዊ ርስት ወራሾች ያደርገናል፡፡ በዓለም
የሚገኘውን ርኩሰትም ሐዋርያው ቅዱስ ጳውሎስ ‹‹የሥጋ
ሥራ
›› በማለት ገልጾታል፡፡‹‹እርሱም ዝሙት
፣ርኩሰት፣መዳራት፣ጣዖት ማምለክ፣ሥራይ ማድረግ፣መጣላት፣
ኩራት፣የምንዝር ጌጥ ፣ቅናት፣ቁጣ ፣ጥርጥር፣ፉክክር፣
ምቀኝነት፣ መጋደል፣ ስካር ፣ይህንም የመሰለ ሁሉ
ነው፡፡››እነዚህን የሚያደርጉ ሰዎችም ከመንግስተ
እግዚአብሔር
በአፍአ ወይም በውጭ እንደሚቀሩ ሲያስረዳ‹‹አስቀድሜ
እንደነገርኋችሁ ይህን የሚያደርግ የእግዚአብሔርን መንግስት
አያይም›› ብሏል ( ገላ5፡19)።
በሕይወታችን ሁሉ የምግባርና የሃይማኖት ፍሬ አፍርተን
መገኘት ለቅድስና የጠራንን እግዚአብሔርን ደስ ማሰኘት
ነው፡፡
እነዚህንም ነገሮች ቅዱስ ጳውሎስ ‹‹የመንፈስ ፍሬዎች ››
ብሏቸዋል፡፡ እነርሱም ‹‹ፍቅር፣ደስታ
፣ሰላም፣ትዕግስት፣ምጽዋት ፣ቸርነት ፣እምነት ፣ገርነት ንጽሕና
››ናቸው፡፡ገላ 5፡22 እግዚአብሔር ማደርያው ይሆን ዘንድ
የመረጠውን ሰውነታችንን እርሱ የሚከብርበትን ሥራ
ልናደርግበት ያስፈልጋል፡፡ ‹‹በሕይወት የሚኖሩትም ስለ
እነርሱ
ቤዛ ሆኖ ለሞተውና ለተነሣውም እንጂ ወደ ፊት ለራሳቸው
የሚኖሩ እንዳይሆኑ እርሱ ስለሁሉ ቤዛ ሆኖ ሞተ›› እንደተባለ
በሕይወታችን ሁሉ ፋቃዱን በመመርመርና በመፈጸም
በቅድስና
ልንኖር ይገባናል፡፡2ቆሮ 5፡15
ቅድስናችን በኑሮአችን ሁሉ እንዲሆን ታዘናል (1ጴጥ1፡15)
፡፡
ስለዚህ በተሰማራንበት የሥራ መስክ ፣በማኅበራዊ ኑራአችን
፣በምንበላው ምግብ ፣በምንለብሰው ልብስ ፣በንግግራችንና
በመሳሰለው ሁሉ ለእግዚአብሔር ደስ የሚያሰኘውን
በማድረግ
እግዚአብሔርን በሚሞት ሥጋችን እናክብረው፡፡ ‹‹እኛ ደግሞ
ሸክምን ሁሉ የኃጢአትንም ጭንቀት ከእኛ አስወግደን
በፊታችን
ያለውን ሩጫ በትዕግስት እንሩጥ፡፡ የእምነታችንንም ራስና
ፈጻሚውን ኢየሱስን እንከተለው፤ እርሱ ነውርን ንቆ ፣
በፊቱም
ስላለው ደስታ በመስቀል ታግሦ በእግዚአብሔር ዙፋን ቀኝ
ተቀምጧል ›› ተብሎ እንደተጻፈ ደምን እስከ ማፍሰስ ድረስ
ተጋድሎ አድርገን ከኃጢአት ርቀት በቅድስና እንድንኖር
ይገባናል(ዕብ 12፡1)። ሥጋዊ ምኞታችንንና መሻታችንን
ሰቅለን አሮጌው ሰዋችንን አስወግደን ንስሐ ገብተን ቅዱስ
ሥጋውንና ክቡር ደሙን ተቀብለን በቅድስና እንድናኖር
ረድኤተ
እግዚአብሔር አይለየን፡፡
ወስብሐት ለእግዚአብሔር
Wednesday, February 22, 2017
ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ነኝ:=>+*"+<+>††7ቱ ኪዳናት+*"+<+>††
በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሃዱ አምላክ አሜን
እንኩዋን ለእመቤታችን ቅድስት #ድንግል_ማርያም
ዓመታዊ "የኪዳን በዓል" በሰላም አደረሳችሁ +"+"+
+*" 7ቱ ኪዳናት "*+
=>"ተካየደ" ማለት "ተስማማ : ተማማለ" እንደ ማለት
ሲሆን "ኪዳን" በቁሙ "ውል : ስምምነት" እንደ ማለት
ነው:: ይኸውም እግዚአብሔር ከሰዎች ጋር: ሰዎችም ከሰዎች
ጋር የሚያደርጉት ሊሆን ይችላል:: ልዩነቱ የእግዚአብሔር
ቃል ኪዳን ቅዱስና የማይለወጥ መሆኑ ነው::
+እግዚአብሔር አምላክ ከሥነ ፍጥረት ጀምሮ በየጊዜው
ከብዙ ወዳጆቹ ጋር ኪዳንን አድርጉዋል:: ቅድስት ቤተ
ክርስቲያንም እነዚህን ኪዳናት ጥቅልል አድርጋ 7 እንደ ሆኑ
ታስተምራለች:: ስለዚህም ዛሬ ፈጣሪ ቢረዳን እነዚሁን 7
ኪዳናት በጥቂቱ እንመለከታለን::
"ኪዳነ ተካየድኩ ምስለ ኅሩያንየ"
"ከመረጥኩዋቸው ጋር ቃል ኪዳንን አደረግሁ" (መዝ. 88:3)
1. +*" ኪዳነ አዳም "*+
=>አዳም ማለት የእግዚአብሔር ድንቅ ፍጥረት: የፍጡራን
አስተዳዳሪ: ነቢይ: ካህንና ንጉሥ ነው:: እግዚአብሔር ከአዳም
ጋር አስቀድሞ በእጸ በለስ አማካኝነት ቃል ኪዳን ነበራቸው::
ነገር ግን አባታችን በዲያብሎስ ሴራ በመረታቱ ኪዳኑ ፈረሰ::
(ዘፍ. 3:1)
+አዳምና ሔዋን ተጸጽተው ቢያለቅሱ ግን አዲስ የኪዳን
ተስፋ: "ከልጅ ልጅህ ተወልጄ አድንሃለሁ" የሚል ኪዳንን
ተቀበሉ:: (ቀሌምንጦስ: ገላ. 4:4)
2. +*" ኪዳነ ኖኅ "*+
=>ከአዳም እስከ ኖኅ ድረስ ባሉት 10 ትውልድ ዓለም
በዓመፃ ተሞላች:: ቅዱስ ኖኅ በደግነቱ መርከብ ሠርቶ
ቤተሰቡን ሲያተርፍ ዓለም በማየ ሥራዌ ጠፋች:: ከመርከቡ
ከወጣ በሁዋላ ኖኅና እግዚአብሔር በቀስተ ደመና ምልክትነት
ቃል ኪዳን ተጋቡ:: "ኢያማስና ለምድር ዳግመ በማየ አይኅ"
እንዲል:: (ዘፍ. 9:12)
3. +*" ኪዳነ መልከ ጼዴቅ "*+
=>መልከ ጼዴቅ የእግዚአብሔር ካህኑ: የክርስቶስም
ምሳሌው የሆነ የሳሌም ንጉሥ ነው:: በ15 ዓመቱ መንኖ:
አጽመ አዳምን ይዞ: በቀራንዮ በሕብስትና በወይን ያስታኩት
ነበር::
+እግዚአብሔር ለመልከ ጼዴቅ: በሐዲስ ኪዳን ለምትሠራው
ክህነትና ምሥጢረ ቁርባን ምሳሌ አድርጐ በቃል ኪዳን
አትሞታል:: በዚህም ተሰውሮ ይኖራል እንጂ ሞትን እስካሁን
አልቀመሰም:: ይህም ካህኑ መልከ ጼዴቅ ከአብርሃም ጋር
በተገናኙበት ጊዜ ተገልጧል:: (ዘፍ. 14:17, ዕብ. 7:1)
4. +*" ኪዳነ አብርሃም "*+
=>ቅዱስ አብርሃም የሕዝብና የአሕዛብ አባት: ሥርወ
ሃይማኖት: የጽድቅም አበጋዝ ነው:: ስለ ፍቅረ እግዚአብሔር
ሲል ከርስቱና ከወገኖቹ ተለይቶ በቅድስና ኑሯልና
እግዚአብሔር "በዘርሕ አሕዛብ ይባረካሉ" አለው:: (ዘፍ.
12:1) የቃል ኪዳን ምልክትም ይሆነው ዘንድ ግዝረትን
ሰጠው:: (ዘፍ. 17:1-14)
5. +*" ኪዳነ ሙሴ "*+
=>ቅዱስ ሙሴ የነቢያት አለቃ: የእሥራኤል እረኛ:
የእግዚአብሔር ሰው እና ፍጹም ትሑት (የዋህ) ሰው ነው::
በፈጣሪው ትዕዛዝ እሥራኤልን ከግብጽ ባርነት አውጥቶ ለ40
ዘመናት በበርሃ ሲመራቸው ከእግዚአብሔር የኪዳንን ጽላትና
አሠርቱን ትዕዛዛት ተቀብሏል:: (ዘጸ. 20:1, 31:18)
6. +*" ኪዳነ ዳዊት "*+
=>ቅዱስ ዳዊት ሥርወ ነገሥት: ጻድቅ: የዋህና ቡሩክ የሆነ
አባት ነው:: እግዚአብሔር ከእረኝነት ጠርቶ ንጉሥ አድርጐ
ሹሞት "ከሆድህ ፍሬ በዙፋንህ ላይ አኖራለሁ" (መዝ.
131:11) ሲል ምሎለታል:: አክሎም ሰፊ ቃል ኪዳን ሰጥቶ
"አልዋሽህም" ብሎ ሲምልለት እንመለከታለን:: (መዝ.
88:35)
7. +*"+ ኪዳነ ምሕረት +"*+
=>በብሉይ ኪዳን የነበሩ 6ቱ ኪዳናት በዘመናቸው ክቡርና
ሕዝቡን ከመቅሰፍት ይታደጉ የነበሩ ቢሆንም ከሲዖል ማዳን
ግን አልቻሉም:: ስለዚህም አንድ ፍጹም ኪዳን ያስፈልግ
ነበር:: ይህን ፍጹም ኪዳን ይፈጽም ዘንድም ከቅድስት ሥላሴ
አንዱ ወልድ ከሰማያት ወርዶ በድንግል ማርያም ማሕጸን
አደረ::
+በፍጹም ተዋሕዶም በሕቱም ድንግልና ተወልዶ: አድጎ:
ተጠምቆ: አስተምሮ: ሙቶ: ተነስቶና ዐርጐ ሥጋ ማርያምን
በዘባነ ኪሩብ አስቀመጠው:: ኪዳነ ምሕረት (የምሕረት
ኪዳን) የምንለው አንዱ ታዲያ ይሔው ነው::
+የጌታችን መጸነሱ: መወለዱ: መሰደዱ: መጠመቁ:
ማስተማሩ: ሥጋውንና ደሙን መስጠቱ: መሰቀሉ: መሞቱና
መነሳቱ: ማረጉና መንፈስ ቅዱስን መላኩ በአንድ ላይ "ኪዳነ
ምሕረት" ይባላል:: ታዲያ ይህ ሁሉ የተደረገው በሥጋ
ማርያም ነውና የኪዳኑ ባለቤት እመቤታችን ቅድስት ድንግል
ማርያም ናት::
+የእርሷ ኪዳን የ6ቱን አበው ኪዳናት ፍጹም በማድረጉ
የኪዳናት ማሕተም ይባላል:: የድንግል ማርያም ኪዳኗ
ከሲዖልና ከገሃነም ሊታደገን አቅሙ አለውና:: መድኃኒታችን
ክርስቶስ ለድንግል እናቱ ቃል ኪዳኑን ያጸናላት ደግሞ ካረገ
ከዓመታት በሁዋላ ጐልጐታ ላይ ነው::
+እመ ብርሃን በዚያ ቁማ ስለ ኃጥአን ስታለቅስ "እናቴ ሆይ!
በስምሽ ያመነውን: በቃል ኪዳንሽ የተማጸነውን
እምርልሻለሁ" ብሎ ደስ አሰኝቷታልና:: ይሔው በእመ ብርሃን
ምልጃና ቃል ኪዳን ምዕመናን ከመቅሰፍትና ከገሃነመ እሳት
ማምለጥ ከጀመሩ 2ሺ ዓመታት ሆኑ:: ዛሬም እኛ ኃጥአን
ልጆቿ ከእሳት እንደምታድነን አምነን በጥላዋ ሥር
እንኖራለን::
+*" ኢትዝክሪ ብነ አበሳነ (ኃጢአተነ : ወጌጋየነ)
ማርያም እሙ ለእግዚእነ:
በኪዳንኪ: ወበስደትኪ ድንግል ተማሕጸነ:: "*+
"ድንግል ሆይ! ኃጢአታችን: አበሳችንና በደላችንን አታስቢብን
ዘንድ በስደትሽና በኪዳንሽ ተማጽነናል::"
=>የአርያም ንግሥት: የሰማያውያንና ምድራውያን ኁሉ
እመቤት: የአምላክ እናት: ቅድስት: ስብሕት: ክብርት:
ልዕልት: ቡርክት: ፍስሕትና ጥዕምት የሆነች ድንግል ማርያም
የድኅነታችን መሠረት: ላመኑባት አንገት የማታስደፋ እውነተኛ
አማላጅ ናት::
+በዚህች ዕለት የካቲት 16 ስለ ወገኖቿ የሰው ልጆች ፍቅር
በእንባ ያቀረበችውን ልመና የባሕርይ አምላክ የሆነ ልጁዋ
ተቀብሎ በማይዋሽ ንጹሕ አንደበቱ ቃል ኪዳን ገብቶላታል::
በስምሽ ያመነ በቃል ኪዳንሽ የተማመነ እሳትን አያይም
ብሏታል::
=>ቸሩ ልጇ ከበረከተ ኪዳኗ አይለየን:: በዓሉንም የሰላም :
የፍቅርና የበረከት ያድርግልን::
=>የካቲት 16 ቀን የሚከበሩ ዓመታዊ የቅዱሳን በዓላት=
1.ኪዳነ ምሕረት (የሰባቱ ኪዳናት ማሕተም)
2.ቅድስት ኤልሳቤጥ (የመጥምቁ ዮሐንስ እናት /
የእመቤታችን አክስት / የሶፍያ ልጅ)
3.ቅዱስ ገብረ ማርያም ጻድቅ ንጉሠ ኢትዮዽያ (የቅ/ላሊበላ
ወንድም)
=>ወርኀዊ በዓላት
1.ቅዱስ አኖሬዎስ ንጉሥ ጻድቅ
2.አባ አቡናፍር ገዳማዊ
3.አባ ዮሐንስ ወንጌሉ ዘወርቅ
4.አባ ዳንኤል ጻድቅ
=>+"+"+ . . . ኤልሳቤጥም የማርያምን ሰላምታ በሰማች
ጊዜ ፅንሱ በማኅፀንዋ ውስጥ ዘለለ:: በኤልሳቤጥም መንፈስ
ቅዱስ ሞላባት:: በታላቅ ድምፅም ጮኻ እንዲህ አለች:-
አንቺ ከሴቶች መካከል የተባረክሽ ነሽ: የማኅፀንሽም ፍሬ
የተባረከ ነው:: የጌታዬ እናት ወደ እኔ ትመጣ ዘንድ እንዴት
ይሆንልኛል? እነሆ የሰላምታሽ ድምፅ በጀሮየ በመጣ ጊዜ
ፅንሱ በማኅፀኔ በደስታ ዘሎአልና:: ከጌታ የተነገረላት ቃል
ይፈፀማልና ያመነች ብፅዕት ናት:: +"+"+ (ሉቃ. 1:39)
<ወስብሐት ለእግዚአብሔር>
እንኩዋን ለእመቤታችን ቅድስት #ድንግል_ማርያም
ዓመታዊ "የኪዳን በዓል" በሰላም አደረሳችሁ +"+"+
+*" 7ቱ ኪዳናት "*+
=>"ተካየደ" ማለት "ተስማማ : ተማማለ" እንደ ማለት
ሲሆን "ኪዳን" በቁሙ "ውል : ስምምነት" እንደ ማለት
ነው:: ይኸውም እግዚአብሔር ከሰዎች ጋር: ሰዎችም ከሰዎች
ጋር የሚያደርጉት ሊሆን ይችላል:: ልዩነቱ የእግዚአብሔር
ቃል ኪዳን ቅዱስና የማይለወጥ መሆኑ ነው::
+እግዚአብሔር አምላክ ከሥነ ፍጥረት ጀምሮ በየጊዜው
ከብዙ ወዳጆቹ ጋር ኪዳንን አድርጉዋል:: ቅድስት ቤተ
ክርስቲያንም እነዚህን ኪዳናት ጥቅልል አድርጋ 7 እንደ ሆኑ
ታስተምራለች:: ስለዚህም ዛሬ ፈጣሪ ቢረዳን እነዚሁን 7
ኪዳናት በጥቂቱ እንመለከታለን::
"ኪዳነ ተካየድኩ ምስለ ኅሩያንየ"
"ከመረጥኩዋቸው ጋር ቃል ኪዳንን አደረግሁ" (መዝ. 88:3)
1. +*" ኪዳነ አዳም "*+
=>አዳም ማለት የእግዚአብሔር ድንቅ ፍጥረት: የፍጡራን
አስተዳዳሪ: ነቢይ: ካህንና ንጉሥ ነው:: እግዚአብሔር ከአዳም
ጋር አስቀድሞ በእጸ በለስ አማካኝነት ቃል ኪዳን ነበራቸው::
ነገር ግን አባታችን በዲያብሎስ ሴራ በመረታቱ ኪዳኑ ፈረሰ::
(ዘፍ. 3:1)
+አዳምና ሔዋን ተጸጽተው ቢያለቅሱ ግን አዲስ የኪዳን
ተስፋ: "ከልጅ ልጅህ ተወልጄ አድንሃለሁ" የሚል ኪዳንን
ተቀበሉ:: (ቀሌምንጦስ: ገላ. 4:4)
2. +*" ኪዳነ ኖኅ "*+
=>ከአዳም እስከ ኖኅ ድረስ ባሉት 10 ትውልድ ዓለም
በዓመፃ ተሞላች:: ቅዱስ ኖኅ በደግነቱ መርከብ ሠርቶ
ቤተሰቡን ሲያተርፍ ዓለም በማየ ሥራዌ ጠፋች:: ከመርከቡ
ከወጣ በሁዋላ ኖኅና እግዚአብሔር በቀስተ ደመና ምልክትነት
ቃል ኪዳን ተጋቡ:: "ኢያማስና ለምድር ዳግመ በማየ አይኅ"
እንዲል:: (ዘፍ. 9:12)
3. +*" ኪዳነ መልከ ጼዴቅ "*+
=>መልከ ጼዴቅ የእግዚአብሔር ካህኑ: የክርስቶስም
ምሳሌው የሆነ የሳሌም ንጉሥ ነው:: በ15 ዓመቱ መንኖ:
አጽመ አዳምን ይዞ: በቀራንዮ በሕብስትና በወይን ያስታኩት
ነበር::
+እግዚአብሔር ለመልከ ጼዴቅ: በሐዲስ ኪዳን ለምትሠራው
ክህነትና ምሥጢረ ቁርባን ምሳሌ አድርጐ በቃል ኪዳን
አትሞታል:: በዚህም ተሰውሮ ይኖራል እንጂ ሞትን እስካሁን
አልቀመሰም:: ይህም ካህኑ መልከ ጼዴቅ ከአብርሃም ጋር
በተገናኙበት ጊዜ ተገልጧል:: (ዘፍ. 14:17, ዕብ. 7:1)
4. +*" ኪዳነ አብርሃም "*+
=>ቅዱስ አብርሃም የሕዝብና የአሕዛብ አባት: ሥርወ
ሃይማኖት: የጽድቅም አበጋዝ ነው:: ስለ ፍቅረ እግዚአብሔር
ሲል ከርስቱና ከወገኖቹ ተለይቶ በቅድስና ኑሯልና
እግዚአብሔር "በዘርሕ አሕዛብ ይባረካሉ" አለው:: (ዘፍ.
12:1) የቃል ኪዳን ምልክትም ይሆነው ዘንድ ግዝረትን
ሰጠው:: (ዘፍ. 17:1-14)
5. +*" ኪዳነ ሙሴ "*+
=>ቅዱስ ሙሴ የነቢያት አለቃ: የእሥራኤል እረኛ:
የእግዚአብሔር ሰው እና ፍጹም ትሑት (የዋህ) ሰው ነው::
በፈጣሪው ትዕዛዝ እሥራኤልን ከግብጽ ባርነት አውጥቶ ለ40
ዘመናት በበርሃ ሲመራቸው ከእግዚአብሔር የኪዳንን ጽላትና
አሠርቱን ትዕዛዛት ተቀብሏል:: (ዘጸ. 20:1, 31:18)
6. +*" ኪዳነ ዳዊት "*+
=>ቅዱስ ዳዊት ሥርወ ነገሥት: ጻድቅ: የዋህና ቡሩክ የሆነ
አባት ነው:: እግዚአብሔር ከእረኝነት ጠርቶ ንጉሥ አድርጐ
ሹሞት "ከሆድህ ፍሬ በዙፋንህ ላይ አኖራለሁ" (መዝ.
131:11) ሲል ምሎለታል:: አክሎም ሰፊ ቃል ኪዳን ሰጥቶ
"አልዋሽህም" ብሎ ሲምልለት እንመለከታለን:: (መዝ.
88:35)
7. +*"+ ኪዳነ ምሕረት +"*+
=>በብሉይ ኪዳን የነበሩ 6ቱ ኪዳናት በዘመናቸው ክቡርና
ሕዝቡን ከመቅሰፍት ይታደጉ የነበሩ ቢሆንም ከሲዖል ማዳን
ግን አልቻሉም:: ስለዚህም አንድ ፍጹም ኪዳን ያስፈልግ
ነበር:: ይህን ፍጹም ኪዳን ይፈጽም ዘንድም ከቅድስት ሥላሴ
አንዱ ወልድ ከሰማያት ወርዶ በድንግል ማርያም ማሕጸን
አደረ::
+በፍጹም ተዋሕዶም በሕቱም ድንግልና ተወልዶ: አድጎ:
ተጠምቆ: አስተምሮ: ሙቶ: ተነስቶና ዐርጐ ሥጋ ማርያምን
በዘባነ ኪሩብ አስቀመጠው:: ኪዳነ ምሕረት (የምሕረት
ኪዳን) የምንለው አንዱ ታዲያ ይሔው ነው::
+የጌታችን መጸነሱ: መወለዱ: መሰደዱ: መጠመቁ:
ማስተማሩ: ሥጋውንና ደሙን መስጠቱ: መሰቀሉ: መሞቱና
መነሳቱ: ማረጉና መንፈስ ቅዱስን መላኩ በአንድ ላይ "ኪዳነ
ምሕረት" ይባላል:: ታዲያ ይህ ሁሉ የተደረገው በሥጋ
ማርያም ነውና የኪዳኑ ባለቤት እመቤታችን ቅድስት ድንግል
ማርያም ናት::
+የእርሷ ኪዳን የ6ቱን አበው ኪዳናት ፍጹም በማድረጉ
የኪዳናት ማሕተም ይባላል:: የድንግል ማርያም ኪዳኗ
ከሲዖልና ከገሃነም ሊታደገን አቅሙ አለውና:: መድኃኒታችን
ክርስቶስ ለድንግል እናቱ ቃል ኪዳኑን ያጸናላት ደግሞ ካረገ
ከዓመታት በሁዋላ ጐልጐታ ላይ ነው::
+እመ ብርሃን በዚያ ቁማ ስለ ኃጥአን ስታለቅስ "እናቴ ሆይ!
በስምሽ ያመነውን: በቃል ኪዳንሽ የተማጸነውን
እምርልሻለሁ" ብሎ ደስ አሰኝቷታልና:: ይሔው በእመ ብርሃን
ምልጃና ቃል ኪዳን ምዕመናን ከመቅሰፍትና ከገሃነመ እሳት
ማምለጥ ከጀመሩ 2ሺ ዓመታት ሆኑ:: ዛሬም እኛ ኃጥአን
ልጆቿ ከእሳት እንደምታድነን አምነን በጥላዋ ሥር
እንኖራለን::
+*" ኢትዝክሪ ብነ አበሳነ (ኃጢአተነ : ወጌጋየነ)
ማርያም እሙ ለእግዚእነ:
በኪዳንኪ: ወበስደትኪ ድንግል ተማሕጸነ:: "*+
"ድንግል ሆይ! ኃጢአታችን: አበሳችንና በደላችንን አታስቢብን
ዘንድ በስደትሽና በኪዳንሽ ተማጽነናል::"
=>የአርያም ንግሥት: የሰማያውያንና ምድራውያን ኁሉ
እመቤት: የአምላክ እናት: ቅድስት: ስብሕት: ክብርት:
ልዕልት: ቡርክት: ፍስሕትና ጥዕምት የሆነች ድንግል ማርያም
የድኅነታችን መሠረት: ላመኑባት አንገት የማታስደፋ እውነተኛ
አማላጅ ናት::
+በዚህች ዕለት የካቲት 16 ስለ ወገኖቿ የሰው ልጆች ፍቅር
በእንባ ያቀረበችውን ልመና የባሕርይ አምላክ የሆነ ልጁዋ
ተቀብሎ በማይዋሽ ንጹሕ አንደበቱ ቃል ኪዳን ገብቶላታል::
በስምሽ ያመነ በቃል ኪዳንሽ የተማመነ እሳትን አያይም
ብሏታል::
=>ቸሩ ልጇ ከበረከተ ኪዳኗ አይለየን:: በዓሉንም የሰላም :
የፍቅርና የበረከት ያድርግልን::
=>የካቲት 16 ቀን የሚከበሩ ዓመታዊ የቅዱሳን በዓላት=
1.ኪዳነ ምሕረት (የሰባቱ ኪዳናት ማሕተም)
2.ቅድስት ኤልሳቤጥ (የመጥምቁ ዮሐንስ እናት /
የእመቤታችን አክስት / የሶፍያ ልጅ)
3.ቅዱስ ገብረ ማርያም ጻድቅ ንጉሠ ኢትዮዽያ (የቅ/ላሊበላ
ወንድም)
=>ወርኀዊ በዓላት
1.ቅዱስ አኖሬዎስ ንጉሥ ጻድቅ
2.አባ አቡናፍር ገዳማዊ
3.አባ ዮሐንስ ወንጌሉ ዘወርቅ
4.አባ ዳንኤል ጻድቅ
=>+"+"+ . . . ኤልሳቤጥም የማርያምን ሰላምታ በሰማች
ጊዜ ፅንሱ በማኅፀንዋ ውስጥ ዘለለ:: በኤልሳቤጥም መንፈስ
ቅዱስ ሞላባት:: በታላቅ ድምፅም ጮኻ እንዲህ አለች:-
አንቺ ከሴቶች መካከል የተባረክሽ ነሽ: የማኅፀንሽም ፍሬ
የተባረከ ነው:: የጌታዬ እናት ወደ እኔ ትመጣ ዘንድ እንዴት
ይሆንልኛል? እነሆ የሰላምታሽ ድምፅ በጀሮየ በመጣ ጊዜ
ፅንሱ በማኅፀኔ በደስታ ዘሎአልና:: ከጌታ የተነገረላት ቃል
ይፈፀማልና ያመነች ብፅዕት ናት:: +"+"+ (ሉቃ. 1:39)
<ወስብሐት ለእግዚአብሔር>
ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ነኝ:=>+*"+<+>†† የእመ ቤታችን የቅድስት ኪዳነ ምህረት የንግስ በዓል ††
""የእመ ቤታችን የቅድስት ኪዳነ ምህረት የንግስ
በዓል"!!!
ኪዳነ ምህረት ማለት የምህረት መሐላ ማለት ነው፡፡
ከ" 33"በዓላተ እግዝእትነ ድንግል ማርያም አንዱ ነው፡፡
እመቤታችንም ከጌታችን መቃብር እየሄደች በምትለምንበት
ጊዜ አይሁድ ለምቀኝነት አያርፉምና ምን ልታመጣብን ነው
በማለት ሊጣሏት ሲመጡ ጌታችንም ከዓይናቸው ሰውሯታል
አይሁድም ጠባቂ ቢያቆሙ እመቤታችን ዕለት ዕለት መሄዷን
አላቋረጠችን እመቤታችንም እንዲህ ብላ ስትጸልይ ልጄ
ወዳጄ ሆይ ከስጋዬ ስጋ ከነፍሴ ነፍስ ነስተህ ሰው በመሆንህ
ዘጠኝ ወር ከ5 ቀን በቻለችህ ማሕጸኔ ከአንተ ጋር ሀገር
ለሀገር ስለ መሰደዴ መትተህ ልምናዬን ትሰማኝ ዘንድ
እለምንሃለሁ አለች በዚህ ጊዜ ንውጽውጽውታ ሆነ መቃብራት
ተሰነጣጠቀ ጌታችንም እልፍ ከእልፍ መላዕክቱ ጋር መጥቶ
ሰላም ለኪ ማርያም ምን እንዳደርግልሽ ትለሚኚኛለሽ
አላት፡፡ እርሷም መታሰቢያዬን ያደረገውን ስለ ስሜ ለችግረኛ
የሚራራውን በስሜ ቤተ ክርስቲያን ያነጻውን መባዕ
የሰጠውን ከሃይማኖት ከፍቅር ጽናት ልጁን በስሜ የጠራውን
ሁሉ ማርልኝ ከሞተ ስጋ ከሞተ ነፍስ አድንልኝ አለችው፡፡
ጌታችንም ይህን ሁለ እንዳደርግልሽ መሐልኩ ለኪ በርእስየ
ወበአቡየ ሕያው ወበመንፈስ ቅዱስ ብሎ ቃል ገብቶላት
አርጓል፡፡
ሌላው በላዔ ሰብ በአማርኛ ሰው በላ ማለት ነው፤ ትክክለኛ
ስሙ ግን ስምዖን ይባላል ቅምር በሚባል አገር የሚኖር
እጅግ ባለጸጋ ነበር፤ እንደ አብርሃም እንግዶችን እየተቀበለ
ድሆችን እየመገበ የሚኖር ጻድቅ ነበር፤ ሰይጣን በዚህ ስራው
ቀናበት ሊፈትነውም በሦስት አረጋዊ ሽማግሌዎች ስላሴ ነን
ብሎ ተገለጠለት ልክ እንደ አብርሃም፤ ሐዋርያው ጳውሎስ
ሰይጣን የብርሃን መልአክ መስሎ ይመጣል እንዳለ፤ እርሱም
ሥላሴ መስለውት ተቀበላቸው ተንከባከባቸውም፤ ምግብ
አቀረበላቸው ምግብ አንበላም የምንጠይቅህን ግን
ትፈጽምልን ዘንድ ቃል ግባልን አሉት ቃል ገባላቸው
እንግዲያውስ የምትወደን ከሆነ አንድያ ልጅህን ሰዋልን
አሉት፤ መጀመሪያ ደነገጠ ኃላ አብርሃም ልጁን ሊሰዋ
አልነበረምን እኔንም ሊፈትኑኝ ይሆናል ብሎ ለማረድ
ተዘጋጀ፤ተው የሚለው ድምጽ አልሰማም፤ አረደው
አወራረደው ይዞላቸው ቀረበ፤ መጀመሪያ ቅመስልን አሉት
ቀመሰው ወዲያው እነዚያ ሰዎች ተሰወሩበት እርሱም
አህምሮውን ሳተ ተቅበዘበዘ ከዚያ በኃላ ምግብ አላሰኘውም
የሰው ስጋ እንጂ መጀመሪያ ቤተሰቦቹን በላ ከዚያም ጓደኞቹን
ጦርና የውኃ መንቀል ይዞ ከቤቱ ወጣ ያገኘውን ሰው እየገደለ
ይበላል የበላቸው ሰው ቁጥር 78 ደረሰ፤ በመንገድ ተቀምጦ
የሚለምን በደዌ የተመታ አንድ ደሃ አገኘ ሊበላው ወደ እርሱ
ተጠጋ ግን ቁስሉን አይቶ ተጸየፈው፤ ደሃውም “ስለ
እግዚያብሔር ከያዝከው ውኃ አጠጣኝ” አለው “ዝም በል
ደሃ” ብሎት አለፈ፤ “ኸረ በውኃ ጥም ልሞት ነው ስለ ጻድቃን
ስለ ቅዱሳን” አለው አሁንም ዝም ብሎት ሄደ ለሦስተኛ ጊዜ
“ስለ አዛኝቷ ስለ እምዬ ማርያም” አለው፤ ሰውነቱን አንዳች
ነገር ወረረው “አሁን የጠራከውን ስም እስኪ ድገመው ስለ
ማን አልከኝ” አለው፤ ስለ አዛኝቷ ስለ እመቤቴ ማርያም
አለው፤ ይህቺስ ደግ እንደሆነች በምልጃዋም ከሲኦል
እንደምታወጣ ህጻን እያለው እናትና አባቴ ይነግሩኝ ነበር፤ በል
እንካ አለው እጁን ዘረጋለት ጥርኝ ውኃ ጠብ አደረገለት ወደ
ጉሮሮው አልወረደም የተሰነጠቀ እጁ ውስጥ ገባ እንጂ፤ በለዔ
ሰብ ከዚያች ደቂቃ በኃላ አዕምሮው ተመለሰለት እንዲህም
አለ “በአንድ ዋሻ ውስጥ ገብቼ ስለ ኃጢያቴ አለቅሳለሁ ስጋዬ
ከአጥንቴ እስኪጣበቅ እጾማለሁ ወዮሊኝ ወዮታም አለቢኝ
አለ፤ ወደ ዋሻ ገባ ምግብ ሳይበላ ውኃም ሳይጠጣ 21 ቀን
ኖሮ በርሃብ ሞተ ይላል ተአምረ ማርያም። ጨለማ የለበሱ
ሰይጣናት እያስፈራሩ እያስደነገጡ ነፍሱን ወደ ሲኦል ሊወስዷት
መጡ፤ እመቤታችን ፈጥና በመካከላቸው ተገኘች፤ ልጄ ወዳጄ
ይህችን ነፍስ ማርሊኝ አለችው እናቴ ሆይ 78 ነፍሳትን የበላ
እንዴት ይማራል አላት፤ የካቲት 16 ቀን በጎለጎታ የገባህልኝ
ቃል ኪዳን አስብ ስምሽን የጠራ መታሰቢያሽን ያደረገን
እምርልሻለው ብለኸኝ የለምን አለችው፤ እርሱም እስኪ
ይህቺን ነፍስ በሚዛን አስቀምጧት አለ ቢያስቀምጧት ጥርኝ
ውኃው መዝኖ ተገኘ፤ ስላቺ ስል ምሬታለው ሰባት ቀን
ሲኦልን አስጎብኝታችሁ ወደ ገነት አግቧት አላቸው። ቦታሽ
እዚህ ነበር እያሉ ሲኦልን አስጎብኝተው ወደ ገነት አገቧት።
ልመናዋ ክብሯ የልጇም ቸርነት ከሁላችን ጋር ይሁን።
ተአምረ ማርያም
ድንግል ማርያም በቃል ኪዳኗ አትለየን
በዓል"!!!
ኪዳነ ምህረት ማለት የምህረት መሐላ ማለት ነው፡፡
ከ" 33"በዓላተ እግዝእትነ ድንግል ማርያም አንዱ ነው፡፡
እመቤታችንም ከጌታችን መቃብር እየሄደች በምትለምንበት
ጊዜ አይሁድ ለምቀኝነት አያርፉምና ምን ልታመጣብን ነው
በማለት ሊጣሏት ሲመጡ ጌታችንም ከዓይናቸው ሰውሯታል
አይሁድም ጠባቂ ቢያቆሙ እመቤታችን ዕለት ዕለት መሄዷን
አላቋረጠችን እመቤታችንም እንዲህ ብላ ስትጸልይ ልጄ
ወዳጄ ሆይ ከስጋዬ ስጋ ከነፍሴ ነፍስ ነስተህ ሰው በመሆንህ
ዘጠኝ ወር ከ5 ቀን በቻለችህ ማሕጸኔ ከአንተ ጋር ሀገር
ለሀገር ስለ መሰደዴ መትተህ ልምናዬን ትሰማኝ ዘንድ
እለምንሃለሁ አለች በዚህ ጊዜ ንውጽውጽውታ ሆነ መቃብራት
ተሰነጣጠቀ ጌታችንም እልፍ ከእልፍ መላዕክቱ ጋር መጥቶ
ሰላም ለኪ ማርያም ምን እንዳደርግልሽ ትለሚኚኛለሽ
አላት፡፡ እርሷም መታሰቢያዬን ያደረገውን ስለ ስሜ ለችግረኛ
የሚራራውን በስሜ ቤተ ክርስቲያን ያነጻውን መባዕ
የሰጠውን ከሃይማኖት ከፍቅር ጽናት ልጁን በስሜ የጠራውን
ሁሉ ማርልኝ ከሞተ ስጋ ከሞተ ነፍስ አድንልኝ አለችው፡፡
ጌታችንም ይህን ሁለ እንዳደርግልሽ መሐልኩ ለኪ በርእስየ
ወበአቡየ ሕያው ወበመንፈስ ቅዱስ ብሎ ቃል ገብቶላት
አርጓል፡፡
ሌላው በላዔ ሰብ በአማርኛ ሰው በላ ማለት ነው፤ ትክክለኛ
ስሙ ግን ስምዖን ይባላል ቅምር በሚባል አገር የሚኖር
እጅግ ባለጸጋ ነበር፤ እንደ አብርሃም እንግዶችን እየተቀበለ
ድሆችን እየመገበ የሚኖር ጻድቅ ነበር፤ ሰይጣን በዚህ ስራው
ቀናበት ሊፈትነውም በሦስት አረጋዊ ሽማግሌዎች ስላሴ ነን
ብሎ ተገለጠለት ልክ እንደ አብርሃም፤ ሐዋርያው ጳውሎስ
ሰይጣን የብርሃን መልአክ መስሎ ይመጣል እንዳለ፤ እርሱም
ሥላሴ መስለውት ተቀበላቸው ተንከባከባቸውም፤ ምግብ
አቀረበላቸው ምግብ አንበላም የምንጠይቅህን ግን
ትፈጽምልን ዘንድ ቃል ግባልን አሉት ቃል ገባላቸው
እንግዲያውስ የምትወደን ከሆነ አንድያ ልጅህን ሰዋልን
አሉት፤ መጀመሪያ ደነገጠ ኃላ አብርሃም ልጁን ሊሰዋ
አልነበረምን እኔንም ሊፈትኑኝ ይሆናል ብሎ ለማረድ
ተዘጋጀ፤ተው የሚለው ድምጽ አልሰማም፤ አረደው
አወራረደው ይዞላቸው ቀረበ፤ መጀመሪያ ቅመስልን አሉት
ቀመሰው ወዲያው እነዚያ ሰዎች ተሰወሩበት እርሱም
አህምሮውን ሳተ ተቅበዘበዘ ከዚያ በኃላ ምግብ አላሰኘውም
የሰው ስጋ እንጂ መጀመሪያ ቤተሰቦቹን በላ ከዚያም ጓደኞቹን
ጦርና የውኃ መንቀል ይዞ ከቤቱ ወጣ ያገኘውን ሰው እየገደለ
ይበላል የበላቸው ሰው ቁጥር 78 ደረሰ፤ በመንገድ ተቀምጦ
የሚለምን በደዌ የተመታ አንድ ደሃ አገኘ ሊበላው ወደ እርሱ
ተጠጋ ግን ቁስሉን አይቶ ተጸየፈው፤ ደሃውም “ስለ
እግዚያብሔር ከያዝከው ውኃ አጠጣኝ” አለው “ዝም በል
ደሃ” ብሎት አለፈ፤ “ኸረ በውኃ ጥም ልሞት ነው ስለ ጻድቃን
ስለ ቅዱሳን” አለው አሁንም ዝም ብሎት ሄደ ለሦስተኛ ጊዜ
“ስለ አዛኝቷ ስለ እምዬ ማርያም” አለው፤ ሰውነቱን አንዳች
ነገር ወረረው “አሁን የጠራከውን ስም እስኪ ድገመው ስለ
ማን አልከኝ” አለው፤ ስለ አዛኝቷ ስለ እመቤቴ ማርያም
አለው፤ ይህቺስ ደግ እንደሆነች በምልጃዋም ከሲኦል
እንደምታወጣ ህጻን እያለው እናትና አባቴ ይነግሩኝ ነበር፤ በል
እንካ አለው እጁን ዘረጋለት ጥርኝ ውኃ ጠብ አደረገለት ወደ
ጉሮሮው አልወረደም የተሰነጠቀ እጁ ውስጥ ገባ እንጂ፤ በለዔ
ሰብ ከዚያች ደቂቃ በኃላ አዕምሮው ተመለሰለት እንዲህም
አለ “በአንድ ዋሻ ውስጥ ገብቼ ስለ ኃጢያቴ አለቅሳለሁ ስጋዬ
ከአጥንቴ እስኪጣበቅ እጾማለሁ ወዮሊኝ ወዮታም አለቢኝ
አለ፤ ወደ ዋሻ ገባ ምግብ ሳይበላ ውኃም ሳይጠጣ 21 ቀን
ኖሮ በርሃብ ሞተ ይላል ተአምረ ማርያም። ጨለማ የለበሱ
ሰይጣናት እያስፈራሩ እያስደነገጡ ነፍሱን ወደ ሲኦል ሊወስዷት
መጡ፤ እመቤታችን ፈጥና በመካከላቸው ተገኘች፤ ልጄ ወዳጄ
ይህችን ነፍስ ማርሊኝ አለችው እናቴ ሆይ 78 ነፍሳትን የበላ
እንዴት ይማራል አላት፤ የካቲት 16 ቀን በጎለጎታ የገባህልኝ
ቃል ኪዳን አስብ ስምሽን የጠራ መታሰቢያሽን ያደረገን
እምርልሻለው ብለኸኝ የለምን አለችው፤ እርሱም እስኪ
ይህቺን ነፍስ በሚዛን አስቀምጧት አለ ቢያስቀምጧት ጥርኝ
ውኃው መዝኖ ተገኘ፤ ስላቺ ስል ምሬታለው ሰባት ቀን
ሲኦልን አስጎብኝታችሁ ወደ ገነት አግቧት አላቸው። ቦታሽ
እዚህ ነበር እያሉ ሲኦልን አስጎብኝተው ወደ ገነት አገቧት።
ልመናዋ ክብሯ የልጇም ቸርነት ከሁላችን ጋር ይሁን።
ተአምረ ማርያም
ድንግል ማርያም በቃል ኪዳኗ አትለየን
Monday, February 20, 2017
ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ነኝ: =>+*"+<+>†† ዘወረደ /ዘመነ አዳም/- ††
ዘወረደ /ዘመነ አዳም/
የዐቢይ ጾም የመጀመሪያ ሳምንት ዘወረደ: ሙሴኒ:ሕርቃል
ይባላል፡፡ ዘወረደ ማለት፣ ከላይ የመጣ፣ የወረደ ማለት ነው፡፡
ይህም የአምላካችን ሰው መሆን ያመለክታል፡፡ ከሰማይ
ከወረደው በቀር ወደሰማይ የወጣ የለም ካለው ከጌታችን
ከመድኃኒታችን ከኢየሱስ ክርስቶስ ቃል በመነሳት ሊቁ ቅዱስ
ያሬድ በዚህ ዕለት ምስባክ “ዘወረደ እምላዕሉ አይሁድ ሰቀሉ
ወሚመ ኢያእመሩ እግዚአ ኩሉ ዘየሐዩ በቃሉ” በማለት
በጾመ ድጓው መጀመሪያ ላይ ገልጾት ይገኛል፡፡
አዳምን ለማዳን ከሰማይ የወረደውን አይሁድ ሰቀሉት፣
የሰማይን ሥልጣን ያለው የሁሉ ጌታ እንደሆነም ምንም
አላወቁም ብሎ ተናግሮ ነበር፡፡ ይህም ድርሰት በቤተ
ክርስቲያናችን የጾም መጀመሪያ የሆነው ዕለተ ሰንበት
ዋዜማ፣ መግቢያ፣ /መሐትው/ ሆኖ ከዋዜማ በፊት
ምንጊዜም በየዓመቱ ይቆማል፡፡ ይዘመራል፡፡ ይመሰገናል
ማለት ነው፡፡
ስለዚህ የሳምንቱ ስያሜ ከዚህ የተወሰደ ነው፡፡ እንዲሁም
ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ የማዳን ሥራውን
የጀመረው፤ ከሰማየ ሰማያት ወርዶ ሰው በመሆን ፣
በዮርዳኖስ ተጠምቆ በማስተማር እንደሆነ ሁሉ የመጀሪያው
ሳምንት ዘወረደ ይባላል፡፡
በዚህ ሳምንት በተለይም እሑድና ሰኞ የሚነገሩት ውዳሴያት
ከመጻሕፍተ ኦሪትና ነቢያት የተወሰዱ ናቸው፡፡ ሁለተኛም
ሙሴኒ በመባል ይታወቃል፡፡ እግዚአብሔር አምላክ አዳምን
ለማዳን ከሰማይ መውረዱንና በመስቀል መሰቀሉን
ስለሚያወሳ ነው፡፡
በተጨማሪም ይህ የመጀመሪያው ሳምንት ጾመ ሕርቃል
ይባላል፡፡ በ714 ዓ.ም.ሕርቃል /ኤራቅሊየስ/ የቤዛንታይን
ንጉሥ ነበረ፡፡ይህ ሳምንት በስሙ የተጠራበት ምክንያት
በዘመኑ ፋርሶች ኢየሩሳሌምን ወርረው የጌታችን መስቀል
ማርከው ወስደው ነበር፡፡ እርሱ ወደፋርስ ዘመቶ መስቀሉን
ከእነርሱ ነጥቆ ይዞ ወደ ኢየሩሳሌም ተመልሷል፡፡
ሕርቃል ከፋርሶች ጋር ከመዋጋቱ በፊት ሐዋርያት
በሲኖዶሳቸው ነፍስ የገደለ ሰው እስከ እድሜ ልኩ ይጹም
ብለው ሥርዓት ሠርተዋልና ጾሙን ፈርቶ ስለነበር
በኢየሩሳሌም የነበሩ ምእመናን አሳቡን ደግፈው “አንተ
ጠላታችንን አጥፋልን ፣መስቀሉን አስመልስልን እንጂ የአንድ
ሰው እድሜ ቢበዛ ሰባ ሰማንያ ነው ፡፡ጾሙንአምስት አምስት
ቀን ተከፋፍለን እኛ ተከፋፍለን እንጾምልሃለን፡፡”ብለው
ጾመውለታል፡፡
ይህንን መሠረት በማድረግ ያላወቁት አንድ ጊዜ ጾመው
ትተውታል፡፡ ያወቁት ግን ቀድሞም ሐዋርያት ጾመውታል
ብለው ሥርዓት አድርገው በዓመት በዐቢይ ጾም መጀመሪያ
ላይ ጾመ ሕርቃል እያሉ የሚጾሙት ሆነዋል፡፡ስለዚህ
ቤተክርስቲያናችን ይህንን መሠረት በማድረግ በጌታችን
ከመድኀኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ጾም የመጀመሪያውን
ሳምንት ጾመ ሕርቃል በሚል ስያሜ ሰማይ እንዲጾም
አድርጋለች፡፡ /መጋቢት 10 ስንክሳር ይመልከቱ፡፡/
የቤተ ክርስቲያናችን ታሉቁ ሊቅ ቅዱስ ያሬድ፣ በዘወረደ ጾመ
ድጓው ሰንበት ለሰው ልጆች ብቻ ሳይሆን፣ ሕይወት ላለው
ነገር ሁሉ ጸጥታና ሰላም የሰፈነባት የዕረፍት ቀን ስለመሆኗ
“አዘዞ እግዚአብሔር ለሙሴ ወይቤሎ ሰብዕከ ወላህምከ
ወኲሉ ቤትከ ያዕርፍ በሰንበት” ዘፀ.20፥10፣23፣12፣ ጾመ
ድጓ፣ እግዚአብሔር ሙሴን ሕዝብህ የከብትህ መንጋህ
ቤተሰብህ ሀሉ በሰንበት ቀን ከድካማቸው ይረፉ በማለት
አዘዘው ይላል፡፡ በዚህም ዘመነ ጾም፣ ወይም ጾመ ሙሴ
ይባላል፡፡
በጾመ ድጓው ዘወረደ እየተባለ የሚታወቀው፣ በጾመ አርባው
ወቅት በተለይም በመጀመሪያው ሳምንት የሚገኘው ያሬዳዊ
ድርሰት በነግህ በሠለስት፣ በቀትርና በሠርክ እንዲሁም
ቅዳሜና እዡድ በሌሊት የሚዘመር ነው፡፡ በውስጡም
የያዘው ፍሬ አሳብ፣ የጾምን፣ የጸሎትን፣ የምጽዋትንና
የፍቅርን ጠቃሚነት አጉልቶ የሚያስተምር ነው፡፡
በዚህ በጾም ወቅት በቤተ ክርስቲያናችን ሥርዓት በአብዛኛው
ከቅዱስ ያሬድ ድርሰቶች ውስጥ የሚዘመረው ምዕራፍ
የተባለው ነው፡፡ ምዕራፍ የተባለበት ምክንያትም
በየመዝሙራቱ መሀል ሃሌታና ድጓ እያስገባ ለመዝሙሩ
ማረፊያ ስላበጀለት በዚህ ምክንያት ምዕራፍ የሚል ስያሜ
ሊያገኝ ችሏል፡፡ ይህ የዜማ መጽሐፍ በሁለት ታላላቅ ክፍሎች
ይከፈላል፡፡ ይኸውም የዘወትር ምዕራፍና የጾም ምዕራፍ
በመባል ይታወቃል፡፡የዘውትር ምዕራፍ የሚባለው በዓመቱ
ውስጥ ባሉት ቀናት ውስጥ ሳምንታትና በዓላት ሁልጊዜ
በአገልግሎት ላይ የሚውል ሲሆን፣ የጾም ምዕራፍ የሚባለው
ደግሞ በጾመ አርባ ብቻ ለአገልግሎት የሚውል ነው፡፡
ከዚህም በተጨማሪ በዐሥሩ ምህላት አርዕስተ ምህላ በዚሁ
ክፍል ይካተታል፡፡ የምዕራፍ ቅንብር ከመዝሙረ ዳዊት፣
ከድጓና ከጾመ ድጓ ጋር የተቀናጀ ነው፡፡ የትምህርት
አሰጣጡም እንደ ድጓው ወይም እንደ ዝማሬ መዋሥዕቱ
መጽሐፍ ተዘርግቶ ሳይሆን በቃል የሚጠናና የሚወሰን ነው፡፡
ስለሆነም ምዕራፍን ለመማር 150 መዝሙረ ዳዊትን፣
ከነቢያት 15 ምዕራፎችንና 5 መኃልያተ ሰሎሞንን በቃል
ሸምድዶ መያዝ ይጠበቅበታል፡፡ ወይም ግድ ነው፡፡
ጾምን መጾም የፈቃድ ብቻ ሳይሆን የትእዛዝም ነው፡፡
በዘመነ ብሉይ ነቢዩ ኢዩኤል “ቀድሱ ጾመ ወስብኩ ምህላ”
ጾምን ያዙ አጽኑ ምሕላንም ዐውጁ ሸማግሌዎቹን
ከፈጣሪያችን ቤት ሰብስባችሁ በአንድነት ሁናችሁ ወደ
እግዚአብሔር ጩሁ /ለምኑ/ ብሏል፡፡ ኢዮ.ምዕ.1፥11፣
2፣12፣15-16 ሐዋርያው ቅዱስ ጳውሎስም ወኲኑ ላዕካነ፣
ለእግዚአብሔር በጾም ወበንጽሕ፡፡ በጾም፣ በንጽሐና
ተወስናችሁ እግዚአብሔርን አገልግሉ ብሏል 2ቆሮ.6፥4-6፡፡
ጾም ከሌለ ወይም ተገቢ ካልሆነ ጌታችን በምትጾሙበት ጊዜ
እንደ ግብዞች አትሁኑ ስለ ጽድቅ የሚራቡ የሚጠሙ ንዑዳን
ክብራን ናቸው ለምን አለ? ማቴ.5፥፣6፣16፡፡ ነቢዩ ዳዊትም
ሰውነቴን በጾም አሳመምኳት በቀጠና፣ በሰልት አደከምኳት
ለምን አለ መዝ.34፥68፣ ት.ዳን. 9፥3-4፣ 14፥5
ነብዩ ሚኪያስ ሐዋርያት ሙሸራውን ከነሱ ለይተው
የሚወስዱበት ጊዜ ይመጣል ያን ጊዜ ይጾማሉ ያለውን የጌታን
ቃል መሠረት በማድረግ ክርስቶስ በሞት ከተለያቸው በኋላ
ጾመዋል፡፡ ጾምንም ሠርተዋል የሐዋ.ሥራ 13፥3፡፡ ሠለስቱ
ምዕትም ሐዋርያት የጾሙትንና እንዲጾም የወሰኑትን መጾም
ይገባል ብለው ቤተ ክርስቲያን የተቀበለቻቸውን አጽዋማት
እንዲጾሙ መወሰናቸው ይህን የጌታ ቃል መሠረት በማድረግ
ስለሆነ፣ የትእዛዝ መሆኑን ተገንዝበን መጾም አለብን፡፡
ጌታችን መድኀኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስም ሠራዔ ሕግ
እንደመሆኑ አርባ ቀን አርቦ ሌሊት ጾመ እንጂ እርሱ ሳይጾም
ጾሙ አላለንም ማቴ.4፥2፡፡ ጾመን ለማበርከት ያብቃን፡፡
አሜን!
የዐቢይ ጾም የመጀመሪያ ሳምንት ዘወረደ: ሙሴኒ:ሕርቃል
ይባላል፡፡ ዘወረደ ማለት፣ ከላይ የመጣ፣ የወረደ ማለት ነው፡፡
ይህም የአምላካችን ሰው መሆን ያመለክታል፡፡ ከሰማይ
ከወረደው በቀር ወደሰማይ የወጣ የለም ካለው ከጌታችን
ከመድኃኒታችን ከኢየሱስ ክርስቶስ ቃል በመነሳት ሊቁ ቅዱስ
ያሬድ በዚህ ዕለት ምስባክ “ዘወረደ እምላዕሉ አይሁድ ሰቀሉ
ወሚመ ኢያእመሩ እግዚአ ኩሉ ዘየሐዩ በቃሉ” በማለት
በጾመ ድጓው መጀመሪያ ላይ ገልጾት ይገኛል፡፡
አዳምን ለማዳን ከሰማይ የወረደውን አይሁድ ሰቀሉት፣
የሰማይን ሥልጣን ያለው የሁሉ ጌታ እንደሆነም ምንም
አላወቁም ብሎ ተናግሮ ነበር፡፡ ይህም ድርሰት በቤተ
ክርስቲያናችን የጾም መጀመሪያ የሆነው ዕለተ ሰንበት
ዋዜማ፣ መግቢያ፣ /መሐትው/ ሆኖ ከዋዜማ በፊት
ምንጊዜም በየዓመቱ ይቆማል፡፡ ይዘመራል፡፡ ይመሰገናል
ማለት ነው፡፡
ስለዚህ የሳምንቱ ስያሜ ከዚህ የተወሰደ ነው፡፡ እንዲሁም
ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ የማዳን ሥራውን
የጀመረው፤ ከሰማየ ሰማያት ወርዶ ሰው በመሆን ፣
በዮርዳኖስ ተጠምቆ በማስተማር እንደሆነ ሁሉ የመጀሪያው
ሳምንት ዘወረደ ይባላል፡፡
በዚህ ሳምንት በተለይም እሑድና ሰኞ የሚነገሩት ውዳሴያት
ከመጻሕፍተ ኦሪትና ነቢያት የተወሰዱ ናቸው፡፡ ሁለተኛም
ሙሴኒ በመባል ይታወቃል፡፡ እግዚአብሔር አምላክ አዳምን
ለማዳን ከሰማይ መውረዱንና በመስቀል መሰቀሉን
ስለሚያወሳ ነው፡፡
በተጨማሪም ይህ የመጀመሪያው ሳምንት ጾመ ሕርቃል
ይባላል፡፡ በ714 ዓ.ም.ሕርቃል /ኤራቅሊየስ/ የቤዛንታይን
ንጉሥ ነበረ፡፡ይህ ሳምንት በስሙ የተጠራበት ምክንያት
በዘመኑ ፋርሶች ኢየሩሳሌምን ወርረው የጌታችን መስቀል
ማርከው ወስደው ነበር፡፡ እርሱ ወደፋርስ ዘመቶ መስቀሉን
ከእነርሱ ነጥቆ ይዞ ወደ ኢየሩሳሌም ተመልሷል፡፡
ሕርቃል ከፋርሶች ጋር ከመዋጋቱ በፊት ሐዋርያት
በሲኖዶሳቸው ነፍስ የገደለ ሰው እስከ እድሜ ልኩ ይጹም
ብለው ሥርዓት ሠርተዋልና ጾሙን ፈርቶ ስለነበር
በኢየሩሳሌም የነበሩ ምእመናን አሳቡን ደግፈው “አንተ
ጠላታችንን አጥፋልን ፣መስቀሉን አስመልስልን እንጂ የአንድ
ሰው እድሜ ቢበዛ ሰባ ሰማንያ ነው ፡፡ጾሙንአምስት አምስት
ቀን ተከፋፍለን እኛ ተከፋፍለን እንጾምልሃለን፡፡”ብለው
ጾመውለታል፡፡
ይህንን መሠረት በማድረግ ያላወቁት አንድ ጊዜ ጾመው
ትተውታል፡፡ ያወቁት ግን ቀድሞም ሐዋርያት ጾመውታል
ብለው ሥርዓት አድርገው በዓመት በዐቢይ ጾም መጀመሪያ
ላይ ጾመ ሕርቃል እያሉ የሚጾሙት ሆነዋል፡፡ስለዚህ
ቤተክርስቲያናችን ይህንን መሠረት በማድረግ በጌታችን
ከመድኀኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ጾም የመጀመሪያውን
ሳምንት ጾመ ሕርቃል በሚል ስያሜ ሰማይ እንዲጾም
አድርጋለች፡፡ /መጋቢት 10 ስንክሳር ይመልከቱ፡፡/
የቤተ ክርስቲያናችን ታሉቁ ሊቅ ቅዱስ ያሬድ፣ በዘወረደ ጾመ
ድጓው ሰንበት ለሰው ልጆች ብቻ ሳይሆን፣ ሕይወት ላለው
ነገር ሁሉ ጸጥታና ሰላም የሰፈነባት የዕረፍት ቀን ስለመሆኗ
“አዘዞ እግዚአብሔር ለሙሴ ወይቤሎ ሰብዕከ ወላህምከ
ወኲሉ ቤትከ ያዕርፍ በሰንበት” ዘፀ.20፥10፣23፣12፣ ጾመ
ድጓ፣ እግዚአብሔር ሙሴን ሕዝብህ የከብትህ መንጋህ
ቤተሰብህ ሀሉ በሰንበት ቀን ከድካማቸው ይረፉ በማለት
አዘዘው ይላል፡፡ በዚህም ዘመነ ጾም፣ ወይም ጾመ ሙሴ
ይባላል፡፡
በጾመ ድጓው ዘወረደ እየተባለ የሚታወቀው፣ በጾመ አርባው
ወቅት በተለይም በመጀመሪያው ሳምንት የሚገኘው ያሬዳዊ
ድርሰት በነግህ በሠለስት፣ በቀትርና በሠርክ እንዲሁም
ቅዳሜና እዡድ በሌሊት የሚዘመር ነው፡፡ በውስጡም
የያዘው ፍሬ አሳብ፣ የጾምን፣ የጸሎትን፣ የምጽዋትንና
የፍቅርን ጠቃሚነት አጉልቶ የሚያስተምር ነው፡፡
በዚህ በጾም ወቅት በቤተ ክርስቲያናችን ሥርዓት በአብዛኛው
ከቅዱስ ያሬድ ድርሰቶች ውስጥ የሚዘመረው ምዕራፍ
የተባለው ነው፡፡ ምዕራፍ የተባለበት ምክንያትም
በየመዝሙራቱ መሀል ሃሌታና ድጓ እያስገባ ለመዝሙሩ
ማረፊያ ስላበጀለት በዚህ ምክንያት ምዕራፍ የሚል ስያሜ
ሊያገኝ ችሏል፡፡ ይህ የዜማ መጽሐፍ በሁለት ታላላቅ ክፍሎች
ይከፈላል፡፡ ይኸውም የዘወትር ምዕራፍና የጾም ምዕራፍ
በመባል ይታወቃል፡፡የዘውትር ምዕራፍ የሚባለው በዓመቱ
ውስጥ ባሉት ቀናት ውስጥ ሳምንታትና በዓላት ሁልጊዜ
በአገልግሎት ላይ የሚውል ሲሆን፣ የጾም ምዕራፍ የሚባለው
ደግሞ በጾመ አርባ ብቻ ለአገልግሎት የሚውል ነው፡፡
ከዚህም በተጨማሪ በዐሥሩ ምህላት አርዕስተ ምህላ በዚሁ
ክፍል ይካተታል፡፡ የምዕራፍ ቅንብር ከመዝሙረ ዳዊት፣
ከድጓና ከጾመ ድጓ ጋር የተቀናጀ ነው፡፡ የትምህርት
አሰጣጡም እንደ ድጓው ወይም እንደ ዝማሬ መዋሥዕቱ
መጽሐፍ ተዘርግቶ ሳይሆን በቃል የሚጠናና የሚወሰን ነው፡፡
ስለሆነም ምዕራፍን ለመማር 150 መዝሙረ ዳዊትን፣
ከነቢያት 15 ምዕራፎችንና 5 መኃልያተ ሰሎሞንን በቃል
ሸምድዶ መያዝ ይጠበቅበታል፡፡ ወይም ግድ ነው፡፡
ጾምን መጾም የፈቃድ ብቻ ሳይሆን የትእዛዝም ነው፡፡
በዘመነ ብሉይ ነቢዩ ኢዩኤል “ቀድሱ ጾመ ወስብኩ ምህላ”
ጾምን ያዙ አጽኑ ምሕላንም ዐውጁ ሸማግሌዎቹን
ከፈጣሪያችን ቤት ሰብስባችሁ በአንድነት ሁናችሁ ወደ
እግዚአብሔር ጩሁ /ለምኑ/ ብሏል፡፡ ኢዮ.ምዕ.1፥11፣
2፣12፣15-16 ሐዋርያው ቅዱስ ጳውሎስም ወኲኑ ላዕካነ፣
ለእግዚአብሔር በጾም ወበንጽሕ፡፡ በጾም፣ በንጽሐና
ተወስናችሁ እግዚአብሔርን አገልግሉ ብሏል 2ቆሮ.6፥4-6፡፡
ጾም ከሌለ ወይም ተገቢ ካልሆነ ጌታችን በምትጾሙበት ጊዜ
እንደ ግብዞች አትሁኑ ስለ ጽድቅ የሚራቡ የሚጠሙ ንዑዳን
ክብራን ናቸው ለምን አለ? ማቴ.5፥፣6፣16፡፡ ነቢዩ ዳዊትም
ሰውነቴን በጾም አሳመምኳት በቀጠና፣ በሰልት አደከምኳት
ለምን አለ መዝ.34፥68፣ ት.ዳን. 9፥3-4፣ 14፥5
ነብዩ ሚኪያስ ሐዋርያት ሙሸራውን ከነሱ ለይተው
የሚወስዱበት ጊዜ ይመጣል ያን ጊዜ ይጾማሉ ያለውን የጌታን
ቃል መሠረት በማድረግ ክርስቶስ በሞት ከተለያቸው በኋላ
ጾመዋል፡፡ ጾምንም ሠርተዋል የሐዋ.ሥራ 13፥3፡፡ ሠለስቱ
ምዕትም ሐዋርያት የጾሙትንና እንዲጾም የወሰኑትን መጾም
ይገባል ብለው ቤተ ክርስቲያን የተቀበለቻቸውን አጽዋማት
እንዲጾሙ መወሰናቸው ይህን የጌታ ቃል መሠረት በማድረግ
ስለሆነ፣ የትእዛዝ መሆኑን ተገንዝበን መጾም አለብን፡፡
ጌታችን መድኀኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስም ሠራዔ ሕግ
እንደመሆኑ አርባ ቀን አርቦ ሌሊት ጾመ እንጂ እርሱ ሳይጾም
ጾሙ አላለንም ማቴ.4፥2፡፡ ጾመን ለማበርከት ያብቃን፡፡
አሜን!
ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ነኝ: =>+*"+<+>†† የዐቢይ ጾም የመጀመሪያው ሳምንት ዘወረደ ††
. ዘወረደ ወይም ሕርቃል ወይምሙሴኒ
✔ የዐቢይ ጾም የመጀመሪያው ሳምንት ዘወረደ ይባላል፡፡
‹‹ዘወረደ እምላዕሉ አይሁድ ሰቀሉ›› የሚልና ይህንን
የመሳሰለ ጌታ እኛን ለማዳንና ፍቅሩን ሊገልጽልን ከሰማያት
መውረዱን ከድንግል ማርያም የእኛን ሥጋ መዋሐዱን
የሚያዘክር ምስጋና የሚቀርብበት ሳምንት ነው፡፡
✔ ሌላም ስም አለው ጾመ ሕርቃል ይባላል፡፡ ይህ ጾም
የጾም መግቢያ የመጀመሪያ ሳምንት የምንጾመው ጾም
ሲሆን ሕርቃል የሚል ስያሜ ተሰጥቶታል፡፡
✔ ሕርቃል ማን ነው? ለምንስ በስሙ ተሰየመ? በ614
ዓ.ም ኪርዮስ የተባለ የፋርስ ንጉሥ ኢየሩሳሌምን በመውረር
ጥቃት አደረሰ፡፡
✔ በዚህ ወቅት በኢየሩሳሌም ንግሥት ዕሌኒ በሠራችው
ቤተመቅደስ ውስጥ ሲገባ ንግሥቷ በክብር አስቀምጣው
የነበረው የጌታችን የመድኃኒታችን የኢየሱስ ክርስቶስ መስቀል
እንደ ፀሐይ ሲያበራ አገኘው፡፡
✔ ቢነካው አቃጠለው ዲያቆናቱን አሸክሞ ሌላውን ንዋየ
ቅድሳት ዘርፎ 60ሺ የሚደርሱትን አቁስሎ ገድሎ 3ሺ
የሚሆኑትን ማርኮ ከተማዋንም አቃጥሎ ወደ ፋርስ ባቢሎን
ይመለሳል፡፡
✔ በዚህ ጊዜ ከጦርነቱ ያመለጡ በየዋሻው በየጉራንጉሩ
ገብተው የተሸሸጉ ተሰብስበው ከ14 ዓመት በኋላ በ628
ጩኸታቸውንና የደረሰባቸውን በደል ለክርስቲየኑ የሮም
ንጉሥ ሕርቃል ይነግሩታል፡፡
✔ እርሱም ሐዋርያት ሰውን የገደለ እድሜውን በሙሉ
ይጹም ስላሉ እንዴት ላድርገው አላቸው እኛ የአንተን እድሜ
ተከፋፍለን እንጾማለን ብለው አንድ አንድ ሳምንት ደርሷቸው
ጾሙን በሚገባ ጾመውታል፡፡
✔ የጌታችን የኢየሱስ ክርስቶስ መስቀልና የተማረኩ
ክርስቲያኖችን ለመመለስ ሕርቃል ጦር መዝዞ በኪርዮስ ላይ
ተነሳበት ድል ለሕርቃል ሆነና መስቀሉን ያለበትን አጥቶ
ሲቸገር መስቀሉን ሲቀብርና ዲያቆናቱን ሲያስገድል በመስኮት
ሆና ያየችው ከኢየሩሳሌም የተማረከች አንዲት ብላቴና
አሳይታው አውጥቶ በልብሰ መንግሥቱ ጠቅልሎ ወደ
ቁስጥንጥንያ ተመለሰ፡፡
✔ የተማረኩት በሙሉ ነጻ ወጡ ይህን ለማሰብ ለማስታወስ
በተጨማሪ በኃጢአት ላይ ድል እንድናገኝ መንፈሳዊ ጦር
በውስጣችን እንዲበዛልን መስቀልህ ከምርኮ እንደተመለሰ
እኛንም ከኃጢአት ምርኮ መልሰን ለሕርቃል ድል መንሳትንና
በጠላቶቹ ላይ ኃይልን እንደሰጠኸው ለእኛም በኃጢአት ላይ
ድል መንሳት መንፈሳዊ ኃይልን ስጠን እያልን እንጾመዋለን፡፡
✔ በጌታ ጾም ላይ እንዲጾም የሆነበት ምክንያት ጾሙ
የጌታ ጾም በሚጾምበት ወቅት ላይ ስለተጾመ
ቤተክርስቲያናችን አብራ ደንግጋዋለች፡፡
✔ እዚህ ላይ በዚያን ጊዜ ለሕርቃል ሕዝቡ ሱባኤ
ይዞለታል፡፡ ዛሬም እኛ ለቤተክርስቲያን ያደረግነውን በማሰብ
እግዚአብሔር አምላክ ለሕርቃል የሰጠውን በጠላቶቹ ላይ
ድል መንሳትን ለእኛም እንዲሰጠን የምንጠይቅበት ስለሆነ
የመጀመሪያውን ሳምንት በሕርቃል ሰይመን ጾሙን
እንጾማለን፡፡
✔ የእኛ ጠላት የጨለማ ገዥ የሆነው ዲያቢሎስ ነውና
እሱን ደግሞ በጾም እንደምናሸንፈው ጌታችን መድኃኒታችን
ኢየሱስ ክርስቶስ አስተምሮናል፡፡
✔ «ዘወረደ» ማለትም በቀጥታ፣ ቃል በቃል ሲተረጐም
«የወረደ» ማለት ነው፡፡ ይህም በምስጢሩ አምላክ ወልደ
አምላክ ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ለቤዛ ዓለም በቅዱስ ፈቃዱ
ሰው ሆኖ ከሰማየ ሰማያት = ከባሕርይ ልዕልናው በትሕትና
ወርዶ ከቅድስት ድንግል ማርያም መወለዱን የሚያመላክት፣
ይህም የሚታወስበት፣ የሚወሳበት የዐቢይ ጾም አንደኛው
ሳምንት ነው፡፡ 《ዮሐ.3-13》፡፡
✔ ሳምንቱ ሙሴኒ የተባለበትም ምክንያት በዚሁ ሳምንት
መጀመሪያ የሰኞ ዕዝል «ከመዝ ይቤ ሙሴ ፀዓቱ
እምትእይንት» «ሙሴ ከከተማ መውጣቱ እንደዚህ ነው አለ»
ስለሚል እንደዚሁም የዚሁ ዕለት ማለት የሰኞ አቡን «ሙሴኒ
ይቤ በውስተ ኦሪት ምድር ሰናይት» እያለ የሙሴን ታሪክ
ስለሚያጠቃቅስ ሳምንቱ ሙሴኒ ተባለ፡፡
✔ ነቢያትም አርባ አርባ ቀን ጾመው ከአለፉ በኋላ የሙሴ
ሕግና ትንቢተ ነቢያት ፈጻሚ የሆነው ምላካችን እንደ እነሱ
40 ቀንና 40 ሌሊት መጾሙን የሚያስታውስ ነው፡፡
《ዘፀ.24-18》፤ 《1ኛ.ነገ.19-8》፤ 《ማቴ. 4-1-4》፡፡
↪ ወስብሐት ለእግዚአብሔር
↪ ምንጭ፡- ጾምና ምጽዋት
✔ የዐቢይ ጾም የመጀመሪያው ሳምንት ዘወረደ ይባላል፡፡
‹‹ዘወረደ እምላዕሉ አይሁድ ሰቀሉ›› የሚልና ይህንን
የመሳሰለ ጌታ እኛን ለማዳንና ፍቅሩን ሊገልጽልን ከሰማያት
መውረዱን ከድንግል ማርያም የእኛን ሥጋ መዋሐዱን
የሚያዘክር ምስጋና የሚቀርብበት ሳምንት ነው፡፡
✔ ሌላም ስም አለው ጾመ ሕርቃል ይባላል፡፡ ይህ ጾም
የጾም መግቢያ የመጀመሪያ ሳምንት የምንጾመው ጾም
ሲሆን ሕርቃል የሚል ስያሜ ተሰጥቶታል፡፡
✔ ሕርቃል ማን ነው? ለምንስ በስሙ ተሰየመ? በ614
ዓ.ም ኪርዮስ የተባለ የፋርስ ንጉሥ ኢየሩሳሌምን በመውረር
ጥቃት አደረሰ፡፡
✔ በዚህ ወቅት በኢየሩሳሌም ንግሥት ዕሌኒ በሠራችው
ቤተመቅደስ ውስጥ ሲገባ ንግሥቷ በክብር አስቀምጣው
የነበረው የጌታችን የመድኃኒታችን የኢየሱስ ክርስቶስ መስቀል
እንደ ፀሐይ ሲያበራ አገኘው፡፡
✔ ቢነካው አቃጠለው ዲያቆናቱን አሸክሞ ሌላውን ንዋየ
ቅድሳት ዘርፎ 60ሺ የሚደርሱትን አቁስሎ ገድሎ 3ሺ
የሚሆኑትን ማርኮ ከተማዋንም አቃጥሎ ወደ ፋርስ ባቢሎን
ይመለሳል፡፡
✔ በዚህ ጊዜ ከጦርነቱ ያመለጡ በየዋሻው በየጉራንጉሩ
ገብተው የተሸሸጉ ተሰብስበው ከ14 ዓመት በኋላ በ628
ጩኸታቸውንና የደረሰባቸውን በደል ለክርስቲየኑ የሮም
ንጉሥ ሕርቃል ይነግሩታል፡፡
✔ እርሱም ሐዋርያት ሰውን የገደለ እድሜውን በሙሉ
ይጹም ስላሉ እንዴት ላድርገው አላቸው እኛ የአንተን እድሜ
ተከፋፍለን እንጾማለን ብለው አንድ አንድ ሳምንት ደርሷቸው
ጾሙን በሚገባ ጾመውታል፡፡
✔ የጌታችን የኢየሱስ ክርስቶስ መስቀልና የተማረኩ
ክርስቲያኖችን ለመመለስ ሕርቃል ጦር መዝዞ በኪርዮስ ላይ
ተነሳበት ድል ለሕርቃል ሆነና መስቀሉን ያለበትን አጥቶ
ሲቸገር መስቀሉን ሲቀብርና ዲያቆናቱን ሲያስገድል በመስኮት
ሆና ያየችው ከኢየሩሳሌም የተማረከች አንዲት ብላቴና
አሳይታው አውጥቶ በልብሰ መንግሥቱ ጠቅልሎ ወደ
ቁስጥንጥንያ ተመለሰ፡፡
✔ የተማረኩት በሙሉ ነጻ ወጡ ይህን ለማሰብ ለማስታወስ
በተጨማሪ በኃጢአት ላይ ድል እንድናገኝ መንፈሳዊ ጦር
በውስጣችን እንዲበዛልን መስቀልህ ከምርኮ እንደተመለሰ
እኛንም ከኃጢአት ምርኮ መልሰን ለሕርቃል ድል መንሳትንና
በጠላቶቹ ላይ ኃይልን እንደሰጠኸው ለእኛም በኃጢአት ላይ
ድል መንሳት መንፈሳዊ ኃይልን ስጠን እያልን እንጾመዋለን፡፡
✔ በጌታ ጾም ላይ እንዲጾም የሆነበት ምክንያት ጾሙ
የጌታ ጾም በሚጾምበት ወቅት ላይ ስለተጾመ
ቤተክርስቲያናችን አብራ ደንግጋዋለች፡፡
✔ እዚህ ላይ በዚያን ጊዜ ለሕርቃል ሕዝቡ ሱባኤ
ይዞለታል፡፡ ዛሬም እኛ ለቤተክርስቲያን ያደረግነውን በማሰብ
እግዚአብሔር አምላክ ለሕርቃል የሰጠውን በጠላቶቹ ላይ
ድል መንሳትን ለእኛም እንዲሰጠን የምንጠይቅበት ስለሆነ
የመጀመሪያውን ሳምንት በሕርቃል ሰይመን ጾሙን
እንጾማለን፡፡
✔ የእኛ ጠላት የጨለማ ገዥ የሆነው ዲያቢሎስ ነውና
እሱን ደግሞ በጾም እንደምናሸንፈው ጌታችን መድኃኒታችን
ኢየሱስ ክርስቶስ አስተምሮናል፡፡
✔ «ዘወረደ» ማለትም በቀጥታ፣ ቃል በቃል ሲተረጐም
«የወረደ» ማለት ነው፡፡ ይህም በምስጢሩ አምላክ ወልደ
አምላክ ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ለቤዛ ዓለም በቅዱስ ፈቃዱ
ሰው ሆኖ ከሰማየ ሰማያት = ከባሕርይ ልዕልናው በትሕትና
ወርዶ ከቅድስት ድንግል ማርያም መወለዱን የሚያመላክት፣
ይህም የሚታወስበት፣ የሚወሳበት የዐቢይ ጾም አንደኛው
ሳምንት ነው፡፡ 《ዮሐ.3-13》፡፡
✔ ሳምንቱ ሙሴኒ የተባለበትም ምክንያት በዚሁ ሳምንት
መጀመሪያ የሰኞ ዕዝል «ከመዝ ይቤ ሙሴ ፀዓቱ
እምትእይንት» «ሙሴ ከከተማ መውጣቱ እንደዚህ ነው አለ»
ስለሚል እንደዚሁም የዚሁ ዕለት ማለት የሰኞ አቡን «ሙሴኒ
ይቤ በውስተ ኦሪት ምድር ሰናይት» እያለ የሙሴን ታሪክ
ስለሚያጠቃቅስ ሳምንቱ ሙሴኒ ተባለ፡፡
✔ ነቢያትም አርባ አርባ ቀን ጾመው ከአለፉ በኋላ የሙሴ
ሕግና ትንቢተ ነቢያት ፈጻሚ የሆነው ምላካችን እንደ እነሱ
40 ቀንና 40 ሌሊት መጾሙን የሚያስታውስ ነው፡፡
《ዘፀ.24-18》፤ 《1ኛ.ነገ.19-8》፤ 《ማቴ. 4-1-4》፡፡
↪ ወስብሐት ለእግዚአብሔር
↪ ምንጭ፡- ጾምና ምጽዋት
Friday, September 30, 2016
=>+*"+<+>†† መስከረም-21- ††
† መስከረም-21- እንኳን ለንጽሕተ ንጹሓን ቅድስተ ቅዱሳን
ድንግል ማርያም ወላዲተ አምላክ ግሸን ደብረከርቤ
ዳግማዊት ጎልጎታ - የግማደ መስቀሉ መገኛ ታላቅ ክብረ
በዓል በሰላም አደረሳችሁ!
† ግሸን ደብረከርቤ ዳግማዊት ጎልጎታ - የግማደ መስቀሉ
መገኛ †
✔ሼር ✔ሼር
ግሸን ማርያም ደብር በወሎ ክፍለ ሀገር በአምባሰል አውራጃ
ውስጥ የምትገኝ ደብር ናት፤ ይህች ደብር በሐይቅና
በመቅደላ፤ በደላንታ፤ በየጁ መካከልና በበሸሎ ወንዝ አዋሳኝ
በርዋ አንድ ዙሪያውን በገደል የተከከበች አምባ ናት፡፡ በበርዋ
ከተገባ በኋላ ግቢዋ ከላይ ሜዳና መስቀለኛ ቦታ ነው፡፡
በትግራይ እንደ ደብረ ዳሞ በበጌምድር እንደዙር አምባ
በመንዝ እንደ አፍቅራ ናት ፡፡
ወደዚህች ደብር ለመሔድ በረሐ አቋርጦ በሸሎን በመሻገር ፫
ሰዓት መንገድ አቀበት በመውጣት አንድ ቀን ሙሉ ተጉዞ
ማታ ፲፪ ሰዓት ይገባል ፡፡ግሸን ማርያም በፊት ደብረ
እግዚአብሔር ትባል ነበር ፡፡ይህ ደብረ እግዚአብሔር
የሚለው ስያሜም በጻድቁ ንጉሥ ላሊበላ እጅ ከቋጥኝ
ድንጋይ ተፈልፍሎ የተሠራ ቤተ መቅደስ በእግዚአብሔር አብ
ስም ስለነበረ ደብረ እግዚአብሔር ተብሎ የተጠራ ነው፡፡
ከዚያም በዓጼ ድግናዣን ዘመን መንግሥት የሐይቅ
እስጢፋኖስ ገዳም ሲመሠረት ሐይቅ ደብር ነጎድጓድ ተብሎ
ሲሰየም ግሸን የሐይቅ ግዛት ስለሆነች ከደብረ እግዚአብሔር
ደብረ ነጎድጓድ ተብላለች ፡፡
ከዚያም በ ፲፬ኛው መቶ ክፍለ ዘመን ላይ በዓጼ ዘርአ ያዕቆብ
ዘመነ መንግሥት የክርስቶስ ግማደ መስቀሉ ግሸን ገብቶ
ሲቀመጥ ከደብረ ነጎድጓድ ደብረ ከርቤ ተብላለች የደብሩ
አስተዳዳሪም መምህረ እሥራኤል ዘደብረ ከርቤ ይባል
ነበር፡፡ ከደብረ ከርቤ ግሸን ማርያም ተብላለች፡፡
† የግማደ መስቀሉ መምጣት ታሪክ †
ዓለምንና በውስጡ የሚገኘውን ሁሉ ፍጡር ፈጥሮ
የሚገዛውን አምላክ መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስን ቤተ
እሥራኤል በቀራንዮ ላይ በመስቀል ሰቀሉት ፡፡ መድኃኔዓለም
በዕለተ ዓርብ ከቀኔ በዘጠኝ ሰዓት ቅድስት ነፍሱን ከቅድስት
ሥጋው በገዛ ሥልጣኑ ከለየ በኋላ በኋላ ከመስቀሉ አውርደው
ቀበሩት ፡፡በ፫ኛው ቀን ሲነሣ ተሰቅሎ የነበረው የእንጨት
መስቀል ሌት ተቀን በሙሉ ሳያቋርጥ እንደፀሐይ ሲያበራ
በተጨማሪም አጋንንት ሲያባርር ድውይ ሲፈውስ ሙት
ሲያነሣ ቤተ እሥራኤል አይሁድ ቀንተው በዓዋጅ ትልቅ
ጉድጓድ ቆፍረው በመቅበር የቤት ጥራጊና አመድ ጠቅላላ
የቆሻሻ መከማቻ እንዲሆን ወሰኑ፡፡ ከዚያ ዘመን ጀመሮ እስከ
ሦስት መቶ ዘመን ድረስ የተከማቸው ቆሻሻ እንደተራራ ሆነ፡፡
ከዚያ በኋላ የታላቁ ቆስጠንጢኖስ እናት እሌኒ ንግሥት
የተባለች ደግ ሴት የክርስቶስን መስቀል መስከረም ፲፯ ቀን
፫፻፳ ዓ.ም. ላይ በዕጣን ጢስ ምልክት ቁፋሮ አስጀምራ
መጋቢት ፲ ቀን አግኝታ በማውጣት ታላቅ ቤተ መቅደስ
ጎልጎታ ላይ ሠርታ በክብር አስቀመጠችው ይህ መስቀልም
ከዚያ ዘመን ጀምሮ እንደ ፀሐይ እያበራ ድውይ እየፈወሰ
አጋንንት እያባረረ ልዩ ልዩ ተአምራትን እየሠራ ሙት እያነሳ
ዕውር እያበራ ተአምራቱን ቀጠለ፡፡ ይህንንም ከኃያላን
ነገሥታት መካከል የፋርስ ንጉሥ መስቀሉን ማርኮ ፋርስ
ወስዶ አስቀመጠው በዚህ ጊዜ የኢየሩሳሌም ምዕመናን
የሮማውን ንጉሥ ሕርቃልን ዕርዳታ በመጠየቅ እንዲመለስ
አድርገው በኢየሩሳሌም ብዙ ዘመን ሲኖር እንደገና ኃያላን
ነገሥታት ይህን መስቀል እኔ እወስድ እኔ እወስድ እያሉ ጠብ
ፈጠሩ፡፡
በዚህ ጊዜ የኢየሩሳሌም ፤ የቁስጥንጥንያ ፤ የአንጾኪያ ፤
የኤፌሶን ፤ የአርማንያ ፤ የግሪክ ፤ የእስክንድርያ የመሳሰሉት
የሃይማኖት መሪዎች ጠቡን አበረዱት ከዚህም አያይዘው
በኢየሩሳሌም የሚገኘውን የክርስቶስ መስቀል ከ፬ ከፍለው
በዕጣ አድርገው በስምምነት ተካፍለው ከሌሎቹ ታሪካዊ
ንዋያት ጋር በየሀገራቸው ወስደው በክብር አስቀመጡት፡፡
የቀኝ ክንፉ የደረሰው ለአፍሪቃ ስለነበር ከታሪካዊ ንዋያተ
ቅድሳት ጋር በግብጽ የሚገኘው የእስክንድርያ ፓትርያርክ
ተረክቦ ወስዶ በክብር አስቀመጠው፡፡
ይህ ግማደ መስቀልም ለብዙ ዘመን በእስክንድርያ ሲኖር
በግብጽ ያሉ እስላሞች እየበዙ ኃይላቸው እየጠነከረ ሔደ
በእስክንድርያ የሚኖሩትን ክርስቲያኖች ሥቃይ ያጸኑባቸው
ጀመር ክርስቲያኖቹም አንድ ሆነው መክረው ለኢትዮጵያዊ
ዓፄ ዳዊት እንዲህ የሚል መልዕክት ላኩ “ንጉሥ ሆይ! በዚህ
በግብጽ ያሉ እስላሞች መከራ አጽንተውብናልና ኃይልህን
አንሥተህ አስታግሥልን ብለው ጠየቁት” ዳግማዊ ዓፄ
ዳዊትም ለመንፈሳዊ ኃይማኖት ቀንተው የክርስቶስ ፍቅር
አስገድዶአቸው ፳ ሽህ ሠራዊት አስከትለው ወደ ግብፅ ዘመቱ
በዚህ ጊዜ በግብፅ ያሉ ኃያላን ፈሩ ተሸበሩ ንጉሡ ዳግማዊ
ዳዊትም እንዲህ የሚል መልዕክት ለእስላሞች ላኩ በተፈጥሮ
ወንድሞቻችሁ ከሆኑት ክርስቲያኖች ጋር ካልታረቃችሁ
ሀገራችሁን መጥቼ አጠፋዋለሁ የሚል ማስጠንቀቂያ ላኩ ፡፡
የንጉሡ መልዕክት ለእስላሞች እንደደረሳቸው ፈርተው
እንደጥንቱ በየሃይማኖታቸው ፀንተው በሰላም እንዲኖሩ
ከክርስቲያን ወንድሞቻቸው ጋር ታረቁ፡፡
መታረቃቸውን ዳግማዊ ዳዊት ሰሙ በዚህም ጉዳይ ንጉሡ
በጣም ደስ አላቸው እገዚአብሔርንም አመሰገኑ በግብፅ
የሚኖሩ ክርስቲያኖችም ከ፲፪ ሺህ ወቄት ወርቅ ጋር
ደስታቸውን ለኢትዮጵያዊው ንጉሥ ለዳግማዊ ዳዊት
በደብዳቤ አድርገው ላኩላቸው ንጉሡም የደስታውን ደብዳቤ
ተመልከተው ደስ ኣላቸው ፤ ወርቁን ግን መልሰው በመላክ
እንዲህ የሚል ደብዳቤ ፃፉ በግብፅ የምትኖሩ የክርስቶስ
ተከታዮች ሆይ እንኳን ደስ አላችሁ የላካችሁልኝን ፲፪ ሺህ
ወቄት ወርቅ መልሼ ልኬላችኋለሁ የእኔ ዓላማ ወርቅ ፍለጋ
አይደለም የክርስቶስ ፍቅር አስገድዶኝ በተቻለኝ ችግራችሁን
ሁሉ አስወገድኩላችሁ አሁንም የምለምናችሁ በሀገሬ
በኢትዮጵያ ረሀብና ቸነፈር ድርቅ ስለወረደብኝ መድኃኒታችን
ኢየሱስ ክርስቶስ ተሰቅሎበት የነበረውን መስቀልና
የቅዱሳንን አፅም ከሌሎች ክቡራን ዕቃዎች ጋር
እንድትልኩልኝ ነው የሚል ነበር፡፡
በእስክንድርያም ያሉ ምእመናን ይህ መልዕክት እንደደረሳቸው
ከሊቃነ ጳጳሳቱና ከኤጲስ ቆጶሳቱ ጋር ውይይት በማድረግ ይህ
ንጉሥ ታላቅ ክርስቲያን ነው፡፡ ስለዚህ ልቡን ደስ እንዲለው
የፈለገውን የጌታችንን ግማደ መስቀል ከቅዱሳን አጽምና
ንዋየ ቅድሳት ጋር አሁን በመለሰው ፲፪ ወቄት ወርቅ የብርና
የንሐስ የመዳብና የወርቅ ሣጥን አዘጋጅተን እንላክለት ብለው
ተስማምተው በክብር በሥነ ሥርዓት በሠረገላና በግመል
አስጭነው ስናር ድረስ አምጥተው ባስረከቡአቸው ጊዜ
በእጃቸው እያጨበጨቡ በእግራቸው እያሸበሸቡ በግንባራቸው
እየሰገዱ በክብር በደስታ ተቀበሉት ይህም የሆነው መስከረም
፳፩ ቀን ነው፡፡ በኢትዮጵያም ታለቅ ብርሃን ሌት ተቀን ፫
ቀን ሙሉ ሲበራ ሰነበተ፡፡
ግማደ መስቀሉ ወደ መካከለኛው ኢትዮጵያ ሳይደርስ በድንገት
ዓፄ ዳዊት ስናር ላይ አረፉ፡፡ ግማደ መስቀሉም የግድ በዚያው
በስናር መቆየት አስፈለገው፡፡ ከዚህ በኋላ የሟቹ የዳግማዊ
ዳዊት ልጅ ዘርአ ያዕቆብ እንደነገሡ ወደ ሥናር ሔደው
ግማደ መስቀሉን ከሌሎቹ ንዋያተ ቅድሳት ጋር አምጥተው
በመናገሻ ከተማቸው በደብረ ብርሃን ላይ ቤተ መቅደስ
ሠርተው ለማስቀመጥ ሲደክሙ በሕልማቸው አንብር
መስቀልየ በዲበ መስቀል ወዳጄ ዘርአ ያዕቆብ ሆይ
መስቀሌን በመስቀልኛ ቦታ ላይ አስቀምጥ የሚል ሕልም
አዩ ፡፡ ንጉሡም መስቀለኛ ቦታ እየፈለጉ በኢትዮጵያ
አውራጃዎች ሁሉ መስቀለኛ ቦታ በመፈለግ ከብዙ ቦታ ላይ
አስቀምጠውት ነበር ለምሳሌ በሸዋ በደርሄ ማርያም ፤
በመናገሻ ማርያም ፤ በወጨጫ መስቀሉን አሳርፈውት
ነበር፡፡ ነገር ግን የመጨረሻውን ቦታ ያላገኙ በመሆኑ በራዕይ
እየደጋገገመ መስቀሌን በመስቀልኛ ቦታ ላይ አስቀምጥ እያለ
ይነግራቸው ነበር፡፡
ዓፄ ዘርአያዕቆብም ለ፯ ቀናት ያህል ሱባዔ ገቡ በዚያም
የተገለፀላቸው መስቀልኛውን ቦታ የሚመራህ ዓምድ ብርሃን
ይመጣል አላቸው እርሳቸው ከዚያ እንደወጡ መስቀለኛውን
ቦታ የሚመራ ዓምደ ብርሃን ከፊታቸው መጥቶ ቆመ በዚያ
መሪነት ወደ ወሎ ክፍለ ሀገር አምባሰል አውራጃ ውስጥ
ግሸን ከምትባል መርቶ አደረሳቸው ፡፡በርግጥም ይህች ግሽን
የተባለች አምባ ጥበበኛ ሰው እንደቀረፃት የተዋበች
መስቀልኛ ቦታ ሁና ስለአገኟት የልባቸው ስለደረሰ ደስ አላቸው
፡፡ በዚያችም አምባ ታላቅ ቤተ መቅደስ ሠርተው
መስቀሉንና ሌሎች ንዋያተ ቅድሳቱን በየማዕረጋቸው የክብር
ቦታ መድበው አስቀመጧቸው ዘመኑም በ፲፬ ኛው ክፍለ
ዘመን ነው፡፡
ከእስክንድርያ ሀገር ከመስቀሉ ጋር በልዩ ልዩ ሣጥን
ተቆልፈው የመጡትም ዝርዝር:
❖ጌታ በዕለተ ዓርብ ለብሶት የነበረው ቀይ ልብስ ከሮም
የመጣ ከለሜዳው
❖ከአፍርጌ ሀገር የመጣው ሐሞት የጠጣበት ሰፍነጉ
❖ዮሐንስ የሳለው የኲርዓተ ርዕሱ ስዕል
❖ቅዱስ ሉቃስ የሣላቸው የእመቤታችን ስዕሎች
❖ የበርካታ ቅዱሳን አጽምና በኢየሩሳሌም ውስጥ ከልዩ ልዩ
ቅዱሳት መካናት የተቆነጠረ የመሬት አፈር
❖የዮርዳኖስ ውሃ
❖በግብጽ ውስጥ ከሚገኙት ታላላቅ ገዳማት የተቆነጠረ አፈር
፡፡
የነዚህንም ዝርዝር ለኢትዮጵያ ሕዝብና ለግሼን ካህናት
መስከረም ፳፩ ቀን ፩ ሺ ፬፻፵ ዓ.ም. ላይ ተናገሩ ፡፡
በመጀመሪያም ይህ ግማደ መስቀል ከእስክንድርያ ስናር
የገባው መስከረም ፲ ቀን ነው ወደ ኢትዮጵያም የገባው
በመስከረም ፳፩ ቀን ነው፡፡ አሁንም በመጨረሻ ግሸን አምባ
የገባው መስከረም ፳፩ ቀን ሲሆን ቤተ መቅደስ ተሠርቶ
ቅዳሴ ቤቱ የተከበረውና አፄ ዘርዓያዕቆብ ለመላው ኢትዮጵያ
በፅሑፍ በመዘርዘር የገለፁበትም መስከረም ፳፩ ቀን ነው፡፡
ስለዚህ ከዚህች በግሸን ደብር የክርስትና እምነት ያላቸው
የኢትዮጵያ ምእመናን ከበረከተ መስቀሉና ከቅዱሳን አፅም
በረከት ለማገኘት በየዓመቱ መስከረም ፳፩ ቀን እየመጡ
ያከብራሉ፡፡ በዚያም ዘመን የነበሩት የኢትዮጵያ ጳጳሳት
የነበሩት አባ ሚካኤልና አባ ገብርኤል የተባሉ ከንጉሡ ከዓፄ
ዘርአ ያዕቆብ ጋር ሆነው የምህረት ቃል ኪዳን ለመቀበል
በዚህች በግሸን ደብር ሱባዔ ገቡ በሱባዔአቸውም በመጨረሻ
መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ተገልጾ ይህች ቦታ እኔ ተወልጄ
ያደኩባትን ኢየሩሳሌምን ትሁን የተሰቀልኩባትን ቀራንዮን
ትሁን የተቀበርኩባትንም ጎልጎታን ትሁን በዚች ቦታ እየመጣ
የሚማፀነውን ሁሉ ቸርነቴ ትጎበኘዋለች ጠለ ምህረቴንም
አይለይባትም ፤ ከሩቅም ሆነ ከቅርብ መጥቶ የተቀበረ
ኢየሩሳሌም እንደተቀበረ ይሁን የሚል የምህረት ቃል ኪዳን
ተገልጾላቸው በዚህ ለተገኙት ምዕመናን ሁሉ በጽሑፍ ካሰሙ
በኋላ ጠቅላላ የግማደ መስቀሉንና የሌሎቹን ታሪካውያን
ንዋያተ ቅዱሳትንም ዝርዝር ታሪክ የያዘውን መጽሐፈ ጤፉት
ብለው ሰይመው ድንጋጌውን ሁሉ በመዘርዘር ለግሸን
እግዚአብሔር አብ ሰጡ፡፡
አፄ አርዓ ያዕቆብም በዚህ ብቻ ሳይወሰኑ እሌኒ እኅታቸው
የተሰኘችው በእመቤታችን ማርያም ስም ቤተ መቅደስ
እንድትሠራ አዘው የእመቤታችን ማርያም ቤተ ክርስቲያን
ከእግዚአብሔር አብ ቤተ ክርስቲያን አጠገብ አሳንጻ ጥር ፳፩
ቀን ቅዳሴ ቤቱ ተከበረ ዓፄ ዘርአ ያዕቆብም ይህችን ደብር
ደብረ ከርቤ ብለው በመሰየም እንኳንስ ሰው የሠገረ ቆቅ ፤
የበረረ ወፍ እንዳይገደል ዳሯ እሳት መሀሏ ገነት ትሁን ብለው
ደንብና ሥርዓት በጤፉት መጽሐፍ ውስጥ አጽፈዋል፡፡ በዚህ
ምክንያት በየጊዜው የነገሡ የኢትዮጵያ ነገሥታትና የተሾሙ
ጳጳሳት መሳፍንትና መኳንንት ልዩ ልዩ ንዋያተ ቅድሳትንና
መጻሕፍትን የወርቅንና የብርን ሰን ፤ ብርና ጻሕል ጽዋን
መስቀልን የመሳሰሉትን የሰጧት ምዕመናንም በየዓመቱ
መስከረም ፳፩ ቀን በግሸን ማርያም ለመገኘት ከዓመት ወደ
ዓመት እየበረከቱ ሔደዋል፡፡
በመስከረም 10 ፤ መስከረም 17 በዓለ መስቀል እና
መስከረም 21 የግሸን በዓል ታሪክ ከረጅም በአጭሩ ይህንን
ይመስላል ፡፡ ስለዚህ የኢትዮጵያ ምዕመናን የሆናችሁ ሁሉ
ከበረከተ መስቀሉ ለመሳተፍ ወደ ግሸን ገሥግሱ፡፡
የእመቤታችን የቅድስት ድንግል ማርያም አማላጅነት እና
ተራዳኢነት ከሁላችን ጋር ይሁን።
የጌቶች ጌታ የንጉሶች ንጉስ ልዑል እግዚአብሔር ዛሬም
ዘወትርም ስሙ የተመሰገነ ይሁን። ከበረከተ መስቀሉ
ያሳትፈን:: አሜን አሜን አሜን !!!
መልካም በዓል
ምንጭ: ትንሣኤ መጽሔት
መለከት መጽሔት
ድንግል ማርያም ወላዲተ አምላክ ግሸን ደብረከርቤ
ዳግማዊት ጎልጎታ - የግማደ መስቀሉ መገኛ ታላቅ ክብረ
በዓል በሰላም አደረሳችሁ!
† ግሸን ደብረከርቤ ዳግማዊት ጎልጎታ - የግማደ መስቀሉ
መገኛ †
✔ሼር ✔ሼር
ግሸን ማርያም ደብር በወሎ ክፍለ ሀገር በአምባሰል አውራጃ
ውስጥ የምትገኝ ደብር ናት፤ ይህች ደብር በሐይቅና
በመቅደላ፤ በደላንታ፤ በየጁ መካከልና በበሸሎ ወንዝ አዋሳኝ
በርዋ አንድ ዙሪያውን በገደል የተከከበች አምባ ናት፡፡ በበርዋ
ከተገባ በኋላ ግቢዋ ከላይ ሜዳና መስቀለኛ ቦታ ነው፡፡
በትግራይ እንደ ደብረ ዳሞ በበጌምድር እንደዙር አምባ
በመንዝ እንደ አፍቅራ ናት ፡፡
ወደዚህች ደብር ለመሔድ በረሐ አቋርጦ በሸሎን በመሻገር ፫
ሰዓት መንገድ አቀበት በመውጣት አንድ ቀን ሙሉ ተጉዞ
ማታ ፲፪ ሰዓት ይገባል ፡፡ግሸን ማርያም በፊት ደብረ
እግዚአብሔር ትባል ነበር ፡፡ይህ ደብረ እግዚአብሔር
የሚለው ስያሜም በጻድቁ ንጉሥ ላሊበላ እጅ ከቋጥኝ
ድንጋይ ተፈልፍሎ የተሠራ ቤተ መቅደስ በእግዚአብሔር አብ
ስም ስለነበረ ደብረ እግዚአብሔር ተብሎ የተጠራ ነው፡፡
ከዚያም በዓጼ ድግናዣን ዘመን መንግሥት የሐይቅ
እስጢፋኖስ ገዳም ሲመሠረት ሐይቅ ደብር ነጎድጓድ ተብሎ
ሲሰየም ግሸን የሐይቅ ግዛት ስለሆነች ከደብረ እግዚአብሔር
ደብረ ነጎድጓድ ተብላለች ፡፡
ከዚያም በ ፲፬ኛው መቶ ክፍለ ዘመን ላይ በዓጼ ዘርአ ያዕቆብ
ዘመነ መንግሥት የክርስቶስ ግማደ መስቀሉ ግሸን ገብቶ
ሲቀመጥ ከደብረ ነጎድጓድ ደብረ ከርቤ ተብላለች የደብሩ
አስተዳዳሪም መምህረ እሥራኤል ዘደብረ ከርቤ ይባል
ነበር፡፡ ከደብረ ከርቤ ግሸን ማርያም ተብላለች፡፡
† የግማደ መስቀሉ መምጣት ታሪክ †
ዓለምንና በውስጡ የሚገኘውን ሁሉ ፍጡር ፈጥሮ
የሚገዛውን አምላክ መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስን ቤተ
እሥራኤል በቀራንዮ ላይ በመስቀል ሰቀሉት ፡፡ መድኃኔዓለም
በዕለተ ዓርብ ከቀኔ በዘጠኝ ሰዓት ቅድስት ነፍሱን ከቅድስት
ሥጋው በገዛ ሥልጣኑ ከለየ በኋላ በኋላ ከመስቀሉ አውርደው
ቀበሩት ፡፡በ፫ኛው ቀን ሲነሣ ተሰቅሎ የነበረው የእንጨት
መስቀል ሌት ተቀን በሙሉ ሳያቋርጥ እንደፀሐይ ሲያበራ
በተጨማሪም አጋንንት ሲያባርር ድውይ ሲፈውስ ሙት
ሲያነሣ ቤተ እሥራኤል አይሁድ ቀንተው በዓዋጅ ትልቅ
ጉድጓድ ቆፍረው በመቅበር የቤት ጥራጊና አመድ ጠቅላላ
የቆሻሻ መከማቻ እንዲሆን ወሰኑ፡፡ ከዚያ ዘመን ጀመሮ እስከ
ሦስት መቶ ዘመን ድረስ የተከማቸው ቆሻሻ እንደተራራ ሆነ፡፡
ከዚያ በኋላ የታላቁ ቆስጠንጢኖስ እናት እሌኒ ንግሥት
የተባለች ደግ ሴት የክርስቶስን መስቀል መስከረም ፲፯ ቀን
፫፻፳ ዓ.ም. ላይ በዕጣን ጢስ ምልክት ቁፋሮ አስጀምራ
መጋቢት ፲ ቀን አግኝታ በማውጣት ታላቅ ቤተ መቅደስ
ጎልጎታ ላይ ሠርታ በክብር አስቀመጠችው ይህ መስቀልም
ከዚያ ዘመን ጀምሮ እንደ ፀሐይ እያበራ ድውይ እየፈወሰ
አጋንንት እያባረረ ልዩ ልዩ ተአምራትን እየሠራ ሙት እያነሳ
ዕውር እያበራ ተአምራቱን ቀጠለ፡፡ ይህንንም ከኃያላን
ነገሥታት መካከል የፋርስ ንጉሥ መስቀሉን ማርኮ ፋርስ
ወስዶ አስቀመጠው በዚህ ጊዜ የኢየሩሳሌም ምዕመናን
የሮማውን ንጉሥ ሕርቃልን ዕርዳታ በመጠየቅ እንዲመለስ
አድርገው በኢየሩሳሌም ብዙ ዘመን ሲኖር እንደገና ኃያላን
ነገሥታት ይህን መስቀል እኔ እወስድ እኔ እወስድ እያሉ ጠብ
ፈጠሩ፡፡
በዚህ ጊዜ የኢየሩሳሌም ፤ የቁስጥንጥንያ ፤ የአንጾኪያ ፤
የኤፌሶን ፤ የአርማንያ ፤ የግሪክ ፤ የእስክንድርያ የመሳሰሉት
የሃይማኖት መሪዎች ጠቡን አበረዱት ከዚህም አያይዘው
በኢየሩሳሌም የሚገኘውን የክርስቶስ መስቀል ከ፬ ከፍለው
በዕጣ አድርገው በስምምነት ተካፍለው ከሌሎቹ ታሪካዊ
ንዋያት ጋር በየሀገራቸው ወስደው በክብር አስቀመጡት፡፡
የቀኝ ክንፉ የደረሰው ለአፍሪቃ ስለነበር ከታሪካዊ ንዋያተ
ቅድሳት ጋር በግብጽ የሚገኘው የእስክንድርያ ፓትርያርክ
ተረክቦ ወስዶ በክብር አስቀመጠው፡፡
ይህ ግማደ መስቀልም ለብዙ ዘመን በእስክንድርያ ሲኖር
በግብጽ ያሉ እስላሞች እየበዙ ኃይላቸው እየጠነከረ ሔደ
በእስክንድርያ የሚኖሩትን ክርስቲያኖች ሥቃይ ያጸኑባቸው
ጀመር ክርስቲያኖቹም አንድ ሆነው መክረው ለኢትዮጵያዊ
ዓፄ ዳዊት እንዲህ የሚል መልዕክት ላኩ “ንጉሥ ሆይ! በዚህ
በግብጽ ያሉ እስላሞች መከራ አጽንተውብናልና ኃይልህን
አንሥተህ አስታግሥልን ብለው ጠየቁት” ዳግማዊ ዓፄ
ዳዊትም ለመንፈሳዊ ኃይማኖት ቀንተው የክርስቶስ ፍቅር
አስገድዶአቸው ፳ ሽህ ሠራዊት አስከትለው ወደ ግብፅ ዘመቱ
በዚህ ጊዜ በግብፅ ያሉ ኃያላን ፈሩ ተሸበሩ ንጉሡ ዳግማዊ
ዳዊትም እንዲህ የሚል መልዕክት ለእስላሞች ላኩ በተፈጥሮ
ወንድሞቻችሁ ከሆኑት ክርስቲያኖች ጋር ካልታረቃችሁ
ሀገራችሁን መጥቼ አጠፋዋለሁ የሚል ማስጠንቀቂያ ላኩ ፡፡
የንጉሡ መልዕክት ለእስላሞች እንደደረሳቸው ፈርተው
እንደጥንቱ በየሃይማኖታቸው ፀንተው በሰላም እንዲኖሩ
ከክርስቲያን ወንድሞቻቸው ጋር ታረቁ፡፡
መታረቃቸውን ዳግማዊ ዳዊት ሰሙ በዚህም ጉዳይ ንጉሡ
በጣም ደስ አላቸው እገዚአብሔርንም አመሰገኑ በግብፅ
የሚኖሩ ክርስቲያኖችም ከ፲፪ ሺህ ወቄት ወርቅ ጋር
ደስታቸውን ለኢትዮጵያዊው ንጉሥ ለዳግማዊ ዳዊት
በደብዳቤ አድርገው ላኩላቸው ንጉሡም የደስታውን ደብዳቤ
ተመልከተው ደስ ኣላቸው ፤ ወርቁን ግን መልሰው በመላክ
እንዲህ የሚል ደብዳቤ ፃፉ በግብፅ የምትኖሩ የክርስቶስ
ተከታዮች ሆይ እንኳን ደስ አላችሁ የላካችሁልኝን ፲፪ ሺህ
ወቄት ወርቅ መልሼ ልኬላችኋለሁ የእኔ ዓላማ ወርቅ ፍለጋ
አይደለም የክርስቶስ ፍቅር አስገድዶኝ በተቻለኝ ችግራችሁን
ሁሉ አስወገድኩላችሁ አሁንም የምለምናችሁ በሀገሬ
በኢትዮጵያ ረሀብና ቸነፈር ድርቅ ስለወረደብኝ መድኃኒታችን
ኢየሱስ ክርስቶስ ተሰቅሎበት የነበረውን መስቀልና
የቅዱሳንን አፅም ከሌሎች ክቡራን ዕቃዎች ጋር
እንድትልኩልኝ ነው የሚል ነበር፡፡
በእስክንድርያም ያሉ ምእመናን ይህ መልዕክት እንደደረሳቸው
ከሊቃነ ጳጳሳቱና ከኤጲስ ቆጶሳቱ ጋር ውይይት በማድረግ ይህ
ንጉሥ ታላቅ ክርስቲያን ነው፡፡ ስለዚህ ልቡን ደስ እንዲለው
የፈለገውን የጌታችንን ግማደ መስቀል ከቅዱሳን አጽምና
ንዋየ ቅድሳት ጋር አሁን በመለሰው ፲፪ ወቄት ወርቅ የብርና
የንሐስ የመዳብና የወርቅ ሣጥን አዘጋጅተን እንላክለት ብለው
ተስማምተው በክብር በሥነ ሥርዓት በሠረገላና በግመል
አስጭነው ስናር ድረስ አምጥተው ባስረከቡአቸው ጊዜ
በእጃቸው እያጨበጨቡ በእግራቸው እያሸበሸቡ በግንባራቸው
እየሰገዱ በክብር በደስታ ተቀበሉት ይህም የሆነው መስከረም
፳፩ ቀን ነው፡፡ በኢትዮጵያም ታለቅ ብርሃን ሌት ተቀን ፫
ቀን ሙሉ ሲበራ ሰነበተ፡፡
ግማደ መስቀሉ ወደ መካከለኛው ኢትዮጵያ ሳይደርስ በድንገት
ዓፄ ዳዊት ስናር ላይ አረፉ፡፡ ግማደ መስቀሉም የግድ በዚያው
በስናር መቆየት አስፈለገው፡፡ ከዚህ በኋላ የሟቹ የዳግማዊ
ዳዊት ልጅ ዘርአ ያዕቆብ እንደነገሡ ወደ ሥናር ሔደው
ግማደ መስቀሉን ከሌሎቹ ንዋያተ ቅድሳት ጋር አምጥተው
በመናገሻ ከተማቸው በደብረ ብርሃን ላይ ቤተ መቅደስ
ሠርተው ለማስቀመጥ ሲደክሙ በሕልማቸው አንብር
መስቀልየ በዲበ መስቀል ወዳጄ ዘርአ ያዕቆብ ሆይ
መስቀሌን በመስቀልኛ ቦታ ላይ አስቀምጥ የሚል ሕልም
አዩ ፡፡ ንጉሡም መስቀለኛ ቦታ እየፈለጉ በኢትዮጵያ
አውራጃዎች ሁሉ መስቀለኛ ቦታ በመፈለግ ከብዙ ቦታ ላይ
አስቀምጠውት ነበር ለምሳሌ በሸዋ በደርሄ ማርያም ፤
በመናገሻ ማርያም ፤ በወጨጫ መስቀሉን አሳርፈውት
ነበር፡፡ ነገር ግን የመጨረሻውን ቦታ ያላገኙ በመሆኑ በራዕይ
እየደጋገገመ መስቀሌን በመስቀልኛ ቦታ ላይ አስቀምጥ እያለ
ይነግራቸው ነበር፡፡
ዓፄ ዘርአያዕቆብም ለ፯ ቀናት ያህል ሱባዔ ገቡ በዚያም
የተገለፀላቸው መስቀልኛውን ቦታ የሚመራህ ዓምድ ብርሃን
ይመጣል አላቸው እርሳቸው ከዚያ እንደወጡ መስቀለኛውን
ቦታ የሚመራ ዓምደ ብርሃን ከፊታቸው መጥቶ ቆመ በዚያ
መሪነት ወደ ወሎ ክፍለ ሀገር አምባሰል አውራጃ ውስጥ
ግሸን ከምትባል መርቶ አደረሳቸው ፡፡በርግጥም ይህች ግሽን
የተባለች አምባ ጥበበኛ ሰው እንደቀረፃት የተዋበች
መስቀልኛ ቦታ ሁና ስለአገኟት የልባቸው ስለደረሰ ደስ አላቸው
፡፡ በዚያችም አምባ ታላቅ ቤተ መቅደስ ሠርተው
መስቀሉንና ሌሎች ንዋያተ ቅድሳቱን በየማዕረጋቸው የክብር
ቦታ መድበው አስቀመጧቸው ዘመኑም በ፲፬ ኛው ክፍለ
ዘመን ነው፡፡
ከእስክንድርያ ሀገር ከመስቀሉ ጋር በልዩ ልዩ ሣጥን
ተቆልፈው የመጡትም ዝርዝር:
❖ጌታ በዕለተ ዓርብ ለብሶት የነበረው ቀይ ልብስ ከሮም
የመጣ ከለሜዳው
❖ከአፍርጌ ሀገር የመጣው ሐሞት የጠጣበት ሰፍነጉ
❖ዮሐንስ የሳለው የኲርዓተ ርዕሱ ስዕል
❖ቅዱስ ሉቃስ የሣላቸው የእመቤታችን ስዕሎች
❖ የበርካታ ቅዱሳን አጽምና በኢየሩሳሌም ውስጥ ከልዩ ልዩ
ቅዱሳት መካናት የተቆነጠረ የመሬት አፈር
❖የዮርዳኖስ ውሃ
❖በግብጽ ውስጥ ከሚገኙት ታላላቅ ገዳማት የተቆነጠረ አፈር
፡፡
የነዚህንም ዝርዝር ለኢትዮጵያ ሕዝብና ለግሼን ካህናት
መስከረም ፳፩ ቀን ፩ ሺ ፬፻፵ ዓ.ም. ላይ ተናገሩ ፡፡
በመጀመሪያም ይህ ግማደ መስቀል ከእስክንድርያ ስናር
የገባው መስከረም ፲ ቀን ነው ወደ ኢትዮጵያም የገባው
በመስከረም ፳፩ ቀን ነው፡፡ አሁንም በመጨረሻ ግሸን አምባ
የገባው መስከረም ፳፩ ቀን ሲሆን ቤተ መቅደስ ተሠርቶ
ቅዳሴ ቤቱ የተከበረውና አፄ ዘርዓያዕቆብ ለመላው ኢትዮጵያ
በፅሑፍ በመዘርዘር የገለፁበትም መስከረም ፳፩ ቀን ነው፡፡
ስለዚህ ከዚህች በግሸን ደብር የክርስትና እምነት ያላቸው
የኢትዮጵያ ምእመናን ከበረከተ መስቀሉና ከቅዱሳን አፅም
በረከት ለማገኘት በየዓመቱ መስከረም ፳፩ ቀን እየመጡ
ያከብራሉ፡፡ በዚያም ዘመን የነበሩት የኢትዮጵያ ጳጳሳት
የነበሩት አባ ሚካኤልና አባ ገብርኤል የተባሉ ከንጉሡ ከዓፄ
ዘርአ ያዕቆብ ጋር ሆነው የምህረት ቃል ኪዳን ለመቀበል
በዚህች በግሸን ደብር ሱባዔ ገቡ በሱባዔአቸውም በመጨረሻ
መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ተገልጾ ይህች ቦታ እኔ ተወልጄ
ያደኩባትን ኢየሩሳሌምን ትሁን የተሰቀልኩባትን ቀራንዮን
ትሁን የተቀበርኩባትንም ጎልጎታን ትሁን በዚች ቦታ እየመጣ
የሚማፀነውን ሁሉ ቸርነቴ ትጎበኘዋለች ጠለ ምህረቴንም
አይለይባትም ፤ ከሩቅም ሆነ ከቅርብ መጥቶ የተቀበረ
ኢየሩሳሌም እንደተቀበረ ይሁን የሚል የምህረት ቃል ኪዳን
ተገልጾላቸው በዚህ ለተገኙት ምዕመናን ሁሉ በጽሑፍ ካሰሙ
በኋላ ጠቅላላ የግማደ መስቀሉንና የሌሎቹን ታሪካውያን
ንዋያተ ቅዱሳትንም ዝርዝር ታሪክ የያዘውን መጽሐፈ ጤፉት
ብለው ሰይመው ድንጋጌውን ሁሉ በመዘርዘር ለግሸን
እግዚአብሔር አብ ሰጡ፡፡
አፄ አርዓ ያዕቆብም በዚህ ብቻ ሳይወሰኑ እሌኒ እኅታቸው
የተሰኘችው በእመቤታችን ማርያም ስም ቤተ መቅደስ
እንድትሠራ አዘው የእመቤታችን ማርያም ቤተ ክርስቲያን
ከእግዚአብሔር አብ ቤተ ክርስቲያን አጠገብ አሳንጻ ጥር ፳፩
ቀን ቅዳሴ ቤቱ ተከበረ ዓፄ ዘርአ ያዕቆብም ይህችን ደብር
ደብረ ከርቤ ብለው በመሰየም እንኳንስ ሰው የሠገረ ቆቅ ፤
የበረረ ወፍ እንዳይገደል ዳሯ እሳት መሀሏ ገነት ትሁን ብለው
ደንብና ሥርዓት በጤፉት መጽሐፍ ውስጥ አጽፈዋል፡፡ በዚህ
ምክንያት በየጊዜው የነገሡ የኢትዮጵያ ነገሥታትና የተሾሙ
ጳጳሳት መሳፍንትና መኳንንት ልዩ ልዩ ንዋያተ ቅድሳትንና
መጻሕፍትን የወርቅንና የብርን ሰን ፤ ብርና ጻሕል ጽዋን
መስቀልን የመሳሰሉትን የሰጧት ምዕመናንም በየዓመቱ
መስከረም ፳፩ ቀን በግሸን ማርያም ለመገኘት ከዓመት ወደ
ዓመት እየበረከቱ ሔደዋል፡፡
በመስከረም 10 ፤ መስከረም 17 በዓለ መስቀል እና
መስከረም 21 የግሸን በዓል ታሪክ ከረጅም በአጭሩ ይህንን
ይመስላል ፡፡ ስለዚህ የኢትዮጵያ ምዕመናን የሆናችሁ ሁሉ
ከበረከተ መስቀሉ ለመሳተፍ ወደ ግሸን ገሥግሱ፡፡
የእመቤታችን የቅድስት ድንግል ማርያም አማላጅነት እና
ተራዳኢነት ከሁላችን ጋር ይሁን።
የጌቶች ጌታ የንጉሶች ንጉስ ልዑል እግዚአብሔር ዛሬም
ዘወትርም ስሙ የተመሰገነ ይሁን። ከበረከተ መስቀሉ
ያሳትፈን:: አሜን አሜን አሜን !!!
መልካም በዓል
ምንጭ: ትንሣኤ መጽሔት
መለከት መጽሔት
Tuesday, September 13, 2016
ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ነኝ: =>+*"+<+>††† መስከረም 2-መጥምቀ መለኮት ቅዱስ ዮሐንስ †††<+>+"*
አንድ አምላክ በሚሆን በአብ በወልድ በመንፈስ ቅዱስ ስም
አሜን
መስከረም 2-መጥምቀ መለኮት ቅዱስ ዮሐንስ በሰማዕትነት
ያረፈበት
ዕለት ነው፡፡ ይኸውም ጌታችን አስቀድሞ "በመወለዱም
ብዙዎች ደስ
ይላቸዋል" (ሉቃ1:14) በማለት የመጥምቁ መወለድ ለእኛ
የደስታ
ቀናችን መሆኑን ነግሮናል፡፡ ዳግመኛም ጌታችን የመጥምቁን
ክብር
ሲገልጥለት "እውነት እላችኋለሁ ከሴቶች ከተወለዱት መካከል
ከመጥምቁ ዮሐንስ የሚበልጥ ማንም የለም" በማለት
መስክሮለታል፡፡
ማቴ 11:11፣ ሉቃ 7:28፡፡ በዚህም መሠረት ቅዱስ ገድሉ
ላይ
እንደተጠቀሰው ጌታችን አምላካችን መድኃኒታችን ኢየሱስ
ክርስቶስ
ለመጥምቁ ዮሐንስ ዓሥር እጅግ አስደናቂ ቃል የድኅነት
ኪዳኖችን
እንደገባለት ከቅዱስ ገድሉ ላይ ያገኘነውን ቀጥሎ
እንናገራለን፡-
ገድለ ቅዱስ ዮሐንስ መጥምቅ (በጎል ሰከበ ደብረ መንክራት
ሚጣቅ
ቅዱስ አማኑኤል ማኅበረ ሰላም አንድነት ገዳም
ያሳተመው-2003
ዓ.ም)
‹‹እግዚአብሔር ወደ በራክይ ልጅ ወደ ዘካርያስ ልጅ
እንደሚወልድ
ይነግረው ዘንድ የመላእክት አለቃ ቅዱስ ገብርኤልን ላከው፡፡
እርሱም
በመሠዊያው በስተቀኝ በኩል ተገልጦ ለዘካርያስ ታየው፡፡
ለሰይጣን ቀኝ
የለውምና መልአክ ግን ብርሃናዊ የማናዊ ነውና መልአክ
እንደሆነ
ለማጠየቅ በቀኝ በኩል ተገልጦ ታየው፡፡ አንድም ሰው ሁሉ
ወደ የማናዊ
ግብር የሚመለስበት ዘመን ደረሰ ሲል በቀኝ በኩል ታየው፡፡
አንድም
ሰውን ሁሉ መክሮ አስተምሮ ወደ ቀኝ ወደ መንፈስ ቅዱስ
ሥራ
የሚመልስ ልጅ ትወልዳለህ ሲለው በቀኝ በኩል ተገልጦ
ታየው፡፡››
የእግዚአብሔርን ስጦታ በልብ ብቻ በድብቅ መያዝ
እንደሚገባ፡-
‹‹የአካባቢዋ ሰዎችም ሁሉ መካን በመሆኗ አልሳቤጥን ‹ጡተ
ደረቅ፣
ማኅፀንሽም የተዘጋ፣ በረከትን ያጣሽ፣ መርገምንም
የተመላሽ፣ የበቅሎ
ዘመድ፣ ቢወልዷት እንጂ አትወልድ…› እያሉ ይሰድቧት ነበር፡፡
አልሳቤጥም ‹በዚህ ወራት መፀነሷን ባወቀች ጊዜ ስድቤን
ሁሉ ከሰው
ያርቅልኝ ዘንድ እግዚአብሔር በረድኤት በጎበኘኝ ጊዜ እንዲህ
አደረገኝን!› ብላ አምስት ወር ፅንሷን ሠወረች (ለማንም
አልተናገረችም)፡፡ እነርሱም ‹ይህቺ ሴት የበላችው ቂጣ
ቢነፋት ፀነስኩ
ትላለች› ብለው ቢሰድቧት እንጂ ሌላ ረብ (ጥቅም)
ባልነበረው ነበር፡፡
ኤልሳቤጥም ስድስት ወር በሆናት ጊዜ መልአኩ ለቅድስት
ድንግል
ማርያም አምላክን እንደምትወልድ አበሰራት፡፡ ድንግል
ማርያምም
መልአኩ ስለ ኤልሳቤጥ መፀነስ የነገራትን ለማረጋገጥ ወደ
እርሷ
ሄደች፡፡ እመቤታችንም ‹እንዴት ነሽ?› ስትላት ኤልሳቤጥ
በሰማች ጊዜ
በማኅፀኗ ያለው ፅንስ በደስታ ሰገደ፡፡››
መንፈስ ቅዱስ የተለየው ሰው የክርስቶስን አምላክነትና
የድንግል
ማርያምን አማላጅነት ማወቅ አይችልም፡- ‹‹ኤልሳቤጥም
‹እንዴት ነሽ?›
ስትላት የእመቤታችንን ድምፅ በሰማች ጊዜ የፈጠረው
አምላክ
በማርያም ማኅፀን ውስጥ መኖሩን አወቀ፡፡ የዓለሙ
መድኃኒት ፈጣሪው
በድንግል ማርያም ማኅፀን ውስጥ መኖሩን ለማየት
የመጥምቀ መለኮት
ቅዱስ ዮሐንስ ዐይኖች በመንፈስ ቅዱስ ፀጋ በእናቱ ማኅፀን
ውስጥ
የተገለጡ ሆኑ፡፡ የሁለቱም የማኅፀን መጋረጃዎች ሳይገለጡ
ፈጣሪውን
ለማየት የዮሐንስ ዐይኖች በመንፈስ ቅዱስ ፀጋ ተገልጠው
እንደ
መስታዎት ሆኑለት፡፡ የሁለቱም የማኅፀን መጋረጃዎች
ፈጣሪውን ለማየት
የዮሐንስ ዐይኖች አልከለከሉትም፡፡ መልአኩ ለአባቱ
ለዘካርያስ ‹ከእናቱ
ማኅፀን ጀምሮ መንፈስ ቅዱስን የተመላ ይሆናልና› ብሎ
እንደነገረው
በእናቱ ማኅፀን ሆኖ በማርያም ማኅፀን ውስጥ ያለውን
ፈጣሪውን
አየው፡፡ ፈጣሪውንም ለመቀበል ሰገደለት፣ እንደ እንቦሳ
ጥጃም በደስታ
ፈንድቆ ዘለለ፡፡ በእርሱ ላይም የመላው መንፈስ ቅዱስ
በኤልሳቤጥም
ላይ መላባትና እንዲህ ብላ ተናረች፡- ‹ከሴቶች ሁሉ ተለይተሽ
አንቺ
የተባረክሽ ነሽ፣ የማኅፀንሽም ፍሬ የተባረከ ነው፡፡ የጌታዬ
እናት ወደ እኔ
ትመጪ ዘንድ እኔ ምንድነኝ?› አለቻት፡፡››
መጥምቁ ዮሐንስ ምግቡ የበረሃ አንበጣ ነበር›› የሚለው
አነጋገር
ስሕተት ነው፡፡ ብዙ ጊዜ በተለምዶ ሲነገር እንደምንሰማው
መጥምቁ
ዮሐንስ የበረሃ አንበጣ እየተመገበ ይኖር ነበር ይባላል፡፡ ነገር
ግን ቅዱስ
ገድሉ የሚናገረው ቅዱስ ዮሐንስ ይመገብ የነበረው ‹‹የበረሃ
አንበጣ››
ሳይሆን ‹‹አንቦጣ›› ተብላ የምትጠራ አንዲት የበረሃ
ቅጠልንና የጣዝማ
ማርን እንደነበር ነው፡፡ ቅዱስ ገድሉ ላይ የተጻፈውን እንይ፡-
‹‹ዮሐንስና
እናቱ ኤልሳቤጥ ወደ በረሃ ከገቡ አምስት ዓመት በሆናቸው
ጊዜ እርሱ
ዕድሜው ሰባት ዓመት ከመንፈቅ ከሆነው በኋላ እናቱ
ኤልሳቤጥ
ሞተችበትና ብቻውን ከበረሃ ውስጥ ተወችው፡፡ ዮሐንስም
በሰፊዋ በረሃ
ውስጥ በአራዊቶች መካክል ብቻውን ቀረ፡፡ ለዮሐንስ ግን
በእርሱ ላይ
ምንም መጥፎ ነገር ሳያደርጉ የቶራና የአንበሳ፣ የነብርም
ልጆች እንደ
ወንድምና እንደ እኅት ሆኑት፡፡ አራዊቶችም ሁሉ ወዳጅ ሆኑት
እንጂ፡፡
ምግቡም የበረሃ ቅጠል ነው፤ መጠጡም ከተቀመጠባት
ድንጋይ ሥር
የምትፈልቀው ውኃ ነበረች፡፡ ዮሐንስ ሰውነትን
አለምልመው፣ ሥጋን
አለስልሰው፣ ገጽንና ፊትን የሚያሳምሩትን የበረሃ
ቅጠሎችንም
አልተመገበም፡፡ አንቦጣ ከተባለችው ከአንዲት የበረሃ ቅጠልና
ከጣዝማ
ማር በስተቀር ከሚበሉት ምግቦች ሁሉ ዮሐንስ ሕርምተኛ
ሆኖ የተለየ
ነበር›› ይላል ቅዱስ ገድሉ፡፡ እስመ ሕሩም ውእቱ ዮሐንስ
እምኲሉ
መባልዕት ዘእንበለ አሐቲ ዕፅ እንተ ይእቲ አንቦጣ ወመዐረ
ጸደንያ
ባሕቲቱ እንዲል መጽሐፍ፡፡
ዮሐንስ ጌታችንን ሲያጠምቀው ሁለቱ ምን ብለው
እንደተነጋገሩ፡-
‹‹በዚያን ቀን ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በዮሐንስ እጅ
በዮርዳኖስ ወንዝ
ያጠምቀው ዘንድ ከገሊላ ወደ ዮርዳኖስ ወደ ዮሐንስ መጣ፡፡
ዮሐንስም
በእርሱ ላይ አድሮበት ባለው በመንፈስ ቅዱስ ፀጋ ጌታችን ወደ
እርሱ
ሲመጣ ባየው ጊዜ አሰምቶ ጮኸ፤ በታላቅ ቃልም እንዲህ
አለ፡- ‹እኛን
ለማዳን የመጣው የእግዚአብሔር በግ እነሆ፡፡ ነቢያትም ስለ
እርሱ
ትንቢት የተናገሩለት ንጉሠ ነገሥት ይህ ነው፡፡ በዕውነት
ቀዳሚና ተከታይ
የሌለውና ለመንግሥቱም ፍጻሜ የሌለው አምላክ ይህ ነው፡፡›
ዮሐንስም
ይህን ቃል እየተናገረ ሳለ ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ጠርቶ
እንዲህ
አለው፡- ‹ዮሐንስ ሆይ! ስለ እኔ የተጻፈውን ሕግ ሁሉ ትፈጽም
ዘንድ እነሆ
ይገባሃል፤ እነሆ በአየኸው ሁሉ ምስክር ትሆን ዘንድ በአንተ
እጅ
የምጠመቅበት ጊዜ ስለደረሰ አጥምቀኝ› አለው፡፡ ዮሐንስም
ለጌታችን
እንዲህ ብሎ መለሰለት፡- ‹ወደ አንተ መጥቼ መጠመቅ ለእኔ
ይገባኛል
እንጂ እኔ ባሪያህ ሆኜ ሳለሁ በእኔ እጅ ትጠመቅ ዘንድ
ስለምን ወደ እኔ
መጣህ? አንተ ጌታ ሆነህ ይህ ነገር ፈጽሞ አይገባም› አለው፡፡
ጌታችንም ‹ዮሐንስ ሆይ! በአንተ እጅ ስለመጠመቄ ደስ
መሰኘት
ይገባሃል፤ አትፍራም፡፡ አንተ እጅህን በራሴ ላይ ታኖራለህ፤
ሰውነቴንም
እኔ አጠምቃታለሁ፡፡ ዮሐንስ ሆይ! እንቢ አትበለኝ እነሆ
ነቢያት ስለ እኔ
የተናገሩትን ሕግና ትእዛዝን ሁሉ ልፈጽም መጥቻሁና›
አለው፡፡ ጌታችንም
ይህን ቃል ለዮሐንስ ነግሮት ከጨረሰ በኋላ ወደ ዮርዳኖስ
ውኃ ውስጥ
ገባ፡፡ ያንጊዜ ዮርዳኖስ አርባ ክንድ ወደኋላው ተመለልሶ ሸሸ፣
ውኃውም
በእሳት እንዳፈሉት ሆነ፡፡ በጸናችው የጥበቡ ኃይል አዳምን
ከነልጆቹ
ለማዳን ወደዚህ ዓለም ከመጣው ከጌታችን ፊት ዮርዳኖስ ስለ
መሸሿና
ወደ ኋላዋ ስለ መመለሷ ነቢዩ ዳዊት ትንቢት ተናግሮአል፡-
‹አቤቱ
ውኆች አዩህ፣ ውኆችም አይተውህ ፈሩ፡፡› አንቺ ባሕር
የሸሸሽው፣ አንቺ
ዮርዳኖስ ወደ ኋላ የተመለሽው ምን ሆናችኋል? ጌታችንም
ዮርዳኖስን
እንዲህ በማለት ገሠፀው፡- ‹ዮርዳኖስ ሆይ! በጥምቀቴ ጊዜ
አትሽሽ፣
ባለህበት ቦታም ተመልሰህ ቁም› አለው፡፡ ጌታችንም ይህን
ቃል
በተናገረው ጊዜ የነቢዩ ዳዊት ትንቢት ይደርስ ዘንድ ውኃው
ወደ ቦታው
ተመልሶ ቆመ፤ ከጌታችንም ፊት ሰገደ፡፡ ዮሐንስም ዮርዳኖስ
ወደ ኋላዋ
ተመልሳ መሸሿንና በጌታችን ትእዛዝ ወደ ቀድሞ ቦታዋ
ተመልሳ
ከጌታችን ፊት ስትሰግድ ባየና በተመለከተ ጊዜ ፈራ፣ ደነገጠ፣
ታላቅ
መንቀጥቀጥም አደረበት፣ በፊቱም ሰገደለት፡፡ ‹እነሆ አንተ
ጌታዬና
ፈጣሪዬና ነህ እኔ አገልጋይህ ባሪያህ ነኝ፣ አቤቱ ጌታዬ ሆይ!
ይህን ሁሉ
ደካማነቴን ተመልክተህ እጁን በራስህ ላይ ያኖር ዘንድ
ባሪያህን
አታስገድደው› አለው፡፡ ጌታችንም ለዮሐንስ እንዲህ አለው፡-
‹ይህ ለእኛ
ተድላ ደስታ ነውና እውነትን ጽድቅን ሁሉ መፈጸም ይገባናልና
ያዘዝኩህን
አድርግ› አለው፡፡ ‹አንተም መጥምቀ መለኮት ተብለህ
ክብርህ
ይነገራልና እኔም በባሪያው እጅ ተጠመቀ ተብዬ ትሕትናዬ
ይነገራልና›
አለው፡፡ ይህንንም ሲናገረው ዮሐንስ ተወው፡፡ ዮሐንስም
እንዲህ
አለው፡- ‹የአብ ስም በአንተው አለ፣ የወልድ ስም አንተው
ነህ፣ የመንፈስ
ቅዱስም ስም በአንተው ሕልው ሆኖ አለ፡፡ ሌላውን በአንተ
ስም
አጠምቃለሁ፣ አንተን ግን በማን ስም አጠምቃለሁ?›
አለው፡፡ ጌታም
ዮሐንስን እንዲህ እያልክ አጥምቀኝ አለው፡- ‹እንደ
መልከጼዴቅ ሹመት
የዓለሙ ካህን፣ ብርሃንን የምትገልጽ፣ የአብ የባሕርይ ልጅ፣
አቤቱ ይቅር
በለን፣ የዓለምን ኃጢአት የምታስወግደው የእግዚአብሔር በግ
ይቅር
በለን እያልክ አጥምቀኝ› አለው፡፡ ያንጊዜ ዮሐንስ ጌታችን
ኢየሱስ
ክርስቶስን ጥር ዐሥራ አንድ ቀን ከሌሊቱ በአሥር ሰዓት
አጠመቀው፡፡››
አስቀድሞ መሐላ መማል ፈጽሞ ተገቢ እንደልሆነ፡-
‹‹የሄሮድያዳ ልጅ
ንጉሥ ሄሮድስን በዘፈኗ በጣም አድርጋ ስላስደሰተችው
እርሱም በተራው
ሊያስደስታት ፈለገ፡፡ ‹እስከ መንግሥቱ እኩሌታ ድረስም
ቢሆን
የለመነችውን ይሰጣት ዘንድ በሕዝቦቹና በመኳንንቱ ሁሉ ፊት
እንዳይከዳት በፅኑ ቃልኪዳን ማለላት፡፡› እንዲህም እያለ
‹የፈለግሽውን
ጠይቂኝ፣ የመንግሥቴንም እኩሌታ ቢሆን እሰጥሻለሁ ምን
ላድርግልሽ?›
እያለ በመሐላ ባላት ጊዜ በእናቷ ምክር የዮሐንስን አንገት
ቆርጦ
ይሰጣት ዘንድ ለመነችው፡፡ ንጉሥ ሄሮድስም ይህን ልመና
ከአፏ በሰማ
ጊዜ ‹የፈለግሽውን እሰጥሻለሁ› ብሎ በሕዝቡ ፊት ስለማለ
ለሰው
ይምሰል አዘነ፣ ተከዘ፡፡ ኃዘኑም ስለ ዮሐንስ መሞት
አይደለም፣ ዮሐንስን
ሕዝቡ ይወደው ስለነበር እነርሱን ስለ መፍራቱና መሐላ ምሎ
ከዳ
እንዳይባል ነው እንጂ፡፡ ስለ ዮሐንስ አዝኖ ቢሆን ኖሮ
ቀድሞውንም
በግፍ እንዲታሰር ባላደረገው ነበር፡፡ ወንድሞቼ እኅቶቼ ሆይ!
ከመሐላ
የተነሣ መፍራት ይገባችኋል፡፡ ‹የለመንሽውን ሁሉ
እሰጥሻለሁ› ብሎ
ስለማለ ሄሮድስ የዮሐንስን አንገት እንድትቆረጥ አደረገ፡፡
ጌታችን
ኢየሱስ ክርስቶስም በቅዱስ ወንጌል ‹ፈጽማችሁ አትማሉ›
ብሏል፡፡
ከዚህ በኋላ ወታደሮች ሠይፍ ይዘው የዮሐንስን አንገት
ይቆርጡ ዘንድ
ወደ መኅኒ ቤት ሄዱ፡፡ ቅዱስ ዮሐንስም የሄሮድስ ጭፍሮች
ሊገድሉት
እንደመጡ በመንፈስ ቅዱስ ፀጋ ስላወቀ ከጨለማው ቤት
ውስጥ
አንገቱን በመስኮት አውጥቶ እንደሚመቻቸው አድርጎ
ጠበቃቸው፡፡
የሄሮድስን ቃል እንዳያቃልሉ ጭፍሮቹም የመጥምቀ
መለኮት ዮሐንስን
አንገት ስለ መሐላው ቆረጡት፡፡ በመሐላ ምክንያት ባይሆን
ኖሮ ሄሮድስ
መጥምቀ መለኮት ዮሐንስን ባላስገደለው ነበር፡፡ ስለዚህ
ወንድሞቸ
እኅቶች ሆይ! እናንተም ከመሐላ የተነሣ መፍራት ይገባችኋል፣
ፈጽማችሁም መማል የለባችሁም፡፡››
ስካርና ዘፈን ከሚገኙበት ቦታ አጋንንትና ኃጢአት ከዚያ አሉ፡-
‹‹ወንድሞችና እኅቶች ሆይ! አለልክ መብላና መጠጣት ካለበት
ቦታ
እግዚአብሔርን መበደል፣ ማስቀየምና ማስቆጣት
ይገኝበታል፡፡ ስካር
ከሚገኝበት ቦታ አጋንንትና ኃጢአት ከዚያ አሉ፡፡ ስካርና ዘፈን
ከሚገኝበት
ቦታ የእግዚአብሔር መቅሰፍት የፈጣሪያችን ቁጣና በቀል
ይፈጸምበታልና፡፡ እናንተ ሕዝበ ክርስቲያኖች ሆይ! ከስካር፣
ከዘፈንና
ከዝሙት መራቅ ይገባችኋል፡፡ መጥምቀ መለኮት ዮሐንስን
ያስገደለው
ዘፈን፣ ስካርና የዘማ ፍቅር መሆኑን ልብ በማለት መገንዘብ
አለባችሁ፡፡››
መድኃኔዓለም ክርስቶስ ለመጥምቁ ዮሐንስ የተገለጠበት ልዩ
ሁኔታ፡-
‹‹ንጉሥ ሄሮድስ በሞተ ጊዜ እነሆ የእግዚአብሔር መልአክ
በግብፅ አገር
ለዮሴፍ በሕልም ተገልጦ ታየው፡፡ እንዲህም አለው፡- ‹እነሆ
የዚህን
ሕፃን ነፍስ የሚሹ ሙተዋልና ተነሥተህ ሕፃኑንና እናቱን ይዘህ
ወደ
ምድረ እስራኤል ተመለስ› አለው፡፡ ዮሴፍም ተነሥቶ ሕፃኑንና
እናቱን ይዞ
ወደ ምድረ እስራኤል ገባ፡፡ ‹ልጄ ናዝራዊ ይባላል› ተብሎ
በነቢይ
የተነገረው ቃል ይደርስ ይፈዘም ዘንድ መጥቶ ናዝሬት
በምትባል አገር
ተቀመጠ፡፡ ለሞት ይፈልገው የነበረው የተረገመ ከሐዲ
ሄሮድስ ከሞተ
በኋላ ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ከእናቱ ከድንግል ማርያም ጋር
ከምድረ
ግብፅ ተመልሶ በናዝሬት ተቀምጦ ሳለ እነሆ የዕድሜ ባለፀጋ
የሆነችው
የዮሐንስ እናት ክብርት ኤልሳቤጥ ልጇን ዮሐንስን ይዛው ወደ
ደብረሲና
በረሃ ከገቡ ከአምስት ዓመት በኋላ ዐረፈች፡፡ ዮሐንስም በእናቱ
አስክሬን
አጠገብ ተቀምጦ በእጅጉ እያዘነ መሪር ልቅሶንም እያለቀሰ
ሳለ
የተሸሸገውን ሁሉ የሚያውቅ ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ
ክርስቶስ
የኤልሳቤጥን መሞት፣ እናቱም ስለሞተችበት ዮሐንስ
ብቻውን ከበረሃ
ውስጥ ተቀምጦ እያለቀሰ መሆኑን ዐወቀ፡፡
ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ የኤልሳቤጥን
መሞት፣ የወዳጁ
ዮሐንስ ኃዘንና ማልቀስ ባወቀ ጊዜ እርሱም በናዝሬት ሆኖ
ያለቅስ
ጀመር፡፡ እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያምም ልጇ
ወዳጅዋ ሲያለቅስ
ባየችው ጊዜ ‹ልጄ ወዳጄ ሆይ! ምን ሆንክ? ስለምንስ
ታለቅሳለህ?› ብላ
ጠየቀችው፡፡ ጌታችንም ለቅድስት እናቱ እንዲህ በማለት
መለሰላት፡-
‹እነሆ ወገንሽ የሆነችው ኤልሳቤጥ ዐረፈች፤ ዮሐንስንም
ብቻውን ከበረሃ
ውስጥ ተወችው፡፡ ዮሐንስም ሕፃን ስለሆነ የሚያደርገውን
አጥቶ በእናቱ
አስክሬን አጠገብ ከፊት ለፊቷ ተቀምጦ በመረረ ኃዘን
ያለቅሳል፡፡ እናቴ
ሆይ እኔም ዘመድሽ የሆነ የዮሐንስን ልቆሶ ስላወቅሁኝና
የእርሱም ኃዘን
ስለተሰማኝ የማለቅሰው ስለዚህ ነው› አላት፡፡ በድንጋሌ ሥጋ
በድንጋሌ
ነፍስ የፀናች እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያምም
የኤልሳቤጥን
መሞት በሰማች ጊዜ በጣም ምርር ብላ አለቀሰች፡፡
ያንጊዜም ብርሕት
ደመና መጥታ ከፊታቸው ቆመች፤ ፈጥናም ተሸከመቻቸውና
ኤልሳቤጥ
ከሞተችበት ዮሐንስም ካለበት ቦታ ከደብረሲና በረሃ ውስጥ
ወስዳ
አደረሰቻቸው፡፡ ዮሐንስም ባያቸው ጊዜ ደነገጠ፡፡ ከዚያ በፊት
ሰው አይቶ
ስለማያውቅ የእናቱን አስክሬን ብቻውን ትቶ ወደ ጫካ ሸሸ፡፡
ጌታችን
ኢየሱስ ክርስቶስም የዮሐንስን ፍርሃት አራቀለትና እንዲህ
አለው፡- ‹እኛን
ከማየትህ የተነሣ አትፍራ፣ አትደንግጥም፤ አይዞህ እነሆ
የእናትህ
ዘመዶች ማርያምና ሰሎሜ በእናትህ አስክሬን ላይ መልካም
ነገር
ሊያደርጉ መጥተዋልና ና ወደ እኛ ቅረብ› አለው፡፡ ዮሐንስም
ይህን ቃል
ከጌታችን አንደበት በሰማ ጊዜ ወደኋላው ተመለሰ፡፡
ከመሬትም ላይ
ወድቆ ለጌታችን ለኢየሱስ ክርስቶስ ሰገደለት፡፡
ጌታችንም እመቤታችን ማርያምንና ሰሎሜን እንዲህ ብሎ
አዘዛቸው፡-
‹በጠማው ጊዜ ለእርሷ ይጠጣ ዘንድ ለዮሐንስ በፈለቀችለት
ውኃ
የኤልሳቤጥን ሥጋ አጥባችሁ ገንዙ› አላቸው፡፡
እንዳዘዛቸውም
የኤልሳቤጥን አስክሬን አጥበው ገነዙት፡፡ ጌታችንም ቅዱስ
ሚካኤልንና
ቅዱስ ገብርኤልን ይመጡ ዘንድ አዘዛቸው፡፡ እነርሱም
ፈጥነው እንደ
ዐይን ጥቅሻ ከሰማይ ወርደው መጡና ከጌታችን ፊት ቆሙ፡፡
ጌታችንም
‹የኤልሳቤጥን ሥጋ የሚቀበርበትን መሬት ቆፍሩ› አላቸው፡፡
ቅዱስ
ሚካኤልንና ቅዱስ ገብርኤልንም መቃብሩን ይቆፍሩ ዘንድ
ጀመሩ፡፡
ጌታችን ዘካርያስንና ስምዖንን በአካለ ነፍስ ከሰማይ መጥተው
በኤልሳቤጥ አስክሬን ላይ ጸሎተ ፍትሐቱን ያደርሱ ዘንድ
አዘዛቸው፡፡
እነርሱም የኤልሳቤጥ አስክሬን ካለበት ቦታ ላይ ቅዱስ
ሚካኤልና ቅዱስ
ገብርኤል፣ እመቤታችን ማርያምና ሰሎሜ ከጌታችን ፊት
ቆመው ሳለ
ስምዖንና ዘካርያስ በአስክሬኑ አጠገብ ቆመው ጸሎተ
ፍትሐቱን ያደርሱ
ጀመር፡፡ ጸሎተ ፍትሐቱንም በጨረሱ ጊዜ መላእክት
በቆፈሩት መቃብር
ውስጥ ቀበሩዋትና የስምዖንና የዘካርያስ ነፍስ ወደነበረችበት
ቦታዋ
ተመለሰች፡፡ ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስም የኤልሳቤጥን
መቃብር
በትእምርተ መስቀል አምሳል ደፈነው፡፡ ኤልሳቤጥም
ያረፈችበት ዕለት
የካቲት አሥራ ስድስት ቀን ሆነ፡፡
ከዚህ በኋላ ዮሐንስን ብቻውን ከበረሃ ውስጥ ትተውት ጌታችን
ኢየሱስ
ክርስቶስ ከእመቤታችን ጋር ወደ ናዝሬት ለመመለስ
ከደመናዋ ላይ
ተሣፍሮ ተነሣ፡፡ ያንጊዜም ክብርት እመቤታችን ልጇን
እንዲህ አለችው፡-
‹ጌታዬና አምላኬ ፈጣሪዬ ሆይ! ስለምን ዮሐንስን ብቻውን
ከበረሃ
ውስጥ ትተወዋለህ? እንዴትስ ትተነው እንሄዳለን? ወደዚህ
ቦታ ይዛው
የሸሸችው እናቱ ጥላው ሞታ በመቃብር ውስጥ ተቀብራለች
ከእኛ ጋር
ይዘነው እንሂድ እንጂ› አለችው፡፡ ዳግመኛም እመቤታችን
እንዲህ
አለችው፡- ‹ነፍስ ያለወቀ ሕፃን ስላሆነ አራዊት ይበሉታልና
ይዘነው መሄድ
አለብን› አለችው፡፡ ጌታችንም ለቅድስት እናቱ እንዲህ
በማለት
መለሰላት፡- ‹በመምህርነት ወጥቶ ለእስራኤል ታይቶ
እስከሚያስተምር
ድረስ የሰማያዊው አባቴ ፈቃድ በበረሃ ውስጥ ብቻውን
እንዲኖር ነው፡፡
አንቺ ብቻውን እንዴት ከበረሃ ይኖራል ትያለሽ፤ አራዊቶች
እንዳይጣሉት
ሊቀ መላእክት ቅዱስ ገብርኤል ከእርሱ አይለይም፡፡
በፈለገው ነገር ሁሉ
እንዲራዱትና እንዲታዘዙለት መላእክተ ብርሃንን አዝለታለሁ፡፡
ብርሃናዊው
መልአክ ገብርኤልም ሰማያዊ ሕብስትን ለምግቡ
ያመጣለታል፤
በጠማውም ጊዜ እንደ ወተት የነጣችውን፣ እንደ ወለላ
ማርም
የጣፈጠችውን ውኃ ከኤዶም ገነት ያመጣለታል፡፡ ይህችንም
እርሱ
ካለበት ድንጋይ ሥር የምትፈልቀውን ውኃ እንደ እናቱ ጡት
ለአፉ
የጣፈጠች አደርግለታለሁ፡፡ አንቺ ብቻውን እንዴት በበረሃ
ውስጥ ይኖራል
ትያለሽ፤ እስከ ዛሬ ድረስም የጠበቅሁት እኔ ነኝ፣ ሌላ ማን
ጠበቀው
ብለሽ ነው? እኔ አይደለሁምን? ወዳጄ ዮሐንስን ሰማያዊው
አባቴ ከዚህ
ዓለም ፍጥረት ሁሉ በጣም አብልጦ ይወደዋል፡፡ አባቱ
ዘካርያስም
በሥጋው ቢሞት በነፍሱ ሕያው ስለሆነ ዮሐንስን ለማጽናናት
በአካለ
ነፍስ ከእርሱ እንዳይለየው አደርጋለሁ፡፡ እናቱ አልሳቤጥም
በሥጋዋ
ብትሞት በነፍሷ ሕያዊት ስለሆነች ታጽናናው ዘንድ በነፍሷ
በፍጹም
ከእርሱ እንዳትለየው አደርጋለሁ፡፡ ዮሐንስን የተሸከመች
ማኅፀን ንዕድ፣
ክብርት ስለሆነች በሥጋዋ ውስጥ መጥፎ ሽታ፣ ክፉ መዓዛ
አይገኝባት፣
በመቃብሯም ውስጥ ትሎች አይገኙበት፡፡ ድንግል እናቴ ሆይ!
አንቺ እኔን
ፀንሰሽ ሳለሽ ወደ ኤልሳቤጥ በሄድሽ ጊዜ በእጇ ይዛ ጨብጣ፣
በአፏ
በሳመችሽ ጊዜ እንዲህ ብላ ትንቢት ተናግራለች፡፡ ‹አንቺ
ከሴቶች ሁሉ
ተለይተሽ የተባረክሽ ነሽ፤ የማኅፀንሽም ፍሬ የተባረከ ነው፤
የጌታዬ እናቱ
ወደ እኔ ትመጪ ዘንድ እኔ ምንድነኝ? ከእግዚአብሔር
አግኝተው
የነገሩሽን ቃል ይደረጋል ብለሽ የተቀበልሽ አንቺ ብፅዕት ነሽ፣
ክብርት ነሽ›
ብላ ስላመሰገነችሽ እንኳን ሥጋዋ ሊፈርስ ይቅርና መግነዟም
አይለወጥም፤ መቃብሯም አይጠፋም፤ ነፍሷንም ከሥጋዋ ጋር
እንድትኖር
አደርጋታለሁ፡፡› ይህን የመሰለ ነገር ስለ ወዳጁ ዮሐንስ
ለድንግል እናቱ
ነግሯት ለጨረሰ በኋላ ዮሐንስን ከበረሃ ውስጥ ትተውት
በደመና ላይ
ተጭነው ወደ ናዝሬት ተመለሱ፡፡››
መድኃኔዓለም ክርስቶስ ለመጥምቁ ዮሐንስ የሰጠው ልዩ
ቃልኪዳን፡-
1. ‹‹…ከሚበላውና ከሚጠጣው ከፍሎ በስምህ ለነዳያን
ለሰጠ ሥጋዬን
ደሜን እሰጠዋለሁ፤ በሃይማኖት ፀንቶ፣ በምግባር ሠፍቶ
ሥጋዬን ደሜን
እንዲቀበል አደርገዋለሁ፤ ለሥጋዬ ለደሜ የሚያበቃ ሥራ
እንዲሠራ
አደርገዋለሁ፤ እስከ ሃምሣ አምስት ትውልድም ድረስ
እምረዋለሁ፡፡››
2. ‹‹ሰው ሁሉ ወደ ሥጋዊ ተግባርም ሆነ ወደ መንፈሳዊ
ተግባርም
ቢሆን ሲሄድ ‹ይህ የመጥምቀ መለኮት ዮሐንስ ቤተክርስቲያን
ነው› ብሎ
ቅጽሩን፣ ገራገሩን ቢሳለም የተሳለመው ሰው ቢኖር እኔ
መንበረ
መንግሥቴን አሳልመዋለሁ፡፡ የገድልህንም መጽሐፍ
የተሳለመ ቢኖር እኔ
መንበረ መንግሥቴን አሳልመዋለሁ፡፡››
3. ‹‹ከቤተክርስቲያንህ የተቀበረውን ሰው ከመከራ ሥጋ፣
ከሲኦል እሳት
አድነዋለሁ፤ እኔ ከተቀበርኩበት ኢየሩሳሌም ሄዶ ከእኔ
መቃብር ውስጥ
እንደተቀበረ አደርገዋለሁ፡፡››
4. ‹‹ቤተክርስቲያንህ ከታነፀችበት፣ ስምህ ከሚጠራበት፣
መታሰቢያህ
ከሚደረግበት፣ የተአምርህ ዜና ከሚነገርበት፣ የገድልህ
መጽሐፍ ተነቦ
ከሚተረጎምበት፣ እኔ በረድኤት ከዚያ እገኛለሁ፤ ከዚያ ቦታ
አልለይም፡፡
የገድልህ መጽሐፍ ከሚተረጎምበት ቦታ አጋንንት አይደርሱም፤
ከዚያ ቦታ
ሰይጣናት ይርቃሉ፡፡››
5. ‹‹የገድልህ የተአምርህ መጽሐፍ የተነበበትን ውኃ እኔ
እንደተጠመቅሁበት እንደ ማየ ዮርዳኖስ አደርገዋለሁ፡፡
የገድልህ
መጽሐፍ በተነበበት ውኃ የተጠመቀበት ሰው ቢኖር የሰማንያ
ዓመት
ኃጢአቱን አስተሠርይለታለሁ፤ ወንዱን የአርባ ቀን፣ ሴቷን
የሰማንያ ቀን
ሕጻን አደርጋቸዋለሁ፤ እኔ በተጠመቅሁበት ማየ ዮርዳኖስ
እንደተጠመቀ
ሆኖለት ከኃጢአቱ ይነጻል፡፡››
6. ‹‹ሰውም ሆነ እንስሳ ቢታመም በጽኑ እምነት
ይደረግልኛል ብሎ
አምኖ ያለ ጥርጥር ውኃ አቅርቦ የገድልህን መጽሐፍ በላዩ
ላይ አንብቦ
የተነበበበትን ውኃ ቢታጠብበት ወይም ቢጠጣ ያለ ጥፋት
ፈጥኖ
ከደዌው ይፈወሳል፡፡››
7. ‹‹የገድልህ መጽሐፍ የተነበበትን ማየ ጸሎት በቤቱ ውስጥ
ቢረጭ
ከዚያ ቤት በረከቴን እመላበታለሁ፤ ተድላን፣ ደስታን፣ ጥጋብን
በዚያ ቤት
አሳድራለሁ፤ እስከ ዘለዓለም ድረስ በቤቱ ውስጥ የእህል
መታጣትና
ረሀብ፣ የውኃ ጥማት፣ ተላላፊ በሽታ አይገባበትም፤ ፈጽሜም
አላመጣበትም፡፡››
8. ‹‹ደስ ብሎት በተድላ በደስታ በዓለህን ያከበረውን ሰው ሁሉ
በቅዱሳን መላእክቶቼና በሰማያዊ አባቴ በአብ ማሕያዊ
በሚሆን
በመንፈስ ቅዱስ ፊት እኔ ደስ አሰኘዋለሁ፡፡ እነሆ እኔም
ከበዓልህ ቦታ
ላይ አልለይም፤ በዓልህንም ከሚያከብሩት ጋር እኔ
አብሬያቸው
እቀመጣለሁ፤ እስከ ሃምሣ አምስት ትውልድም
እምረዋለሁ፡፡››
9. ‹‹ለቤተክርስቲያንህ ዕጣን፣ ሻማ፣ ጧፍ፣ ልብሰ ተክህኖ፣
መጎናጸፊያ፣
መጋረጃ፣ ነጭ ስንዴ የሰጠ ሰው ቢኖር እስከ ሃምሣ አምስት
ትውልድም
ድረስ እምረዋለሁ፡፡››
10. ‹‹ሥጋዬን ደሜን መቀበል ያልተቻለው ሰው ቢኖር
ለመታሰቢያህ
ዝክር ከተደረገው ፍርፋሪ ይቅመስ፣ ሥጋዬን ደሜን
እንደተቀበለ እኔ
አደርግለታለሁ፡፡ ፍርፋሪውን ባያገኝ እንጀራውና ዳቦው
የተበላበትን
ገበታ፣ ጠላው የተጠጣበትን ፅዋ በምላሱ ይላስ፣ እኔ ኢየሱስ
ቃሌ
የማያብለው ሥጋዬን ደሜን እንደተቀበለ አደርግለታለሁ፤ ስለ
እምነቱ
ሥጋዬን ደሜን ለመቀበል የሚያበቃውና እውነተኛውን
ምግባር የጽድቅ
ሥራ እንዲሠራ አደርገዋለሁ፡፡››
ጌታችን በቅዱስ ወንጌሉ ስለ ዮሐንስ ሲናገር ‹‹ዮሐንስ
የሚያበራ መብራት ነበረ›› ነው ያለው፡፡ ዮሐ 5፡35፡፡
ዳግመኛም ክብሩን ሲገልጥለት "እውነት እላችኋለሁ ከሴቶች
ከተወለዱት መካከል ከመጥምቁ ዮሐንስ የሚበልጥ ማንም
የለም" በማለት መስክሮለታል፡፡ ማቴ 11:11፣ ሉቃ
7:28፡፡ የቅዱስ ዮሐንስ ረድኤት በረከቱ ይደርብን፣ በጸሎቱ
ይማረን፡፡
አሜን
መስከረም 2-መጥምቀ መለኮት ቅዱስ ዮሐንስ በሰማዕትነት
ያረፈበት
ዕለት ነው፡፡ ይኸውም ጌታችን አስቀድሞ "በመወለዱም
ብዙዎች ደስ
ይላቸዋል" (ሉቃ1:14) በማለት የመጥምቁ መወለድ ለእኛ
የደስታ
ቀናችን መሆኑን ነግሮናል፡፡ ዳግመኛም ጌታችን የመጥምቁን
ክብር
ሲገልጥለት "እውነት እላችኋለሁ ከሴቶች ከተወለዱት መካከል
ከመጥምቁ ዮሐንስ የሚበልጥ ማንም የለም" በማለት
መስክሮለታል፡፡
ማቴ 11:11፣ ሉቃ 7:28፡፡ በዚህም መሠረት ቅዱስ ገድሉ
ላይ
እንደተጠቀሰው ጌታችን አምላካችን መድኃኒታችን ኢየሱስ
ክርስቶስ
ለመጥምቁ ዮሐንስ ዓሥር እጅግ አስደናቂ ቃል የድኅነት
ኪዳኖችን
እንደገባለት ከቅዱስ ገድሉ ላይ ያገኘነውን ቀጥሎ
እንናገራለን፡-
ገድለ ቅዱስ ዮሐንስ መጥምቅ (በጎል ሰከበ ደብረ መንክራት
ሚጣቅ
ቅዱስ አማኑኤል ማኅበረ ሰላም አንድነት ገዳም
ያሳተመው-2003
ዓ.ም)
‹‹እግዚአብሔር ወደ በራክይ ልጅ ወደ ዘካርያስ ልጅ
እንደሚወልድ
ይነግረው ዘንድ የመላእክት አለቃ ቅዱስ ገብርኤልን ላከው፡፡
እርሱም
በመሠዊያው በስተቀኝ በኩል ተገልጦ ለዘካርያስ ታየው፡፡
ለሰይጣን ቀኝ
የለውምና መልአክ ግን ብርሃናዊ የማናዊ ነውና መልአክ
እንደሆነ
ለማጠየቅ በቀኝ በኩል ተገልጦ ታየው፡፡ አንድም ሰው ሁሉ
ወደ የማናዊ
ግብር የሚመለስበት ዘመን ደረሰ ሲል በቀኝ በኩል ታየው፡፡
አንድም
ሰውን ሁሉ መክሮ አስተምሮ ወደ ቀኝ ወደ መንፈስ ቅዱስ
ሥራ
የሚመልስ ልጅ ትወልዳለህ ሲለው በቀኝ በኩል ተገልጦ
ታየው፡፡››
የእግዚአብሔርን ስጦታ በልብ ብቻ በድብቅ መያዝ
እንደሚገባ፡-
‹‹የአካባቢዋ ሰዎችም ሁሉ መካን በመሆኗ አልሳቤጥን ‹ጡተ
ደረቅ፣
ማኅፀንሽም የተዘጋ፣ በረከትን ያጣሽ፣ መርገምንም
የተመላሽ፣ የበቅሎ
ዘመድ፣ ቢወልዷት እንጂ አትወልድ…› እያሉ ይሰድቧት ነበር፡፡
አልሳቤጥም ‹በዚህ ወራት መፀነሷን ባወቀች ጊዜ ስድቤን
ሁሉ ከሰው
ያርቅልኝ ዘንድ እግዚአብሔር በረድኤት በጎበኘኝ ጊዜ እንዲህ
አደረገኝን!› ብላ አምስት ወር ፅንሷን ሠወረች (ለማንም
አልተናገረችም)፡፡ እነርሱም ‹ይህቺ ሴት የበላችው ቂጣ
ቢነፋት ፀነስኩ
ትላለች› ብለው ቢሰድቧት እንጂ ሌላ ረብ (ጥቅም)
ባልነበረው ነበር፡፡
ኤልሳቤጥም ስድስት ወር በሆናት ጊዜ መልአኩ ለቅድስት
ድንግል
ማርያም አምላክን እንደምትወልድ አበሰራት፡፡ ድንግል
ማርያምም
መልአኩ ስለ ኤልሳቤጥ መፀነስ የነገራትን ለማረጋገጥ ወደ
እርሷ
ሄደች፡፡ እመቤታችንም ‹እንዴት ነሽ?› ስትላት ኤልሳቤጥ
በሰማች ጊዜ
በማኅፀኗ ያለው ፅንስ በደስታ ሰገደ፡፡››
መንፈስ ቅዱስ የተለየው ሰው የክርስቶስን አምላክነትና
የድንግል
ማርያምን አማላጅነት ማወቅ አይችልም፡- ‹‹ኤልሳቤጥም
‹እንዴት ነሽ?›
ስትላት የእመቤታችንን ድምፅ በሰማች ጊዜ የፈጠረው
አምላክ
በማርያም ማኅፀን ውስጥ መኖሩን አወቀ፡፡ የዓለሙ
መድኃኒት ፈጣሪው
በድንግል ማርያም ማኅፀን ውስጥ መኖሩን ለማየት
የመጥምቀ መለኮት
ቅዱስ ዮሐንስ ዐይኖች በመንፈስ ቅዱስ ፀጋ በእናቱ ማኅፀን
ውስጥ
የተገለጡ ሆኑ፡፡ የሁለቱም የማኅፀን መጋረጃዎች ሳይገለጡ
ፈጣሪውን
ለማየት የዮሐንስ ዐይኖች በመንፈስ ቅዱስ ፀጋ ተገልጠው
እንደ
መስታዎት ሆኑለት፡፡ የሁለቱም የማኅፀን መጋረጃዎች
ፈጣሪውን ለማየት
የዮሐንስ ዐይኖች አልከለከሉትም፡፡ መልአኩ ለአባቱ
ለዘካርያስ ‹ከእናቱ
ማኅፀን ጀምሮ መንፈስ ቅዱስን የተመላ ይሆናልና› ብሎ
እንደነገረው
በእናቱ ማኅፀን ሆኖ በማርያም ማኅፀን ውስጥ ያለውን
ፈጣሪውን
አየው፡፡ ፈጣሪውንም ለመቀበል ሰገደለት፣ እንደ እንቦሳ
ጥጃም በደስታ
ፈንድቆ ዘለለ፡፡ በእርሱ ላይም የመላው መንፈስ ቅዱስ
በኤልሳቤጥም
ላይ መላባትና እንዲህ ብላ ተናረች፡- ‹ከሴቶች ሁሉ ተለይተሽ
አንቺ
የተባረክሽ ነሽ፣ የማኅፀንሽም ፍሬ የተባረከ ነው፡፡ የጌታዬ
እናት ወደ እኔ
ትመጪ ዘንድ እኔ ምንድነኝ?› አለቻት፡፡››
መጥምቁ ዮሐንስ ምግቡ የበረሃ አንበጣ ነበር›› የሚለው
አነጋገር
ስሕተት ነው፡፡ ብዙ ጊዜ በተለምዶ ሲነገር እንደምንሰማው
መጥምቁ
ዮሐንስ የበረሃ አንበጣ እየተመገበ ይኖር ነበር ይባላል፡፡ ነገር
ግን ቅዱስ
ገድሉ የሚናገረው ቅዱስ ዮሐንስ ይመገብ የነበረው ‹‹የበረሃ
አንበጣ››
ሳይሆን ‹‹አንቦጣ›› ተብላ የምትጠራ አንዲት የበረሃ
ቅጠልንና የጣዝማ
ማርን እንደነበር ነው፡፡ ቅዱስ ገድሉ ላይ የተጻፈውን እንይ፡-
‹‹ዮሐንስና
እናቱ ኤልሳቤጥ ወደ በረሃ ከገቡ አምስት ዓመት በሆናቸው
ጊዜ እርሱ
ዕድሜው ሰባት ዓመት ከመንፈቅ ከሆነው በኋላ እናቱ
ኤልሳቤጥ
ሞተችበትና ብቻውን ከበረሃ ውስጥ ተወችው፡፡ ዮሐንስም
በሰፊዋ በረሃ
ውስጥ በአራዊቶች መካክል ብቻውን ቀረ፡፡ ለዮሐንስ ግን
በእርሱ ላይ
ምንም መጥፎ ነገር ሳያደርጉ የቶራና የአንበሳ፣ የነብርም
ልጆች እንደ
ወንድምና እንደ እኅት ሆኑት፡፡ አራዊቶችም ሁሉ ወዳጅ ሆኑት
እንጂ፡፡
ምግቡም የበረሃ ቅጠል ነው፤ መጠጡም ከተቀመጠባት
ድንጋይ ሥር
የምትፈልቀው ውኃ ነበረች፡፡ ዮሐንስ ሰውነትን
አለምልመው፣ ሥጋን
አለስልሰው፣ ገጽንና ፊትን የሚያሳምሩትን የበረሃ
ቅጠሎችንም
አልተመገበም፡፡ አንቦጣ ከተባለችው ከአንዲት የበረሃ ቅጠልና
ከጣዝማ
ማር በስተቀር ከሚበሉት ምግቦች ሁሉ ዮሐንስ ሕርምተኛ
ሆኖ የተለየ
ነበር›› ይላል ቅዱስ ገድሉ፡፡ እስመ ሕሩም ውእቱ ዮሐንስ
እምኲሉ
መባልዕት ዘእንበለ አሐቲ ዕፅ እንተ ይእቲ አንቦጣ ወመዐረ
ጸደንያ
ባሕቲቱ እንዲል መጽሐፍ፡፡
ዮሐንስ ጌታችንን ሲያጠምቀው ሁለቱ ምን ብለው
እንደተነጋገሩ፡-
‹‹በዚያን ቀን ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በዮሐንስ እጅ
በዮርዳኖስ ወንዝ
ያጠምቀው ዘንድ ከገሊላ ወደ ዮርዳኖስ ወደ ዮሐንስ መጣ፡፡
ዮሐንስም
በእርሱ ላይ አድሮበት ባለው በመንፈስ ቅዱስ ፀጋ ጌታችን ወደ
እርሱ
ሲመጣ ባየው ጊዜ አሰምቶ ጮኸ፤ በታላቅ ቃልም እንዲህ
አለ፡- ‹እኛን
ለማዳን የመጣው የእግዚአብሔር በግ እነሆ፡፡ ነቢያትም ስለ
እርሱ
ትንቢት የተናገሩለት ንጉሠ ነገሥት ይህ ነው፡፡ በዕውነት
ቀዳሚና ተከታይ
የሌለውና ለመንግሥቱም ፍጻሜ የሌለው አምላክ ይህ ነው፡፡›
ዮሐንስም
ይህን ቃል እየተናገረ ሳለ ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ጠርቶ
እንዲህ
አለው፡- ‹ዮሐንስ ሆይ! ስለ እኔ የተጻፈውን ሕግ ሁሉ ትፈጽም
ዘንድ እነሆ
ይገባሃል፤ እነሆ በአየኸው ሁሉ ምስክር ትሆን ዘንድ በአንተ
እጅ
የምጠመቅበት ጊዜ ስለደረሰ አጥምቀኝ› አለው፡፡ ዮሐንስም
ለጌታችን
እንዲህ ብሎ መለሰለት፡- ‹ወደ አንተ መጥቼ መጠመቅ ለእኔ
ይገባኛል
እንጂ እኔ ባሪያህ ሆኜ ሳለሁ በእኔ እጅ ትጠመቅ ዘንድ
ስለምን ወደ እኔ
መጣህ? አንተ ጌታ ሆነህ ይህ ነገር ፈጽሞ አይገባም› አለው፡፡
ጌታችንም ‹ዮሐንስ ሆይ! በአንተ እጅ ስለመጠመቄ ደስ
መሰኘት
ይገባሃል፤ አትፍራም፡፡ አንተ እጅህን በራሴ ላይ ታኖራለህ፤
ሰውነቴንም
እኔ አጠምቃታለሁ፡፡ ዮሐንስ ሆይ! እንቢ አትበለኝ እነሆ
ነቢያት ስለ እኔ
የተናገሩትን ሕግና ትእዛዝን ሁሉ ልፈጽም መጥቻሁና›
አለው፡፡ ጌታችንም
ይህን ቃል ለዮሐንስ ነግሮት ከጨረሰ በኋላ ወደ ዮርዳኖስ
ውኃ ውስጥ
ገባ፡፡ ያንጊዜ ዮርዳኖስ አርባ ክንድ ወደኋላው ተመለልሶ ሸሸ፣
ውኃውም
በእሳት እንዳፈሉት ሆነ፡፡ በጸናችው የጥበቡ ኃይል አዳምን
ከነልጆቹ
ለማዳን ወደዚህ ዓለም ከመጣው ከጌታችን ፊት ዮርዳኖስ ስለ
መሸሿና
ወደ ኋላዋ ስለ መመለሷ ነቢዩ ዳዊት ትንቢት ተናግሮአል፡-
‹አቤቱ
ውኆች አዩህ፣ ውኆችም አይተውህ ፈሩ፡፡› አንቺ ባሕር
የሸሸሽው፣ አንቺ
ዮርዳኖስ ወደ ኋላ የተመለሽው ምን ሆናችኋል? ጌታችንም
ዮርዳኖስን
እንዲህ በማለት ገሠፀው፡- ‹ዮርዳኖስ ሆይ! በጥምቀቴ ጊዜ
አትሽሽ፣
ባለህበት ቦታም ተመልሰህ ቁም› አለው፡፡ ጌታችንም ይህን
ቃል
በተናገረው ጊዜ የነቢዩ ዳዊት ትንቢት ይደርስ ዘንድ ውኃው
ወደ ቦታው
ተመልሶ ቆመ፤ ከጌታችንም ፊት ሰገደ፡፡ ዮሐንስም ዮርዳኖስ
ወደ ኋላዋ
ተመልሳ መሸሿንና በጌታችን ትእዛዝ ወደ ቀድሞ ቦታዋ
ተመልሳ
ከጌታችን ፊት ስትሰግድ ባየና በተመለከተ ጊዜ ፈራ፣ ደነገጠ፣
ታላቅ
መንቀጥቀጥም አደረበት፣ በፊቱም ሰገደለት፡፡ ‹እነሆ አንተ
ጌታዬና
ፈጣሪዬና ነህ እኔ አገልጋይህ ባሪያህ ነኝ፣ አቤቱ ጌታዬ ሆይ!
ይህን ሁሉ
ደካማነቴን ተመልክተህ እጁን በራስህ ላይ ያኖር ዘንድ
ባሪያህን
አታስገድደው› አለው፡፡ ጌታችንም ለዮሐንስ እንዲህ አለው፡-
‹ይህ ለእኛ
ተድላ ደስታ ነውና እውነትን ጽድቅን ሁሉ መፈጸም ይገባናልና
ያዘዝኩህን
አድርግ› አለው፡፡ ‹አንተም መጥምቀ መለኮት ተብለህ
ክብርህ
ይነገራልና እኔም በባሪያው እጅ ተጠመቀ ተብዬ ትሕትናዬ
ይነገራልና›
አለው፡፡ ይህንንም ሲናገረው ዮሐንስ ተወው፡፡ ዮሐንስም
እንዲህ
አለው፡- ‹የአብ ስም በአንተው አለ፣ የወልድ ስም አንተው
ነህ፣ የመንፈስ
ቅዱስም ስም በአንተው ሕልው ሆኖ አለ፡፡ ሌላውን በአንተ
ስም
አጠምቃለሁ፣ አንተን ግን በማን ስም አጠምቃለሁ?›
አለው፡፡ ጌታም
ዮሐንስን እንዲህ እያልክ አጥምቀኝ አለው፡- ‹እንደ
መልከጼዴቅ ሹመት
የዓለሙ ካህን፣ ብርሃንን የምትገልጽ፣ የአብ የባሕርይ ልጅ፣
አቤቱ ይቅር
በለን፣ የዓለምን ኃጢአት የምታስወግደው የእግዚአብሔር በግ
ይቅር
በለን እያልክ አጥምቀኝ› አለው፡፡ ያንጊዜ ዮሐንስ ጌታችን
ኢየሱስ
ክርስቶስን ጥር ዐሥራ አንድ ቀን ከሌሊቱ በአሥር ሰዓት
አጠመቀው፡፡››
አስቀድሞ መሐላ መማል ፈጽሞ ተገቢ እንደልሆነ፡-
‹‹የሄሮድያዳ ልጅ
ንጉሥ ሄሮድስን በዘፈኗ በጣም አድርጋ ስላስደሰተችው
እርሱም በተራው
ሊያስደስታት ፈለገ፡፡ ‹እስከ መንግሥቱ እኩሌታ ድረስም
ቢሆን
የለመነችውን ይሰጣት ዘንድ በሕዝቦቹና በመኳንንቱ ሁሉ ፊት
እንዳይከዳት በፅኑ ቃልኪዳን ማለላት፡፡› እንዲህም እያለ
‹የፈለግሽውን
ጠይቂኝ፣ የመንግሥቴንም እኩሌታ ቢሆን እሰጥሻለሁ ምን
ላድርግልሽ?›
እያለ በመሐላ ባላት ጊዜ በእናቷ ምክር የዮሐንስን አንገት
ቆርጦ
ይሰጣት ዘንድ ለመነችው፡፡ ንጉሥ ሄሮድስም ይህን ልመና
ከአፏ በሰማ
ጊዜ ‹የፈለግሽውን እሰጥሻለሁ› ብሎ በሕዝቡ ፊት ስለማለ
ለሰው
ይምሰል አዘነ፣ ተከዘ፡፡ ኃዘኑም ስለ ዮሐንስ መሞት
አይደለም፣ ዮሐንስን
ሕዝቡ ይወደው ስለነበር እነርሱን ስለ መፍራቱና መሐላ ምሎ
ከዳ
እንዳይባል ነው እንጂ፡፡ ስለ ዮሐንስ አዝኖ ቢሆን ኖሮ
ቀድሞውንም
በግፍ እንዲታሰር ባላደረገው ነበር፡፡ ወንድሞቼ እኅቶቼ ሆይ!
ከመሐላ
የተነሣ መፍራት ይገባችኋል፡፡ ‹የለመንሽውን ሁሉ
እሰጥሻለሁ› ብሎ
ስለማለ ሄሮድስ የዮሐንስን አንገት እንድትቆረጥ አደረገ፡፡
ጌታችን
ኢየሱስ ክርስቶስም በቅዱስ ወንጌል ‹ፈጽማችሁ አትማሉ›
ብሏል፡፡
ከዚህ በኋላ ወታደሮች ሠይፍ ይዘው የዮሐንስን አንገት
ይቆርጡ ዘንድ
ወደ መኅኒ ቤት ሄዱ፡፡ ቅዱስ ዮሐንስም የሄሮድስ ጭፍሮች
ሊገድሉት
እንደመጡ በመንፈስ ቅዱስ ፀጋ ስላወቀ ከጨለማው ቤት
ውስጥ
አንገቱን በመስኮት አውጥቶ እንደሚመቻቸው አድርጎ
ጠበቃቸው፡፡
የሄሮድስን ቃል እንዳያቃልሉ ጭፍሮቹም የመጥምቀ
መለኮት ዮሐንስን
አንገት ስለ መሐላው ቆረጡት፡፡ በመሐላ ምክንያት ባይሆን
ኖሮ ሄሮድስ
መጥምቀ መለኮት ዮሐንስን ባላስገደለው ነበር፡፡ ስለዚህ
ወንድሞቸ
እኅቶች ሆይ! እናንተም ከመሐላ የተነሣ መፍራት ይገባችኋል፣
ፈጽማችሁም መማል የለባችሁም፡፡››
ስካርና ዘፈን ከሚገኙበት ቦታ አጋንንትና ኃጢአት ከዚያ አሉ፡-
‹‹ወንድሞችና እኅቶች ሆይ! አለልክ መብላና መጠጣት ካለበት
ቦታ
እግዚአብሔርን መበደል፣ ማስቀየምና ማስቆጣት
ይገኝበታል፡፡ ስካር
ከሚገኝበት ቦታ አጋንንትና ኃጢአት ከዚያ አሉ፡፡ ስካርና ዘፈን
ከሚገኝበት
ቦታ የእግዚአብሔር መቅሰፍት የፈጣሪያችን ቁጣና በቀል
ይፈጸምበታልና፡፡ እናንተ ሕዝበ ክርስቲያኖች ሆይ! ከስካር፣
ከዘፈንና
ከዝሙት መራቅ ይገባችኋል፡፡ መጥምቀ መለኮት ዮሐንስን
ያስገደለው
ዘፈን፣ ስካርና የዘማ ፍቅር መሆኑን ልብ በማለት መገንዘብ
አለባችሁ፡፡››
መድኃኔዓለም ክርስቶስ ለመጥምቁ ዮሐንስ የተገለጠበት ልዩ
ሁኔታ፡-
‹‹ንጉሥ ሄሮድስ በሞተ ጊዜ እነሆ የእግዚአብሔር መልአክ
በግብፅ አገር
ለዮሴፍ በሕልም ተገልጦ ታየው፡፡ እንዲህም አለው፡- ‹እነሆ
የዚህን
ሕፃን ነፍስ የሚሹ ሙተዋልና ተነሥተህ ሕፃኑንና እናቱን ይዘህ
ወደ
ምድረ እስራኤል ተመለስ› አለው፡፡ ዮሴፍም ተነሥቶ ሕፃኑንና
እናቱን ይዞ
ወደ ምድረ እስራኤል ገባ፡፡ ‹ልጄ ናዝራዊ ይባላል› ተብሎ
በነቢይ
የተነገረው ቃል ይደርስ ይፈዘም ዘንድ መጥቶ ናዝሬት
በምትባል አገር
ተቀመጠ፡፡ ለሞት ይፈልገው የነበረው የተረገመ ከሐዲ
ሄሮድስ ከሞተ
በኋላ ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ከእናቱ ከድንግል ማርያም ጋር
ከምድረ
ግብፅ ተመልሶ በናዝሬት ተቀምጦ ሳለ እነሆ የዕድሜ ባለፀጋ
የሆነችው
የዮሐንስ እናት ክብርት ኤልሳቤጥ ልጇን ዮሐንስን ይዛው ወደ
ደብረሲና
በረሃ ከገቡ ከአምስት ዓመት በኋላ ዐረፈች፡፡ ዮሐንስም በእናቱ
አስክሬን
አጠገብ ተቀምጦ በእጅጉ እያዘነ መሪር ልቅሶንም እያለቀሰ
ሳለ
የተሸሸገውን ሁሉ የሚያውቅ ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ
ክርስቶስ
የኤልሳቤጥን መሞት፣ እናቱም ስለሞተችበት ዮሐንስ
ብቻውን ከበረሃ
ውስጥ ተቀምጦ እያለቀሰ መሆኑን ዐወቀ፡፡
ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ የኤልሳቤጥን
መሞት፣ የወዳጁ
ዮሐንስ ኃዘንና ማልቀስ ባወቀ ጊዜ እርሱም በናዝሬት ሆኖ
ያለቅስ
ጀመር፡፡ እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያምም ልጇ
ወዳጅዋ ሲያለቅስ
ባየችው ጊዜ ‹ልጄ ወዳጄ ሆይ! ምን ሆንክ? ስለምንስ
ታለቅሳለህ?› ብላ
ጠየቀችው፡፡ ጌታችንም ለቅድስት እናቱ እንዲህ በማለት
መለሰላት፡-
‹እነሆ ወገንሽ የሆነችው ኤልሳቤጥ ዐረፈች፤ ዮሐንስንም
ብቻውን ከበረሃ
ውስጥ ተወችው፡፡ ዮሐንስም ሕፃን ስለሆነ የሚያደርገውን
አጥቶ በእናቱ
አስክሬን አጠገብ ከፊት ለፊቷ ተቀምጦ በመረረ ኃዘን
ያለቅሳል፡፡ እናቴ
ሆይ እኔም ዘመድሽ የሆነ የዮሐንስን ልቆሶ ስላወቅሁኝና
የእርሱም ኃዘን
ስለተሰማኝ የማለቅሰው ስለዚህ ነው› አላት፡፡ በድንጋሌ ሥጋ
በድንጋሌ
ነፍስ የፀናች እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያምም
የኤልሳቤጥን
መሞት በሰማች ጊዜ በጣም ምርር ብላ አለቀሰች፡፡
ያንጊዜም ብርሕት
ደመና መጥታ ከፊታቸው ቆመች፤ ፈጥናም ተሸከመቻቸውና
ኤልሳቤጥ
ከሞተችበት ዮሐንስም ካለበት ቦታ ከደብረሲና በረሃ ውስጥ
ወስዳ
አደረሰቻቸው፡፡ ዮሐንስም ባያቸው ጊዜ ደነገጠ፡፡ ከዚያ በፊት
ሰው አይቶ
ስለማያውቅ የእናቱን አስክሬን ብቻውን ትቶ ወደ ጫካ ሸሸ፡፡
ጌታችን
ኢየሱስ ክርስቶስም የዮሐንስን ፍርሃት አራቀለትና እንዲህ
አለው፡- ‹እኛን
ከማየትህ የተነሣ አትፍራ፣ አትደንግጥም፤ አይዞህ እነሆ
የእናትህ
ዘመዶች ማርያምና ሰሎሜ በእናትህ አስክሬን ላይ መልካም
ነገር
ሊያደርጉ መጥተዋልና ና ወደ እኛ ቅረብ› አለው፡፡ ዮሐንስም
ይህን ቃል
ከጌታችን አንደበት በሰማ ጊዜ ወደኋላው ተመለሰ፡፡
ከመሬትም ላይ
ወድቆ ለጌታችን ለኢየሱስ ክርስቶስ ሰገደለት፡፡
ጌታችንም እመቤታችን ማርያምንና ሰሎሜን እንዲህ ብሎ
አዘዛቸው፡-
‹በጠማው ጊዜ ለእርሷ ይጠጣ ዘንድ ለዮሐንስ በፈለቀችለት
ውኃ
የኤልሳቤጥን ሥጋ አጥባችሁ ገንዙ› አላቸው፡፡
እንዳዘዛቸውም
የኤልሳቤጥን አስክሬን አጥበው ገነዙት፡፡ ጌታችንም ቅዱስ
ሚካኤልንና
ቅዱስ ገብርኤልን ይመጡ ዘንድ አዘዛቸው፡፡ እነርሱም
ፈጥነው እንደ
ዐይን ጥቅሻ ከሰማይ ወርደው መጡና ከጌታችን ፊት ቆሙ፡፡
ጌታችንም
‹የኤልሳቤጥን ሥጋ የሚቀበርበትን መሬት ቆፍሩ› አላቸው፡፡
ቅዱስ
ሚካኤልንና ቅዱስ ገብርኤልንም መቃብሩን ይቆፍሩ ዘንድ
ጀመሩ፡፡
ጌታችን ዘካርያስንና ስምዖንን በአካለ ነፍስ ከሰማይ መጥተው
በኤልሳቤጥ አስክሬን ላይ ጸሎተ ፍትሐቱን ያደርሱ ዘንድ
አዘዛቸው፡፡
እነርሱም የኤልሳቤጥ አስክሬን ካለበት ቦታ ላይ ቅዱስ
ሚካኤልና ቅዱስ
ገብርኤል፣ እመቤታችን ማርያምና ሰሎሜ ከጌታችን ፊት
ቆመው ሳለ
ስምዖንና ዘካርያስ በአስክሬኑ አጠገብ ቆመው ጸሎተ
ፍትሐቱን ያደርሱ
ጀመር፡፡ ጸሎተ ፍትሐቱንም በጨረሱ ጊዜ መላእክት
በቆፈሩት መቃብር
ውስጥ ቀበሩዋትና የስምዖንና የዘካርያስ ነፍስ ወደነበረችበት
ቦታዋ
ተመለሰች፡፡ ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስም የኤልሳቤጥን
መቃብር
በትእምርተ መስቀል አምሳል ደፈነው፡፡ ኤልሳቤጥም
ያረፈችበት ዕለት
የካቲት አሥራ ስድስት ቀን ሆነ፡፡
ከዚህ በኋላ ዮሐንስን ብቻውን ከበረሃ ውስጥ ትተውት ጌታችን
ኢየሱስ
ክርስቶስ ከእመቤታችን ጋር ወደ ናዝሬት ለመመለስ
ከደመናዋ ላይ
ተሣፍሮ ተነሣ፡፡ ያንጊዜም ክብርት እመቤታችን ልጇን
እንዲህ አለችው፡-
‹ጌታዬና አምላኬ ፈጣሪዬ ሆይ! ስለምን ዮሐንስን ብቻውን
ከበረሃ
ውስጥ ትተወዋለህ? እንዴትስ ትተነው እንሄዳለን? ወደዚህ
ቦታ ይዛው
የሸሸችው እናቱ ጥላው ሞታ በመቃብር ውስጥ ተቀብራለች
ከእኛ ጋር
ይዘነው እንሂድ እንጂ› አለችው፡፡ ዳግመኛም እመቤታችን
እንዲህ
አለችው፡- ‹ነፍስ ያለወቀ ሕፃን ስላሆነ አራዊት ይበሉታልና
ይዘነው መሄድ
አለብን› አለችው፡፡ ጌታችንም ለቅድስት እናቱ እንዲህ
በማለት
መለሰላት፡- ‹በመምህርነት ወጥቶ ለእስራኤል ታይቶ
እስከሚያስተምር
ድረስ የሰማያዊው አባቴ ፈቃድ በበረሃ ውስጥ ብቻውን
እንዲኖር ነው፡፡
አንቺ ብቻውን እንዴት ከበረሃ ይኖራል ትያለሽ፤ አራዊቶች
እንዳይጣሉት
ሊቀ መላእክት ቅዱስ ገብርኤል ከእርሱ አይለይም፡፡
በፈለገው ነገር ሁሉ
እንዲራዱትና እንዲታዘዙለት መላእክተ ብርሃንን አዝለታለሁ፡፡
ብርሃናዊው
መልአክ ገብርኤልም ሰማያዊ ሕብስትን ለምግቡ
ያመጣለታል፤
በጠማውም ጊዜ እንደ ወተት የነጣችውን፣ እንደ ወለላ
ማርም
የጣፈጠችውን ውኃ ከኤዶም ገነት ያመጣለታል፡፡ ይህችንም
እርሱ
ካለበት ድንጋይ ሥር የምትፈልቀውን ውኃ እንደ እናቱ ጡት
ለአፉ
የጣፈጠች አደርግለታለሁ፡፡ አንቺ ብቻውን እንዴት በበረሃ
ውስጥ ይኖራል
ትያለሽ፤ እስከ ዛሬ ድረስም የጠበቅሁት እኔ ነኝ፣ ሌላ ማን
ጠበቀው
ብለሽ ነው? እኔ አይደለሁምን? ወዳጄ ዮሐንስን ሰማያዊው
አባቴ ከዚህ
ዓለም ፍጥረት ሁሉ በጣም አብልጦ ይወደዋል፡፡ አባቱ
ዘካርያስም
በሥጋው ቢሞት በነፍሱ ሕያው ስለሆነ ዮሐንስን ለማጽናናት
በአካለ
ነፍስ ከእርሱ እንዳይለየው አደርጋለሁ፡፡ እናቱ አልሳቤጥም
በሥጋዋ
ብትሞት በነፍሷ ሕያዊት ስለሆነች ታጽናናው ዘንድ በነፍሷ
በፍጹም
ከእርሱ እንዳትለየው አደርጋለሁ፡፡ ዮሐንስን የተሸከመች
ማኅፀን ንዕድ፣
ክብርት ስለሆነች በሥጋዋ ውስጥ መጥፎ ሽታ፣ ክፉ መዓዛ
አይገኝባት፣
በመቃብሯም ውስጥ ትሎች አይገኙበት፡፡ ድንግል እናቴ ሆይ!
አንቺ እኔን
ፀንሰሽ ሳለሽ ወደ ኤልሳቤጥ በሄድሽ ጊዜ በእጇ ይዛ ጨብጣ፣
በአፏ
በሳመችሽ ጊዜ እንዲህ ብላ ትንቢት ተናግራለች፡፡ ‹አንቺ
ከሴቶች ሁሉ
ተለይተሽ የተባረክሽ ነሽ፤ የማኅፀንሽም ፍሬ የተባረከ ነው፤
የጌታዬ እናቱ
ወደ እኔ ትመጪ ዘንድ እኔ ምንድነኝ? ከእግዚአብሔር
አግኝተው
የነገሩሽን ቃል ይደረጋል ብለሽ የተቀበልሽ አንቺ ብፅዕት ነሽ፣
ክብርት ነሽ›
ብላ ስላመሰገነችሽ እንኳን ሥጋዋ ሊፈርስ ይቅርና መግነዟም
አይለወጥም፤ መቃብሯም አይጠፋም፤ ነፍሷንም ከሥጋዋ ጋር
እንድትኖር
አደርጋታለሁ፡፡› ይህን የመሰለ ነገር ስለ ወዳጁ ዮሐንስ
ለድንግል እናቱ
ነግሯት ለጨረሰ በኋላ ዮሐንስን ከበረሃ ውስጥ ትተውት
በደመና ላይ
ተጭነው ወደ ናዝሬት ተመለሱ፡፡››
መድኃኔዓለም ክርስቶስ ለመጥምቁ ዮሐንስ የሰጠው ልዩ
ቃልኪዳን፡-
1. ‹‹…ከሚበላውና ከሚጠጣው ከፍሎ በስምህ ለነዳያን
ለሰጠ ሥጋዬን
ደሜን እሰጠዋለሁ፤ በሃይማኖት ፀንቶ፣ በምግባር ሠፍቶ
ሥጋዬን ደሜን
እንዲቀበል አደርገዋለሁ፤ ለሥጋዬ ለደሜ የሚያበቃ ሥራ
እንዲሠራ
አደርገዋለሁ፤ እስከ ሃምሣ አምስት ትውልድም ድረስ
እምረዋለሁ፡፡››
2. ‹‹ሰው ሁሉ ወደ ሥጋዊ ተግባርም ሆነ ወደ መንፈሳዊ
ተግባርም
ቢሆን ሲሄድ ‹ይህ የመጥምቀ መለኮት ዮሐንስ ቤተክርስቲያን
ነው› ብሎ
ቅጽሩን፣ ገራገሩን ቢሳለም የተሳለመው ሰው ቢኖር እኔ
መንበረ
መንግሥቴን አሳልመዋለሁ፡፡ የገድልህንም መጽሐፍ
የተሳለመ ቢኖር እኔ
መንበረ መንግሥቴን አሳልመዋለሁ፡፡››
3. ‹‹ከቤተክርስቲያንህ የተቀበረውን ሰው ከመከራ ሥጋ፣
ከሲኦል እሳት
አድነዋለሁ፤ እኔ ከተቀበርኩበት ኢየሩሳሌም ሄዶ ከእኔ
መቃብር ውስጥ
እንደተቀበረ አደርገዋለሁ፡፡››
4. ‹‹ቤተክርስቲያንህ ከታነፀችበት፣ ስምህ ከሚጠራበት፣
መታሰቢያህ
ከሚደረግበት፣ የተአምርህ ዜና ከሚነገርበት፣ የገድልህ
መጽሐፍ ተነቦ
ከሚተረጎምበት፣ እኔ በረድኤት ከዚያ እገኛለሁ፤ ከዚያ ቦታ
አልለይም፡፡
የገድልህ መጽሐፍ ከሚተረጎምበት ቦታ አጋንንት አይደርሱም፤
ከዚያ ቦታ
ሰይጣናት ይርቃሉ፡፡››
5. ‹‹የገድልህ የተአምርህ መጽሐፍ የተነበበትን ውኃ እኔ
እንደተጠመቅሁበት እንደ ማየ ዮርዳኖስ አደርገዋለሁ፡፡
የገድልህ
መጽሐፍ በተነበበት ውኃ የተጠመቀበት ሰው ቢኖር የሰማንያ
ዓመት
ኃጢአቱን አስተሠርይለታለሁ፤ ወንዱን የአርባ ቀን፣ ሴቷን
የሰማንያ ቀን
ሕጻን አደርጋቸዋለሁ፤ እኔ በተጠመቅሁበት ማየ ዮርዳኖስ
እንደተጠመቀ
ሆኖለት ከኃጢአቱ ይነጻል፡፡››
6. ‹‹ሰውም ሆነ እንስሳ ቢታመም በጽኑ እምነት
ይደረግልኛል ብሎ
አምኖ ያለ ጥርጥር ውኃ አቅርቦ የገድልህን መጽሐፍ በላዩ
ላይ አንብቦ
የተነበበበትን ውኃ ቢታጠብበት ወይም ቢጠጣ ያለ ጥፋት
ፈጥኖ
ከደዌው ይፈወሳል፡፡››
7. ‹‹የገድልህ መጽሐፍ የተነበበትን ማየ ጸሎት በቤቱ ውስጥ
ቢረጭ
ከዚያ ቤት በረከቴን እመላበታለሁ፤ ተድላን፣ ደስታን፣ ጥጋብን
በዚያ ቤት
አሳድራለሁ፤ እስከ ዘለዓለም ድረስ በቤቱ ውስጥ የእህል
መታጣትና
ረሀብ፣ የውኃ ጥማት፣ ተላላፊ በሽታ አይገባበትም፤ ፈጽሜም
አላመጣበትም፡፡››
8. ‹‹ደስ ብሎት በተድላ በደስታ በዓለህን ያከበረውን ሰው ሁሉ
በቅዱሳን መላእክቶቼና በሰማያዊ አባቴ በአብ ማሕያዊ
በሚሆን
በመንፈስ ቅዱስ ፊት እኔ ደስ አሰኘዋለሁ፡፡ እነሆ እኔም
ከበዓልህ ቦታ
ላይ አልለይም፤ በዓልህንም ከሚያከብሩት ጋር እኔ
አብሬያቸው
እቀመጣለሁ፤ እስከ ሃምሣ አምስት ትውልድም
እምረዋለሁ፡፡››
9. ‹‹ለቤተክርስቲያንህ ዕጣን፣ ሻማ፣ ጧፍ፣ ልብሰ ተክህኖ፣
መጎናጸፊያ፣
መጋረጃ፣ ነጭ ስንዴ የሰጠ ሰው ቢኖር እስከ ሃምሣ አምስት
ትውልድም
ድረስ እምረዋለሁ፡፡››
10. ‹‹ሥጋዬን ደሜን መቀበል ያልተቻለው ሰው ቢኖር
ለመታሰቢያህ
ዝክር ከተደረገው ፍርፋሪ ይቅመስ፣ ሥጋዬን ደሜን
እንደተቀበለ እኔ
አደርግለታለሁ፡፡ ፍርፋሪውን ባያገኝ እንጀራውና ዳቦው
የተበላበትን
ገበታ፣ ጠላው የተጠጣበትን ፅዋ በምላሱ ይላስ፣ እኔ ኢየሱስ
ቃሌ
የማያብለው ሥጋዬን ደሜን እንደተቀበለ አደርግለታለሁ፤ ስለ
እምነቱ
ሥጋዬን ደሜን ለመቀበል የሚያበቃውና እውነተኛውን
ምግባር የጽድቅ
ሥራ እንዲሠራ አደርገዋለሁ፡፡››
ጌታችን በቅዱስ ወንጌሉ ስለ ዮሐንስ ሲናገር ‹‹ዮሐንስ
የሚያበራ መብራት ነበረ›› ነው ያለው፡፡ ዮሐ 5፡35፡፡
ዳግመኛም ክብሩን ሲገልጥለት "እውነት እላችኋለሁ ከሴቶች
ከተወለዱት መካከል ከመጥምቁ ዮሐንስ የሚበልጥ ማንም
የለም" በማለት መስክሮለታል፡፡ ማቴ 11:11፣ ሉቃ
7:28፡፡ የቅዱስ ዮሐንስ ረድኤት በረከቱ ይደርብን፣ በጸሎቱ
ይማረን፡፡
ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ነኝ: =>+*"+<+>††† መስከረም 1-ሊቀ መላእክት ቅዱስ ራጉኤል †††<+>+"*
አንድ አምላክ በሚሆን በአብ በወልድ በመንፈስ ቅዱስ ስም
አሜን
መስከረም 1-ሊቀ መላእክት ቅዱስ ራጉኤል የተሾመበት
ዕለት ነው፡፡
+ ዳግመኛም በዚኽች ዕለት ሐዋርያው ቅዱስ በርተሎሜዎስ
ዕረፍቱ ነው፡፡
+ ታላቁ አባት ጻድቁ አባ ሚልኪ ዕረፍቱ ነው፡፡
+ ጻዲቁ ኢዮብም ከበሽታው የዳነው በዚህች ዕለት ነው፡፡
ጻዲቁ ኢዮብ በፈሳሽ ውኃ ታጥቦ ከደዌው ሁሉ ስለተፈወሰ
ለሰዎች ልማዳቸው ሆኖ ዓመቱ ዞሮ ሲመጣ ፈሳሹ ውኃም
በመላ ጊዜ በአዲስ ውኃ ይጠመቃሉ፣ በእርሱም ይባረካሉ፡፡
ሐዋርያው በርተሎሜዎስ፡- ወንጌልን ይሰብክ ዘንድ ዕጣ
የደረሰው አልዋሕ በሚባል አገር ነው፡፡ ቅዱስ ጴጥሮስ
ሊያደርሰው አብረው ወደ አልዋሕ ሄዱ፡፡ ወደ ከተማው
ለመግባት ምክንያት ፈለጉና ቅዱስ ጴጥሮስ ቅዱስ
በርተሎሜዎስን ‹‹አትክልተኛ ባለሙያ ነው›› ብሎ የወይኑን
ቦታ እንዲጠብቅለት ለአንድ ባለጸጋ መኰንን ባሪያ አድርጎ
ሸጠው፡፡ ባለጸጋውም በርተሎሜዎስን በ30 እስቴታር
ገዝቶት ሄደ፡፡ ቅዱስ ጴጥሮስ ገንዘቡን ደብቆ ለቅዱስ
በርተሎሜዎስ በድብቅ ሰጥቶት እንዲመጸውተው ነግሮት
ወደ ኢየሩሳሌም ተመለሰ፡፡ አልዋሕ ከገባ በኋላ ቅዱስ
በርተሎሜዎስ የወይን ቦታው አለቃ ሆኖ 40 ቀን
ተቀመጠ፡፡ ወንጌሉን ባለመስበኩ በሀዘን እያለቀሰ ጌታችንን
በጸሎት ጠየቀው፡፡ በገንዘቡ ገዝቶት ባሪያው ያደረገው
ባለጸጋውም የወይኑን ቦታ ያይ ዘንድ እንደመጣ መርዘኛ እባብ
ነድፎት ሞተ፡፡ ሕዝቡም ተሰብስቦ ሲያለቅስ በርተሎሜዎስ
ግን ወደ ጌታችን ከጸለየ በኋላ ሄዶ ባለጸጋውን ሰው ከሞት
አስነሣው፡፡ በዚህም ሕዝቡ ሁሉ አምነው ተጠምቀዋል፡፡
በርተሎሜዎስም ወደ ሌሎች አገሮች ሄዶ አስተማረ፡፡
ጌታችን ወደ በርበሮች ዘንድ ሄዶ ወንጌልን እንዲሰብክ
አዘዘው፡፡ ረዳት እንዲሆነውም እንድርያስን ከደቀ መዝሙሩ
ጋር ላከለት፡፡ የሀገሪቱ ሰዎች ግን እጅግ ክፉዎች ነበሩ፡፡
በሐዋርያቱም ፊት በአስማት አስደናቂ ተአምራት እያሳዩ
ትምህርታቸውን የማይቀበሏቸው ሁኑ፡፡ ይህን ጊዜ ጌታችን
ሰውን ከሚበሉ አገር አንዱን ገጸ ከልብ ይታዘዝላቸው ዘንድ
በሚያዙትም ነገር ሁሉ ከትእዛዛቸው እንዳይወጣ አዘዘው፡፡
ሐዋርያትም ወደ በርበሮች አገር ዳግመኛ በገቡ ሰዓት
ይበሏቸው ዘንድ ኃይለኛ አራዊትን አውጥተው ለቀቁባቸው፡፡
ያ ገጸ ከልብም በአራዊቱ ላይ ተነሥቶ እየነጠቀ በላቸው፡፡
ይህንንም የተመለከቱት በርበሮች እጅግ ፈርተው በድንጋጤ
ብቻ የሞቱ አሉ፡፡ በሐዋርያቱም እግር ሥር ወደቁ፡፡
ሐዋርያቱም አስተምረው ካሳመኗቸው በኋላ
አጥምቀዋቸዋል፡፡ ከዚህ በኋላ ቅዱስ በርተሎሜዎስ
እግዚአብሔርን ወደማያውቁ አገሮች ሄዶ ብዙ ተአምራትን
እያደረገ አስተምሮ አጠመቃቸው፡፡ የከሃዲው ንጉሡ
የአግሪጳን ሚስትም ትምህርቱን ሰምታ በጌታችን አመነች፡፡
ንጉሡ አግሪጳም በዚህ እጅግ ተቆጥቶ ቅዱስ
በርተሎሜዎስን ብዙ ካሠቃየው በኋላ አሸዋ በተሞላ ትልቅ
ከረጢት ውስጥ ከቶ ከነሕይወቱ ባሕር ውስጥ እንዲጥሉት
አደረገ፡፡ ምእመናንም ሥጋውን አውጥተው በክብር
ቀብረውታል፡፡ ረድኤት በረከቱ ይደርብን፣ በጸሎቱ ይማረን፡፡
+ + + + + + + + + + + + + + +
አባ ሚልኪ ዘቁልዝም፡- በላይኛው ግብጽ የሚኖሩ ባለጸጋ
ወላጆቻቸው በስዕለት ወለዷቸው፣ ብሉይን ከሐዲስ አጠናቀው
ከተማሩ በኋላ የአባታቸውን ወርቅ ለድኆች ሰጥተው ገዳም
ገብተው መነኩሰው በታላቅ ተጋድሎ ኖሩ፣ የአገረ ገዥውልን
ልጅ ዘንዶ ውጦት ሳለ አባ ሚልኪ ዘንዶውን ጠርቶት ልጁን
ይተፋው ዘንድ አዘዘውና ልጁ ጤነኛ እንደሆነ ከዘንዶው ውስጥ
ወጣ፣ በውስጡ ያደረ ከይሲም በኖ ጠፋ፣ ጻድቁ ቤ/ክ ሲሠሩ
የመሠረቱ ድንጋይ ራሱ በተአምራት እየተፈነቀለ ይተከል
ነበር፣ ለ300 መነኮሳትም አባት ሆነው በተአምራታቸው
የፋርስንና የሮም ሰዎችን አሳመኗቸው፣ ዋሻ ዘግተው ሊኖሩ
በማሉ ጊዜ ሰይጣን መሀላቸውን ሊያፈርስ አስቦ በሮሙ ንጉሥ
ልጅ አድሮ አሳመማትና በአባ ሚልኪ ካልሆነ በቀር
አልወጣም አለ፣ ንጉሡም ልኮባቸው በደመና ተጭነው ሄደው
ልጅቷን ፈውሰው አድሮባት የነበረውን ሰይጣን ገዝተው
አሠሩትና ከንጉሡ ቤት 14 ሰው የማይሸከመውን ድንጋይ
በአንገቱ ላይ አሳስረው አስሸክመውት ሰው ሁሉ እያየው ወደ
ገዳማቸው አስመጡትና ድንጋዩን የበዓታቸው መዝጊያ
አደረጉት፤ ጻድቁ በብርቱ ሲጋደሉ ኖረው የሚያርፉበት ቀን
ከተነገራቸው በኋላ እነ እንጦንስ፣ መቃርስ፣ ሲኖዳ፣ ብሶይ፣
ጳኩሚስ ተገልጠውላቸው ወንድማችን ና ወደ እኛ ብለዋቸው
በሰላም ዐርፈዋል፡፡ ረድኤት በረከታቸው ይደርብን፣
በጸሎታቸው ይማረን፡፡
+ + + + + + + + + + + + + + +
ራጉኤል ሊቀ መላእክት:- ራጉኤል ማለት የብርሃናት አለቃ
ማለት ነው። የብርሃናት አለቃ ሲባል ፀሐይን፣ ጨረቃን እና
ከዋክብትን በማመላለስና ለሰው ልጆች፣ ለአዝርዕት፣
ለእንስሳት፣ ለአራዊት ሁሉ ብርሃንን የሚመግብ ነው ማለት
ነው። አንድም ራጉኤል ማለት የሚበቀል ማለት ነው።
የሚበቀል ነው ማለት በቀል የሚገባው ለጠላት ነው የሰው
ልጅ ጠላት ደግሞ ዲያብሎስ ነው፤ ስለሆነም ቅዱስ ራጉኤል
እግዚአብሔርን አምነው ሕገ እግዚአብሔርን ጠብቀው
በፍርሐተ እግዚአብሔር አምልኮቱን ለሚፈጽሙ ሁሉ ጠላት
ዲያብሎስን የሚያርቅላቸው ወደ እነርሱም ፈጥኖ በመድረስ
የሚታደጋቸው ነው ማለት ነው። ሔኖክ 6:4፡፡ አንድም
ራጉኤል ማለት የኃያላን ኃያል እግዚአብሔር ማለት ነው።
የኃያላን ኃያል ያለው የእግዚአብሔርን ኃያልነት ከምድር
ፍጥረታት ዘንድ ኃያል ከሚባሉት ሁሉ ሊገለጽ የማይችል
ኃያልነቱን ለመግለጽ ኃያልነቱም ከ እስከ የሌለው መሆኑን
ለመግለጽ የተቀመጠ ነው። ስለዚህ እግዚአብሔር ኃያል
የኃያላን ኃያል መሆኑን የሚገልጽ ትርጉም አለው።
አንድም ራጉኤል ማለት ጽኑ እግዚአብሔር ማለት ነው።
የእግዚአብሔር አምላክን ጽኑነት ለማጉላት ሲል ጽኑ አለው።
እግዚአብሔር የማይወላውል የማይዋዥቅ የማይከዳ ነው
ለማለትም ሲል ይህ ስያሜ ተሰጠው። የእግዚአብሔርን ጽናት
የሚያሳይ ትርጉም ያለው ስያሜ ነው። የሊቀ መላእክት
የቅዱስ ራጉኤል አገልግሎት እና ስልጣን፡- እመቤታችን
ቅድስት ድንግል ማርያም ከዚህ ዓለም በ64 ዓመቷ ካረፈች
በኋላ ሥጋዋ ወደ ዕፀ ሕይወት ሲነጠቅ (ሲያርፍ) አብሮ
ለሔደው እና ስጋዋን በእጣን ሲያጥን ለነበረው ለፍቁረ እግዚ
ለቅዱስ ዮሐንስ ኅብስትን የመገበ መልአክ ነው።
በብርሃናት ሁሉ ላይ የሰለጠነ መልአክ ነው። ከአዳም ሰባተኛ
ትውልድ የሆነ በእግዚአብሔር ፊት ግሩም ያማረ ሥራው
የሰመረ እስከዛሬ የሞት ወጥመድ ያልያዘው የሞት ጥላ
ያላረፈበት ነብዩ ሔኖክ "ከቅዱሳን መላእክት አንዱ የሆነ ጸላዒ
ዲያብሎስን የሚበቀለው ራጉኤል በብርሃናት ላይ የሰለጠነ
ነው" ሲል ስለ እርሱ ተናግሯል፡፡
እግዚአብሔር ዓለምን ይቆጣጠር ዘንድ የሾመው ታላቅና
ቅዱስ መልአክ ነው። (ድርሳነ ራጉኤል ዘ ጥቅምት ገጽ 23)
አዲስ ሰማይና አዲስ ምድር ለመተካት ዓለምን የመለወጥ
ሥልጣን የተሰጠው ቅዱስ መልአክ ነው። ከእግዚአብሔር
የጌትነቱ አዳራሽ ይገባና ይወጣ ዘንድ ስልጣን ያለው
ከኪሩቤልና ከሱራፌል ጋር ከፈጣሪ የጌትነት ዙፋን ፊት
የሚቆም ነው። ሎጥን ሚስቱንና ልጆቹን ከእሳተ ጎመራ
ያዳነ የበለአምን እርግማን ወደ በረከት የለወጠ እርሱ ነው።
በቅዱስ ራጉኤል ስነ ሥዕል ላይ የምናየው ይህ ባለ አራት
እራስ ንስር ከአርባእቱ ኪሩቤል አንዱ ገጸ ንስር ነው።
የሥላሴን የጌትነት ዙፋን የሚሸከሙ አርባዕቱ እንስሳት
ናቸው። የሚሸከሙት ሲባል ጫማ የሰውን ልጅ
እንደሚሸከመው እንጂ ችለውትስ አይደለም። እነርሱም
የሰው ገጽ፣ የእንስሳ ገጽ፣ የንስር ገጽ እና የአንበሳ ገጽ ያላቸው
ናቸው። ይህንንም ነብዩ ሕዝቅኤል "ለእያንዳንዱ እንስሳትም
የተለያዩ አራት ገጾች ነበሩት። ይህውም በስተቀኝ በኩል
የእንስሳ መልክ፣ በስተ ግራ የላም ገጽ፣ በበስተ ኋላም የንስር
ገጽ የሚመስሉ ነበሩ" ብሏል ሕዝ 1፡6-13፡፡ ከዚህ
የምንገነዘበው ነገር ቢኖር አራት ገጽ ካላቸው ኪሩቤል
መካከል አንዱ ንስር መሆኑን ነው። ቅዱስ ራጉኤል ደግሞ
የእነዚህ ኪሩቤል አለቃቸው (የጌትነቱ ዙፋን ጠባቂ) በመሆኑ
በዚህ ምክንያት ማለትም እነርሱ ዙፋኑን ተሸካሚ እርሱ
ደግሞ አጠገባቸው መቆሙ መንበሩን ጠባቂ በመሆኑ በዚህ
አይነት የአገልግሎት ድርሻ አብረው ሊሳሉ ችለዋል። ቅዱስ
ያሬድም በድጓው "አርባእቱ እንስሳ አልቄንጥሩ እንደሚባለው
ንስር ፊት ለፊት አይታዩም አንዱም በመራቸው ይሔዳሉ
እነርሱም እያንዳንዳቸው አራት ገጽ ሲኖራቸው ሳያርፉና
ሳይደክሙ የሚያመሰግኑ ናቸው" በማለት ጽፏል። አንድም
መላእክት ነገደ ሱራፌል እና ነገደ ኪሩቤል በመባል
ይከፈላሉ። በነገደ ሱራፌል እነ ቅዱስ ሚካኤል፣ ቅዱስ
ሩፋኤል ወዘተ ሲሆኑ በነገደ ኪሩቤል ደግሞ ቅዱስ ገብርኤል
ቅዱስ ራጉኤል ወዘተ ያጠቃልላል። ስለዚህ ቅዱስ ራጉኤል
ነገዱ ከነገደ ኪሩቤል ነው በዚህም ላይ የነገደ ኪሩቤል
አልቄንጡራ (አራት እራስ ንስር) አለቃቸው ቅዱስ ራጉኤል
ነው። በዚህም ምክንያት አብረው ሊሳሉ ችሏል። አንድም
መላእክትን ሁሉ እንደ እየስራቸው መለያ ስነ ሥዕላቸውን
መሳል ልማድ ነውና። ለምሳሌ ቅዱስ ሚካኤል ከቅድስት
አፎምያ ጋር፣ ቅዱስ ገብርኤል ከሠለስቱ ደቂቅ ጋር፣ ቅዱስ
ዑራኤል ከእዝራ ሱቱኤል ጋር እንደሚሳሉት ሁሉ ማለት
ነው። በዚህም መሰረት ቅዱስ ራጉኤልም ዐቃቤ መንበር
ነውና መንበሩን በሚሸከሙት ኪሩቤል ከሚመሰሉት ንስሮች
ጋር አብረው ሊሳሉ ችለዋል፡፡
ሊቀ መላእክት ቅዱስ ራጉኤል ከአምላክ የተሰጠው ቃል
ኪዳን እግዚአብሔር አምላክ በስሙ ለታመኑት ቅዱሳን፣
ጻድቃን፣ ሰማእታት፣ ሐዋርያት፣ ዘወትር ያለማቋረጥ ስሙን
ለሚጠሩት ቅዱሳን መላእክት ሁሉ ቃል ኪዳን ሰጥቷቸዋል።
የሰጣቸውም ቃል ኪዳን ዘላለማዊ እና ሊሻር የማይችል
ነው። ለመላእክት አለቃ ለቅዱስ ራጉኤልም ይህን ቃል ኪዳን
ሰጥቶታል "የራጉኤል አምላክ ይቅር በለኝ በማለት አንዲት
ቃልስ እንኳን ቢናገር እንደ ወዳጄ እንደ አብርሃም፣ እንደ
ባለሟሌም እንደ ይስሐቅ፣ እንደ አከበርኩትም እንደ ያዕቆብ
ክብርን ባለሟልነትን እሰጠዋለሁ በራሱ ላይም አክሊል
አቀዳጀዋለሁ እረጅም ዘመናት ሰፊ ወራትም እሰጠዋለሁ"
ሲል ቃሉን ሰጥቶታል፡፡ ሊቀ መላእክት ቅዱስ ራጉኤል
መስከረም 1 ቀን ከሊቃነ መላእክት በ4ተኛ ደረጃ
የተሾመበት ዕለት ነው። ግንቦት 1 ቀን ለታላቁ አባት ለሄኖክ
ምሥጢራትን የገለጸበት በዓሉ ነው፡፡ ጥበቃው አይለየን፣
በምልጃው ይማረን፡፡
የቅዱሳን አባቶቻችን አምላክ ሀገራችንን ይጠብቅልን፡፡
አሜን
መስከረም 1-ሊቀ መላእክት ቅዱስ ራጉኤል የተሾመበት
ዕለት ነው፡፡
+ ዳግመኛም በዚኽች ዕለት ሐዋርያው ቅዱስ በርተሎሜዎስ
ዕረፍቱ ነው፡፡
+ ታላቁ አባት ጻድቁ አባ ሚልኪ ዕረፍቱ ነው፡፡
+ ጻዲቁ ኢዮብም ከበሽታው የዳነው በዚህች ዕለት ነው፡፡
ጻዲቁ ኢዮብ በፈሳሽ ውኃ ታጥቦ ከደዌው ሁሉ ስለተፈወሰ
ለሰዎች ልማዳቸው ሆኖ ዓመቱ ዞሮ ሲመጣ ፈሳሹ ውኃም
በመላ ጊዜ በአዲስ ውኃ ይጠመቃሉ፣ በእርሱም ይባረካሉ፡፡
ሐዋርያው በርተሎሜዎስ፡- ወንጌልን ይሰብክ ዘንድ ዕጣ
የደረሰው አልዋሕ በሚባል አገር ነው፡፡ ቅዱስ ጴጥሮስ
ሊያደርሰው አብረው ወደ አልዋሕ ሄዱ፡፡ ወደ ከተማው
ለመግባት ምክንያት ፈለጉና ቅዱስ ጴጥሮስ ቅዱስ
በርተሎሜዎስን ‹‹አትክልተኛ ባለሙያ ነው›› ብሎ የወይኑን
ቦታ እንዲጠብቅለት ለአንድ ባለጸጋ መኰንን ባሪያ አድርጎ
ሸጠው፡፡ ባለጸጋውም በርተሎሜዎስን በ30 እስቴታር
ገዝቶት ሄደ፡፡ ቅዱስ ጴጥሮስ ገንዘቡን ደብቆ ለቅዱስ
በርተሎሜዎስ በድብቅ ሰጥቶት እንዲመጸውተው ነግሮት
ወደ ኢየሩሳሌም ተመለሰ፡፡ አልዋሕ ከገባ በኋላ ቅዱስ
በርተሎሜዎስ የወይን ቦታው አለቃ ሆኖ 40 ቀን
ተቀመጠ፡፡ ወንጌሉን ባለመስበኩ በሀዘን እያለቀሰ ጌታችንን
በጸሎት ጠየቀው፡፡ በገንዘቡ ገዝቶት ባሪያው ያደረገው
ባለጸጋውም የወይኑን ቦታ ያይ ዘንድ እንደመጣ መርዘኛ እባብ
ነድፎት ሞተ፡፡ ሕዝቡም ተሰብስቦ ሲያለቅስ በርተሎሜዎስ
ግን ወደ ጌታችን ከጸለየ በኋላ ሄዶ ባለጸጋውን ሰው ከሞት
አስነሣው፡፡ በዚህም ሕዝቡ ሁሉ አምነው ተጠምቀዋል፡፡
በርተሎሜዎስም ወደ ሌሎች አገሮች ሄዶ አስተማረ፡፡
ጌታችን ወደ በርበሮች ዘንድ ሄዶ ወንጌልን እንዲሰብክ
አዘዘው፡፡ ረዳት እንዲሆነውም እንድርያስን ከደቀ መዝሙሩ
ጋር ላከለት፡፡ የሀገሪቱ ሰዎች ግን እጅግ ክፉዎች ነበሩ፡፡
በሐዋርያቱም ፊት በአስማት አስደናቂ ተአምራት እያሳዩ
ትምህርታቸውን የማይቀበሏቸው ሁኑ፡፡ ይህን ጊዜ ጌታችን
ሰውን ከሚበሉ አገር አንዱን ገጸ ከልብ ይታዘዝላቸው ዘንድ
በሚያዙትም ነገር ሁሉ ከትእዛዛቸው እንዳይወጣ አዘዘው፡፡
ሐዋርያትም ወደ በርበሮች አገር ዳግመኛ በገቡ ሰዓት
ይበሏቸው ዘንድ ኃይለኛ አራዊትን አውጥተው ለቀቁባቸው፡፡
ያ ገጸ ከልብም በአራዊቱ ላይ ተነሥቶ እየነጠቀ በላቸው፡፡
ይህንንም የተመለከቱት በርበሮች እጅግ ፈርተው በድንጋጤ
ብቻ የሞቱ አሉ፡፡ በሐዋርያቱም እግር ሥር ወደቁ፡፡
ሐዋርያቱም አስተምረው ካሳመኗቸው በኋላ
አጥምቀዋቸዋል፡፡ ከዚህ በኋላ ቅዱስ በርተሎሜዎስ
እግዚአብሔርን ወደማያውቁ አገሮች ሄዶ ብዙ ተአምራትን
እያደረገ አስተምሮ አጠመቃቸው፡፡ የከሃዲው ንጉሡ
የአግሪጳን ሚስትም ትምህርቱን ሰምታ በጌታችን አመነች፡፡
ንጉሡ አግሪጳም በዚህ እጅግ ተቆጥቶ ቅዱስ
በርተሎሜዎስን ብዙ ካሠቃየው በኋላ አሸዋ በተሞላ ትልቅ
ከረጢት ውስጥ ከቶ ከነሕይወቱ ባሕር ውስጥ እንዲጥሉት
አደረገ፡፡ ምእመናንም ሥጋውን አውጥተው በክብር
ቀብረውታል፡፡ ረድኤት በረከቱ ይደርብን፣ በጸሎቱ ይማረን፡፡
+ + + + + + + + + + + + + + +
አባ ሚልኪ ዘቁልዝም፡- በላይኛው ግብጽ የሚኖሩ ባለጸጋ
ወላጆቻቸው በስዕለት ወለዷቸው፣ ብሉይን ከሐዲስ አጠናቀው
ከተማሩ በኋላ የአባታቸውን ወርቅ ለድኆች ሰጥተው ገዳም
ገብተው መነኩሰው በታላቅ ተጋድሎ ኖሩ፣ የአገረ ገዥውልን
ልጅ ዘንዶ ውጦት ሳለ አባ ሚልኪ ዘንዶውን ጠርቶት ልጁን
ይተፋው ዘንድ አዘዘውና ልጁ ጤነኛ እንደሆነ ከዘንዶው ውስጥ
ወጣ፣ በውስጡ ያደረ ከይሲም በኖ ጠፋ፣ ጻድቁ ቤ/ክ ሲሠሩ
የመሠረቱ ድንጋይ ራሱ በተአምራት እየተፈነቀለ ይተከል
ነበር፣ ለ300 መነኮሳትም አባት ሆነው በተአምራታቸው
የፋርስንና የሮም ሰዎችን አሳመኗቸው፣ ዋሻ ዘግተው ሊኖሩ
በማሉ ጊዜ ሰይጣን መሀላቸውን ሊያፈርስ አስቦ በሮሙ ንጉሥ
ልጅ አድሮ አሳመማትና በአባ ሚልኪ ካልሆነ በቀር
አልወጣም አለ፣ ንጉሡም ልኮባቸው በደመና ተጭነው ሄደው
ልጅቷን ፈውሰው አድሮባት የነበረውን ሰይጣን ገዝተው
አሠሩትና ከንጉሡ ቤት 14 ሰው የማይሸከመውን ድንጋይ
በአንገቱ ላይ አሳስረው አስሸክመውት ሰው ሁሉ እያየው ወደ
ገዳማቸው አስመጡትና ድንጋዩን የበዓታቸው መዝጊያ
አደረጉት፤ ጻድቁ በብርቱ ሲጋደሉ ኖረው የሚያርፉበት ቀን
ከተነገራቸው በኋላ እነ እንጦንስ፣ መቃርስ፣ ሲኖዳ፣ ብሶይ፣
ጳኩሚስ ተገልጠውላቸው ወንድማችን ና ወደ እኛ ብለዋቸው
በሰላም ዐርፈዋል፡፡ ረድኤት በረከታቸው ይደርብን፣
በጸሎታቸው ይማረን፡፡
+ + + + + + + + + + + + + + +
ራጉኤል ሊቀ መላእክት:- ራጉኤል ማለት የብርሃናት አለቃ
ማለት ነው። የብርሃናት አለቃ ሲባል ፀሐይን፣ ጨረቃን እና
ከዋክብትን በማመላለስና ለሰው ልጆች፣ ለአዝርዕት፣
ለእንስሳት፣ ለአራዊት ሁሉ ብርሃንን የሚመግብ ነው ማለት
ነው። አንድም ራጉኤል ማለት የሚበቀል ማለት ነው።
የሚበቀል ነው ማለት በቀል የሚገባው ለጠላት ነው የሰው
ልጅ ጠላት ደግሞ ዲያብሎስ ነው፤ ስለሆነም ቅዱስ ራጉኤል
እግዚአብሔርን አምነው ሕገ እግዚአብሔርን ጠብቀው
በፍርሐተ እግዚአብሔር አምልኮቱን ለሚፈጽሙ ሁሉ ጠላት
ዲያብሎስን የሚያርቅላቸው ወደ እነርሱም ፈጥኖ በመድረስ
የሚታደጋቸው ነው ማለት ነው። ሔኖክ 6:4፡፡ አንድም
ራጉኤል ማለት የኃያላን ኃያል እግዚአብሔር ማለት ነው።
የኃያላን ኃያል ያለው የእግዚአብሔርን ኃያልነት ከምድር
ፍጥረታት ዘንድ ኃያል ከሚባሉት ሁሉ ሊገለጽ የማይችል
ኃያልነቱን ለመግለጽ ኃያልነቱም ከ እስከ የሌለው መሆኑን
ለመግለጽ የተቀመጠ ነው። ስለዚህ እግዚአብሔር ኃያል
የኃያላን ኃያል መሆኑን የሚገልጽ ትርጉም አለው።
አንድም ራጉኤል ማለት ጽኑ እግዚአብሔር ማለት ነው።
የእግዚአብሔር አምላክን ጽኑነት ለማጉላት ሲል ጽኑ አለው።
እግዚአብሔር የማይወላውል የማይዋዥቅ የማይከዳ ነው
ለማለትም ሲል ይህ ስያሜ ተሰጠው። የእግዚአብሔርን ጽናት
የሚያሳይ ትርጉም ያለው ስያሜ ነው። የሊቀ መላእክት
የቅዱስ ራጉኤል አገልግሎት እና ስልጣን፡- እመቤታችን
ቅድስት ድንግል ማርያም ከዚህ ዓለም በ64 ዓመቷ ካረፈች
በኋላ ሥጋዋ ወደ ዕፀ ሕይወት ሲነጠቅ (ሲያርፍ) አብሮ
ለሔደው እና ስጋዋን በእጣን ሲያጥን ለነበረው ለፍቁረ እግዚ
ለቅዱስ ዮሐንስ ኅብስትን የመገበ መልአክ ነው።
በብርሃናት ሁሉ ላይ የሰለጠነ መልአክ ነው። ከአዳም ሰባተኛ
ትውልድ የሆነ በእግዚአብሔር ፊት ግሩም ያማረ ሥራው
የሰመረ እስከዛሬ የሞት ወጥመድ ያልያዘው የሞት ጥላ
ያላረፈበት ነብዩ ሔኖክ "ከቅዱሳን መላእክት አንዱ የሆነ ጸላዒ
ዲያብሎስን የሚበቀለው ራጉኤል በብርሃናት ላይ የሰለጠነ
ነው" ሲል ስለ እርሱ ተናግሯል፡፡
እግዚአብሔር ዓለምን ይቆጣጠር ዘንድ የሾመው ታላቅና
ቅዱስ መልአክ ነው። (ድርሳነ ራጉኤል ዘ ጥቅምት ገጽ 23)
አዲስ ሰማይና አዲስ ምድር ለመተካት ዓለምን የመለወጥ
ሥልጣን የተሰጠው ቅዱስ መልአክ ነው። ከእግዚአብሔር
የጌትነቱ አዳራሽ ይገባና ይወጣ ዘንድ ስልጣን ያለው
ከኪሩቤልና ከሱራፌል ጋር ከፈጣሪ የጌትነት ዙፋን ፊት
የሚቆም ነው። ሎጥን ሚስቱንና ልጆቹን ከእሳተ ጎመራ
ያዳነ የበለአምን እርግማን ወደ በረከት የለወጠ እርሱ ነው።
በቅዱስ ራጉኤል ስነ ሥዕል ላይ የምናየው ይህ ባለ አራት
እራስ ንስር ከአርባእቱ ኪሩቤል አንዱ ገጸ ንስር ነው።
የሥላሴን የጌትነት ዙፋን የሚሸከሙ አርባዕቱ እንስሳት
ናቸው። የሚሸከሙት ሲባል ጫማ የሰውን ልጅ
እንደሚሸከመው እንጂ ችለውትስ አይደለም። እነርሱም
የሰው ገጽ፣ የእንስሳ ገጽ፣ የንስር ገጽ እና የአንበሳ ገጽ ያላቸው
ናቸው። ይህንንም ነብዩ ሕዝቅኤል "ለእያንዳንዱ እንስሳትም
የተለያዩ አራት ገጾች ነበሩት። ይህውም በስተቀኝ በኩል
የእንስሳ መልክ፣ በስተ ግራ የላም ገጽ፣ በበስተ ኋላም የንስር
ገጽ የሚመስሉ ነበሩ" ብሏል ሕዝ 1፡6-13፡፡ ከዚህ
የምንገነዘበው ነገር ቢኖር አራት ገጽ ካላቸው ኪሩቤል
መካከል አንዱ ንስር መሆኑን ነው። ቅዱስ ራጉኤል ደግሞ
የእነዚህ ኪሩቤል አለቃቸው (የጌትነቱ ዙፋን ጠባቂ) በመሆኑ
በዚህ ምክንያት ማለትም እነርሱ ዙፋኑን ተሸካሚ እርሱ
ደግሞ አጠገባቸው መቆሙ መንበሩን ጠባቂ በመሆኑ በዚህ
አይነት የአገልግሎት ድርሻ አብረው ሊሳሉ ችለዋል። ቅዱስ
ያሬድም በድጓው "አርባእቱ እንስሳ አልቄንጥሩ እንደሚባለው
ንስር ፊት ለፊት አይታዩም አንዱም በመራቸው ይሔዳሉ
እነርሱም እያንዳንዳቸው አራት ገጽ ሲኖራቸው ሳያርፉና
ሳይደክሙ የሚያመሰግኑ ናቸው" በማለት ጽፏል። አንድም
መላእክት ነገደ ሱራፌል እና ነገደ ኪሩቤል በመባል
ይከፈላሉ። በነገደ ሱራፌል እነ ቅዱስ ሚካኤል፣ ቅዱስ
ሩፋኤል ወዘተ ሲሆኑ በነገደ ኪሩቤል ደግሞ ቅዱስ ገብርኤል
ቅዱስ ራጉኤል ወዘተ ያጠቃልላል። ስለዚህ ቅዱስ ራጉኤል
ነገዱ ከነገደ ኪሩቤል ነው በዚህም ላይ የነገደ ኪሩቤል
አልቄንጡራ (አራት እራስ ንስር) አለቃቸው ቅዱስ ራጉኤል
ነው። በዚህም ምክንያት አብረው ሊሳሉ ችሏል። አንድም
መላእክትን ሁሉ እንደ እየስራቸው መለያ ስነ ሥዕላቸውን
መሳል ልማድ ነውና። ለምሳሌ ቅዱስ ሚካኤል ከቅድስት
አፎምያ ጋር፣ ቅዱስ ገብርኤል ከሠለስቱ ደቂቅ ጋር፣ ቅዱስ
ዑራኤል ከእዝራ ሱቱኤል ጋር እንደሚሳሉት ሁሉ ማለት
ነው። በዚህም መሰረት ቅዱስ ራጉኤልም ዐቃቤ መንበር
ነውና መንበሩን በሚሸከሙት ኪሩቤል ከሚመሰሉት ንስሮች
ጋር አብረው ሊሳሉ ችለዋል፡፡
ሊቀ መላእክት ቅዱስ ራጉኤል ከአምላክ የተሰጠው ቃል
ኪዳን እግዚአብሔር አምላክ በስሙ ለታመኑት ቅዱሳን፣
ጻድቃን፣ ሰማእታት፣ ሐዋርያት፣ ዘወትር ያለማቋረጥ ስሙን
ለሚጠሩት ቅዱሳን መላእክት ሁሉ ቃል ኪዳን ሰጥቷቸዋል።
የሰጣቸውም ቃል ኪዳን ዘላለማዊ እና ሊሻር የማይችል
ነው። ለመላእክት አለቃ ለቅዱስ ራጉኤልም ይህን ቃል ኪዳን
ሰጥቶታል "የራጉኤል አምላክ ይቅር በለኝ በማለት አንዲት
ቃልስ እንኳን ቢናገር እንደ ወዳጄ እንደ አብርሃም፣ እንደ
ባለሟሌም እንደ ይስሐቅ፣ እንደ አከበርኩትም እንደ ያዕቆብ
ክብርን ባለሟልነትን እሰጠዋለሁ በራሱ ላይም አክሊል
አቀዳጀዋለሁ እረጅም ዘመናት ሰፊ ወራትም እሰጠዋለሁ"
ሲል ቃሉን ሰጥቶታል፡፡ ሊቀ መላእክት ቅዱስ ራጉኤል
መስከረም 1 ቀን ከሊቃነ መላእክት በ4ተኛ ደረጃ
የተሾመበት ዕለት ነው። ግንቦት 1 ቀን ለታላቁ አባት ለሄኖክ
ምሥጢራትን የገለጸበት በዓሉ ነው፡፡ ጥበቃው አይለየን፣
በምልጃው ይማረን፡፡
የቅዱሳን አባቶቻችን አምላክ ሀገራችንን ይጠብቅልን፡፡
Tuesday, September 6, 2016
=>+*"+<+>††† ዻጉሜን-1 +" ወርኀ ዻጉሜን "+ †††<+>+"*
በስመአብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን
ዻጉሜን-1
+" ወርኀ ዻጉሜን "+
=>#እግዚአብሔር አዝማናትን የፈጠራቸው ለሰው ልጆች
ጥቅም መሆኑ ይታወቃል:: እርሱ ባወቀ: በረቂቅ ሥልጣኑ
ዓለምን ፈጥሮ: ጊዜያትን እንዲከፍሉ ብርሃናትን (ፀሐይ:
ጨረቃ: ከዋክብትን) ፈጥሮልናል::
+ጊዜያትንም በደቂቃ: በሰዓት: በቀን: በሳምንት: በወር:
በዓመታት: በኢዮቤልዩ: በክፍላተ ዘመናት እንድንቆጥር
ያስማረንም እርሱ ነው:: የሰከንድ 540,000 ክፋይ
ከሆነችው 'ሳድሲት' እስከ ትልቁ ቀመር (532 ዓመት) ድረስ
እርሱ ለወደዳቸው እንዲያስተውሉት ገልጧል::
+በየዘመኑም በቅዱስ #ድሜጥሮስ: በቅዱስ #ዮሐንስ
ዘደማስቆ: በቅዱስ #አቡሻኽር እና በሌሎቹም አድሮ
መልካሙን አቆጣጠር አስተምሯል:: ሃገራችን ኢትዮዽያ
ደግሞ የ13 ወራት የፀሐይ ጸጋ (thirteen months sun
shine) ያላት: 4ቱ ወቅቶች የተስማሙላት ናት::
+ሌላው ዓለም ወሮችን 31,30,29 እያደረገ ሲጠቀም እኛ
ግን እንደ ኖኅ (ዘፍ) አቆጣጠር ወሮችን በ30 ቀናት ወስነን:
ዻጉሜንን ለብቻዋ እናስቀምጣለን:: ዻጉሜን 'ኤዻጉሚኖስ'
ከሚል የግሪክ (ጽርዕ) ቃል የተወሰደ ሲሆን ትርጉሙም
'ትርፍ: ጭማሪ' እንደ ማለት ነው::
+የወርኀ ዻጉሜን 5ቱ (6ቱ) ቀናትም ወደ አዲስ ዓመት
መሸጋገሪያ እንደ መሆናቸው ብዙ ምሳሌያት (ምሥጢራት)
አሏቸው:: ዋናው ግን በዚህ ጊዜ ዳግም ምጽዓት ይታሠባል::
ጊዜውንም በጾምና በጸሎት ሊያሳልፉት ይገባል:: ግን በፈቃድ
ነው እንጂ የግዴታ አይደለም::
+" ቅዱስ ዮሐንስ መጥምቅ "+
*የቅዱሳኑ ዘካርያስና ኤልሳቤጥ ልጅ
*በማሕጸን ሳለ መንፈስ ቅዱስ የሞላበት
*በበርኀ ያደገና በገዳማዊ ቅድስና ያጌጠ
*እሥራኤልን ለንስሃ ያጠመቀ
*የጌታችንን መንገድ የጠረገ
*ጌታውን ያጠመቀና
*ስለ እውነት አንገቱን የተቆረጠ ታላቅ ሰው ነው::
*ስለዚሕም ቤተ ክርስቲያን ነቢይ: ሐዋርያ: ሰማዕት: ጻድቅ:
ገዳማዊ: መጥምቀ መለኮት: ጸያሔ ፍኖት: ቃለ ዐዋዲ ብላ
ታከብረዋለች::
+ቅዱሱ በዚህች ዕለት ወደ እሥር ቤት ገብቷል:: ይሕስ እንደ
ምን ነው ቢሉ:-
ንጉሡ ሔሮድስ የወንድሙን የፊልዾስን ሚስት ሔሮድያዳን
በማግባቱና በመሰል ክፋቶቹ ቅዱስ ዮሐንስ ይገስጸው ነበር::
ቅዱስ ዮሐንስ "መምሕር ወመገስጽ: ዘኢያደሉ ለገጽ - ፊት
አይቶ የማያዳላ" ነውና ገሰጸው::
+ሔሮድስ ቅዱሱን ይፈራው: ያከብረውም ነበር:: በኋላ ግን
ፈቃደ ሥጋው ስላየለበት: በተለይ ደግሞ ከ7 ቀናት በሁዋላ
ልደቱን ሲያከብር እንዳይረብሸው በመስጋት በዚህች ቀን
በወታደሮቹ አስይዞ እሥር ቤት ውስጥ ጥሎታል:: ለ7 ቀናት
በጨለማ ውስጥ አሥሮ መስከረም 2 ቀን አንገቱን እንዴት
እንዳስቆረጠው ዕለቱን ጠብቀን እንመለከታለንና የዚያ ሰው
ይበለን::
+" ቅዱስ ዑቲኮስ ሐዋርያ "+
=>ቅዱሱ ሐዋርያ ጭራሽ ከነ ስማቸው እንኩዋ እየተዘነጉ
ከሔዱ ሐዋርያት አንዱ ሲሆን ቁጥሩም ከ72ቱ አርድእት
ነው:: በወጣትነት ዘመኑ የጌታችን ደቀ መዝሙር መሆንን
መርጦ ለ3 ዓመታት ከ3 ወራት ምሥጢረ ወንጌልን ጠንቅቆ
ተምሯል::
+መንፈስ ቅዱስ በወረደ ጊዜም እንደ መጠኑ ተቀብሎ
ለአገልግሎት ወጥቷል:: በመጀመሪያ የወንጌላዊው ዮሐንስ
ተከታይ ሁኖ ብዙ ምሥጢራትን ተካፍሏል:: ቀጥሎም ቅዱስ
ዻውሎስን ተከትሎ ብዙ አሕጉራትን በስብከተ ወንጌል
አዳርሷል::
+በመጨረሻም በእስያ አካባቢ ለብቻው ተጉዞ: ብዙ ነፍሳትን
ማርኮ: ጣዖታትን አጥፍቷል:: ስለዚህ ፈንታም በእሳት:
በስለትና በግርፋት ብዙ መከራዎችን አሳልፏል:: በዚህች
ቀንም በበጐው እርግና (ሽምግልና) ዐርፏል::
+" ቅዱስ ብሶይ ቀሲስ "+
=>በ3ኛው መቶ ክ/ዘመን ካህናት አንዱ የነበረው አባ ብሶይ
ለአገልግሎት ወጥቶ ሲመለስ የቤተሰቦቹ ቤት ሰው
አልነበረበትም:: "የት ሔዱ?" ብሎ ቢጠይቅ "ወንድምህ አባ
ሖርና እናትህ ቅድስት ይድራ ወደ እስክንድርያ ሔደዋል::
በዚያም ስለ ክርስቶስ ፍቅር ተሰውተዋል" አሉት::
+በማግስቱ የኔ ብጤዎችን ጠርቶ ሃብቱን: ንብረቱን: ቤቱን
አካፈላቸው:: ለራሱ ግን አንዲት በትር እና 3 የዳቦ ቁራሾች
ይዞ ጉዞ ተነሳ:: ወደ እስክንድርያ እንደ ደረሰ አፈላልጐ
የቤተሰቦቹን መቃብር አገኘ:: ከፊታቸው ወድቆም የናፍቆት
ለቅሶን አለቀሰ::
+ወዲያውም እንዲህ አላቸው:- "ፈጥኜ ወደ እናንተ
ስለምመጣ ጠብቁኝ:: ደግሞም ጸልዩልኝ::" ከዚያ ተነስቶ
በመኮንኑ ፊት ስለ ክርስቶስ የባሕርይ አምላክነት መሰከረ::
በዚህ ምክንያት ብዙ ተሰቃይቶ በዚህች ቀን ሰማዕት ሆኗል::
ከወገኖቹም ጋር ተቀብሯል::
=>አምላከ ቅዱሳን ተረፈ ዘመኑን ባርኮ ለአዲሱ ዘመን በቸር
ያድርሰን:: ከወዳጆቹም ጸጋ በረከትን ይክፈለን::
=>ዻጉሜን 1 ቀን የሚከበሩ ዓመታዊ የቅዱሳን በዓላት=
1.ቅዱስ ዮሐንስ መጥምቅ (የታሠረበት)
2.ቅዱስ ዑቲኮስ ሐዋርያ (ከ72ቱ አርድእት)
3.ቅዱስ ብሶይ ቀሲስ (ሰማዕት)
4.አባ ዻኩሚስ / ባኹም (የ3,000 ቅዱሳን አባት)
5.አባ ሰራብዮን / ሰራፕዮን (የ10,000 ቅዱሳን አባት)
=>+"+ ጌታ ኢየሱስ ለሕዝቡ ስለ ዮሐንስ ሊናገር ጀመረ. . .
ምን ልታዩ ወጣችሁ? ነቢይን? አዎን እላችሁአለሁ ከነቢይም
የሚበልጠውን. . . እውነት እላቹሃለሁ ከሴቶች ከተወለዱት
መካከል ከመጥምቁ ዮሐንስ የሚበልጥ አልተነሳም. . .
ነቢያት ሁሉና ሕጉ እስከ ዮሐንስ ድረስ ትንቢት ተናገሩ::
ልትቀበሉትስ ብትወዱ ይመጣ ዘንድ ያለው ኤልያስ ይሕ ነው::
የሚሰማ ጀሮ ያለው ይስማ:: +"+ (ማቴ. 11:7-15)
<ወስብሐት ለእግዚአብሔር>
ዻጉሜን-1
+" ወርኀ ዻጉሜን "+
=>#እግዚአብሔር አዝማናትን የፈጠራቸው ለሰው ልጆች
ጥቅም መሆኑ ይታወቃል:: እርሱ ባወቀ: በረቂቅ ሥልጣኑ
ዓለምን ፈጥሮ: ጊዜያትን እንዲከፍሉ ብርሃናትን (ፀሐይ:
ጨረቃ: ከዋክብትን) ፈጥሮልናል::
+ጊዜያትንም በደቂቃ: በሰዓት: በቀን: በሳምንት: በወር:
በዓመታት: በኢዮቤልዩ: በክፍላተ ዘመናት እንድንቆጥር
ያስማረንም እርሱ ነው:: የሰከንድ 540,000 ክፋይ
ከሆነችው 'ሳድሲት' እስከ ትልቁ ቀመር (532 ዓመት) ድረስ
እርሱ ለወደዳቸው እንዲያስተውሉት ገልጧል::
+በየዘመኑም በቅዱስ #ድሜጥሮስ: በቅዱስ #ዮሐንስ
ዘደማስቆ: በቅዱስ #አቡሻኽር እና በሌሎቹም አድሮ
መልካሙን አቆጣጠር አስተምሯል:: ሃገራችን ኢትዮዽያ
ደግሞ የ13 ወራት የፀሐይ ጸጋ (thirteen months sun
shine) ያላት: 4ቱ ወቅቶች የተስማሙላት ናት::
+ሌላው ዓለም ወሮችን 31,30,29 እያደረገ ሲጠቀም እኛ
ግን እንደ ኖኅ (ዘፍ) አቆጣጠር ወሮችን በ30 ቀናት ወስነን:
ዻጉሜንን ለብቻዋ እናስቀምጣለን:: ዻጉሜን 'ኤዻጉሚኖስ'
ከሚል የግሪክ (ጽርዕ) ቃል የተወሰደ ሲሆን ትርጉሙም
'ትርፍ: ጭማሪ' እንደ ማለት ነው::
+የወርኀ ዻጉሜን 5ቱ (6ቱ) ቀናትም ወደ አዲስ ዓመት
መሸጋገሪያ እንደ መሆናቸው ብዙ ምሳሌያት (ምሥጢራት)
አሏቸው:: ዋናው ግን በዚህ ጊዜ ዳግም ምጽዓት ይታሠባል::
ጊዜውንም በጾምና በጸሎት ሊያሳልፉት ይገባል:: ግን በፈቃድ
ነው እንጂ የግዴታ አይደለም::
+" ቅዱስ ዮሐንስ መጥምቅ "+
*የቅዱሳኑ ዘካርያስና ኤልሳቤጥ ልጅ
*በማሕጸን ሳለ መንፈስ ቅዱስ የሞላበት
*በበርኀ ያደገና በገዳማዊ ቅድስና ያጌጠ
*እሥራኤልን ለንስሃ ያጠመቀ
*የጌታችንን መንገድ የጠረገ
*ጌታውን ያጠመቀና
*ስለ እውነት አንገቱን የተቆረጠ ታላቅ ሰው ነው::
*ስለዚሕም ቤተ ክርስቲያን ነቢይ: ሐዋርያ: ሰማዕት: ጻድቅ:
ገዳማዊ: መጥምቀ መለኮት: ጸያሔ ፍኖት: ቃለ ዐዋዲ ብላ
ታከብረዋለች::
+ቅዱሱ በዚህች ዕለት ወደ እሥር ቤት ገብቷል:: ይሕስ እንደ
ምን ነው ቢሉ:-
ንጉሡ ሔሮድስ የወንድሙን የፊልዾስን ሚስት ሔሮድያዳን
በማግባቱና በመሰል ክፋቶቹ ቅዱስ ዮሐንስ ይገስጸው ነበር::
ቅዱስ ዮሐንስ "መምሕር ወመገስጽ: ዘኢያደሉ ለገጽ - ፊት
አይቶ የማያዳላ" ነውና ገሰጸው::
+ሔሮድስ ቅዱሱን ይፈራው: ያከብረውም ነበር:: በኋላ ግን
ፈቃደ ሥጋው ስላየለበት: በተለይ ደግሞ ከ7 ቀናት በሁዋላ
ልደቱን ሲያከብር እንዳይረብሸው በመስጋት በዚህች ቀን
በወታደሮቹ አስይዞ እሥር ቤት ውስጥ ጥሎታል:: ለ7 ቀናት
በጨለማ ውስጥ አሥሮ መስከረም 2 ቀን አንገቱን እንዴት
እንዳስቆረጠው ዕለቱን ጠብቀን እንመለከታለንና የዚያ ሰው
ይበለን::
+" ቅዱስ ዑቲኮስ ሐዋርያ "+
=>ቅዱሱ ሐዋርያ ጭራሽ ከነ ስማቸው እንኩዋ እየተዘነጉ
ከሔዱ ሐዋርያት አንዱ ሲሆን ቁጥሩም ከ72ቱ አርድእት
ነው:: በወጣትነት ዘመኑ የጌታችን ደቀ መዝሙር መሆንን
መርጦ ለ3 ዓመታት ከ3 ወራት ምሥጢረ ወንጌልን ጠንቅቆ
ተምሯል::
+መንፈስ ቅዱስ በወረደ ጊዜም እንደ መጠኑ ተቀብሎ
ለአገልግሎት ወጥቷል:: በመጀመሪያ የወንጌላዊው ዮሐንስ
ተከታይ ሁኖ ብዙ ምሥጢራትን ተካፍሏል:: ቀጥሎም ቅዱስ
ዻውሎስን ተከትሎ ብዙ አሕጉራትን በስብከተ ወንጌል
አዳርሷል::
+በመጨረሻም በእስያ አካባቢ ለብቻው ተጉዞ: ብዙ ነፍሳትን
ማርኮ: ጣዖታትን አጥፍቷል:: ስለዚህ ፈንታም በእሳት:
በስለትና በግርፋት ብዙ መከራዎችን አሳልፏል:: በዚህች
ቀንም በበጐው እርግና (ሽምግልና) ዐርፏል::
+" ቅዱስ ብሶይ ቀሲስ "+
=>በ3ኛው መቶ ክ/ዘመን ካህናት አንዱ የነበረው አባ ብሶይ
ለአገልግሎት ወጥቶ ሲመለስ የቤተሰቦቹ ቤት ሰው
አልነበረበትም:: "የት ሔዱ?" ብሎ ቢጠይቅ "ወንድምህ አባ
ሖርና እናትህ ቅድስት ይድራ ወደ እስክንድርያ ሔደዋል::
በዚያም ስለ ክርስቶስ ፍቅር ተሰውተዋል" አሉት::
+በማግስቱ የኔ ብጤዎችን ጠርቶ ሃብቱን: ንብረቱን: ቤቱን
አካፈላቸው:: ለራሱ ግን አንዲት በትር እና 3 የዳቦ ቁራሾች
ይዞ ጉዞ ተነሳ:: ወደ እስክንድርያ እንደ ደረሰ አፈላልጐ
የቤተሰቦቹን መቃብር አገኘ:: ከፊታቸው ወድቆም የናፍቆት
ለቅሶን አለቀሰ::
+ወዲያውም እንዲህ አላቸው:- "ፈጥኜ ወደ እናንተ
ስለምመጣ ጠብቁኝ:: ደግሞም ጸልዩልኝ::" ከዚያ ተነስቶ
በመኮንኑ ፊት ስለ ክርስቶስ የባሕርይ አምላክነት መሰከረ::
በዚህ ምክንያት ብዙ ተሰቃይቶ በዚህች ቀን ሰማዕት ሆኗል::
ከወገኖቹም ጋር ተቀብሯል::
=>አምላከ ቅዱሳን ተረፈ ዘመኑን ባርኮ ለአዲሱ ዘመን በቸር
ያድርሰን:: ከወዳጆቹም ጸጋ በረከትን ይክፈለን::
=>ዻጉሜን 1 ቀን የሚከበሩ ዓመታዊ የቅዱሳን በዓላት=
1.ቅዱስ ዮሐንስ መጥምቅ (የታሠረበት)
2.ቅዱስ ዑቲኮስ ሐዋርያ (ከ72ቱ አርድእት)
3.ቅዱስ ብሶይ ቀሲስ (ሰማዕት)
4.አባ ዻኩሚስ / ባኹም (የ3,000 ቅዱሳን አባት)
5.አባ ሰራብዮን / ሰራፕዮን (የ10,000 ቅዱሳን አባት)
=>+"+ ጌታ ኢየሱስ ለሕዝቡ ስለ ዮሐንስ ሊናገር ጀመረ. . .
ምን ልታዩ ወጣችሁ? ነቢይን? አዎን እላችሁአለሁ ከነቢይም
የሚበልጠውን. . . እውነት እላቹሃለሁ ከሴቶች ከተወለዱት
መካከል ከመጥምቁ ዮሐንስ የሚበልጥ አልተነሳም. . .
ነቢያት ሁሉና ሕጉ እስከ ዮሐንስ ድረስ ትንቢት ተናገሩ::
ልትቀበሉትስ ብትወዱ ይመጣ ዘንድ ያለው ኤልያስ ይሕ ነው::
የሚሰማ ጀሮ ያለው ይስማ:: +"+ (ማቴ. 11:7-15)
<ወስብሐት ለእግዚአብሔር>
=>+*"+<+>††† ጳጉሜ †††<+>+"*
ጳጉሜን
በኢትዮጵያ አቆጣጠር ከነሐሴ በኋላ ጳጉሜን የምትባል
አምስት ቀን አለች፡፡ ወር እንዳትባል አቅም ያንሳታል፡፡
ሳምንት እንዳትባል አምስት ቀን ብቻ ኾናለች፡፡ ጳጉሜን
የሚለው ስያሜዋ ግን “ኤፓጉሜኔ” ከሚለው የግሪክ ቃል
የመጣ መኾኑ በአበው ቃል ተነግሯል፡፡
“ኤፓጉሜኔ” ማለት ጭማሪ ማለት ነው ፡፡ በግእዝ
ቋንቋችን ተውሳክ ማለት ነው፡፡ ተውሳክ ማለት ተጨማሪ
ማለት ነው፡፡ “ወሰከ - ጨመረ” ከሚለው የግእዝ ግስ
የተገኘ ነው፡፡ ኤውሮፓዎች ጳጉሜን የወር ተጨማሪ
አድርገዋታል፡፡ ይኸውም ይታወቅ ዘንድ እኛ የወርን ቁጠር
ሠላሳ ስናደርግ እነርሱ ሠላሳ አንድ ብለው የሚቆጥሩት ወር
አላቸው፡፡ ይኹን እንጂ የኢትዮጵያ ሊቃውንት ጳጉሜን የወር
ተጨማሪ ሳያደርጉ የዓመት ተጨማሪ አድርገዋታል፡፡
የዓመቱንም ቀን ቁጥር ሦስት መቶ ስድሳ አምስት ቀን ከነሱ
ብለው ደምረውታል፡፡
በቅድስት ቤተክርስቲያን ካሉት ሁለት የፈቃድ አጽዋማት
መካከል አንዱ በዚህ በጳጉሜ ወር የምንጾመው የፈቃድ ጾም
ነው፡፡ ይህም ጾመ ዮዲት በመባል ይታወቃል፡፡ ይህ ግን እንደ
አንደኛው የፈቃድ ጾም /ጽጌ ጾም/ በብዙዋኑ ዘንድ የታወቀ
አይደለም፡፡ የዮዲት ጾም የሚባለውም እርሷ ስለ ጾመችው
ነው፡፡ እዚህ ላይ ዮዲት ተብላ የተጠቀሰችው በቤተክርስቲያን
ታሪክ ትምህርት ላይ በጥፋት ሥራዋ በተደጋጋሚ
የምትጠቀሰው ዮዲት ጉዲት እንዳልሆነች ለማሳወቅ
እንወዳለን፡፡ ወደ ታሪኩ ስንመለስ የፋርስ ንጉስ ናቡከደነጾር
በሠራዊቱ ተመክቶ ሹም ጠላት አጥፋ ድንበር አስፋ ካመነው
እጅ መንሻ እየተቀበልህ ያላመነውን እያሳመንህ ና ብሎ ለጦር
አበጋዙ ለሆሎፎርኒስ ትዕዛዝ ሰጠ፡፡ ዮዲ 2፡-2-7፡፡ እርሱም
እንደታዘዘው በኃይላቸው የታመኑ 12ሺህ እግረኞችንና በፈረስ
የተቀመጡ 12ሺህ ጦረኞችን እየመራ ዘምቶ ካመነው እጅ
መንሻ እየተቀበለ ያላመነውን እያሳመነ ብዙ ሀገሮችን እያጠፋ
ሲሔድ ከአይሁድ ከተማ ደረሰ በዚህም ብዙ ጥፋ በመድረሱ
የእስራኤል ልጆች አለቀሱ፡፡
ዮዲት ባሏ ሞቶባት ከወንድ ርቃ ንጽሕናዋን ጠብቃ በጾም
በቀኖና በሀዘን ተወስና ትኖራለች በተፈጠረው ጥፋት ህዝቡ
ላይ ለመጣው መከራ ማቅ ለብሳ በራስዋ ላይ ትብያ ነስንሳ
ወደ እግዚአብሔር አለቀሰች፡፡ የፍጥረቱን ጥፋት የማይሻ
እግዚአብሔር አምላክም ሕዝቡን የሚያድኑበትን መንገድ
ለመጠየቅ ሱባኤ በገባች በሦስተኛው ቀን ገለፀላት፡፡ ዮዲ
8፡-2 ፡፡ ከዚህ በኋላ ጠላታቸውን በዮዲት ምክንያት
እስራኤላውያን እስከ ዮርዳኖስ እየተከተሉ አጥፍተዋቸዋል፡፡
ዮዲት ጠላቷን ለማጥፋት የቻለችው በጾምና በጸሎት
ከእግዚአብሔር አምላክ ኃይል አግኝታ ነው፡፡ ስለዚህ
ምዕመናን ጥንተ ጠላታችን ሰይጣንን ፈቃደ ሥጋን ለማሸነፍ
በጾም ከፈጣሪያችን ኃይልን መጎናጸፍ አለብን ብለው ጳጉሜን
በፈቃድ ይጾማሉ፡፡
የጳጉሜ ወር ዕለተ ምጽአት የሚታሰብበትም ወር ነው፡፡
ይህም ጳጉሜ የዓመታት መሸጋገሪያ ጨለማው የክረምት
ወቅት ወደ ማብቂያው የምናልፍባት እንደሆነች ሁሉ
ምጽአትም ከጊዜያዊው ወደ ዘላለማዊ ከምድራዊ ወደ
ሰማያዊ ከዚህ ዓለም ወደ ወዲያኛው መሸጋገሪያ ነውና ነው፡፡
ሊቃውንቱ እንደ ሱባኤ ቀን ቀኖና እንዲፈጽምባት ለብቻ
ለይተው አኑረውታል፡፡ “ይህ ዓለም ኑሮ፣ ኑሮ በመጨረሻ
ያልፋል፡፡ ጌታ ዓለምን ለማሳለፍ ይመጣል” ሲሉ የገታ
የመምጣቱ ነገር እንዲነገርባት፣ መሥዋዕት እንዲሠዋባት፣
ጾም እንዲያዝባት፣ ምጽዋት እንዲመጸወትባት ለይተው
መድበዋታል፡፡
ሕዝቡ ሳይቀር “ጳጉሜን ዕድሜ ትሰጠናለች፤ በኋላም
ታድነናለች” ብለው ጾም ይጾሙባታል፡፡ የዚሁም ማስረጃ
በቅዱስ መልከ ጸዴቅ ድርሳን ይገኛል፡፡ ንግሥት ዘውዲቱ
ምኒልክ የጾም ሥርዐት ይፈጽሙባት ነበር፡፡ ሌሎችም
ሽማግሌዎችና ባልቴቶች አክብረው ይጾሙባታል፡፡ ኾኖም
የጳጉሜን አቆጣጠር አንዱ ከወር ጋራ፣ ሌላውም ከዓመት
ጋራ ቢያደርገውም በሀሉም አቆጣጠር ውስጥ ሕያዊት ኾና
መገኘቷ የታወቀ ነው፡፡
የነቢዩ ኄኖክ መጽሐፍም ጳጉሜን ጨርሶ አልዘነጋትም፡፡
ክርስቲያኖች ሁሉ በየዓመቱ በጳጉሜ ወር ሁሉም ተሰብስበው
ከሌሊት ጀምረው በቤተክርስቲያን ተገኝተው ጸበል
ይጠመቃሉ፡፡ ይህንን የምናደገውም እግዚአብሔር የተባረከ
ዓመት እንዲሰጠን፣ ባሳለፍነው ዓመት የሰራነውን ኃጢአት
ይቅር እንዲለን ነው፡፡ የምንጠመቀውም ንስሐ ገብተን
ነው፡፡ በእግዚአብሔር ስም የተቀደሰው ጸበል ደግሞ
ከበሽታችን ያድነናል፣ የተቀደስንም ያደርገናል፣ መጪውንም
ህይወታችን የተባረከ ያደርግልናል፡፡
ወስብሐት ለእግዚአብሔር
መልካም የአዲስ ዓመት ዋዜማ (ጷጉሜ) ይሁንላችሁ፡፡
ተዋሕዶ ሀይማኖታችን ለዘለአለም አለም ፀንታ ትኑርልን!!!
ጸልዩ በእንተ ሰላመ ቤተክርስትያን!!!
በኢትዮጵያ አቆጣጠር ከነሐሴ በኋላ ጳጉሜን የምትባል
አምስት ቀን አለች፡፡ ወር እንዳትባል አቅም ያንሳታል፡፡
ሳምንት እንዳትባል አምስት ቀን ብቻ ኾናለች፡፡ ጳጉሜን
የሚለው ስያሜዋ ግን “ኤፓጉሜኔ” ከሚለው የግሪክ ቃል
የመጣ መኾኑ በአበው ቃል ተነግሯል፡፡
“ኤፓጉሜኔ” ማለት ጭማሪ ማለት ነው ፡፡ በግእዝ
ቋንቋችን ተውሳክ ማለት ነው፡፡ ተውሳክ ማለት ተጨማሪ
ማለት ነው፡፡ “ወሰከ - ጨመረ” ከሚለው የግእዝ ግስ
የተገኘ ነው፡፡ ኤውሮፓዎች ጳጉሜን የወር ተጨማሪ
አድርገዋታል፡፡ ይኸውም ይታወቅ ዘንድ እኛ የወርን ቁጠር
ሠላሳ ስናደርግ እነርሱ ሠላሳ አንድ ብለው የሚቆጥሩት ወር
አላቸው፡፡ ይኹን እንጂ የኢትዮጵያ ሊቃውንት ጳጉሜን የወር
ተጨማሪ ሳያደርጉ የዓመት ተጨማሪ አድርገዋታል፡፡
የዓመቱንም ቀን ቁጥር ሦስት መቶ ስድሳ አምስት ቀን ከነሱ
ብለው ደምረውታል፡፡
በቅድስት ቤተክርስቲያን ካሉት ሁለት የፈቃድ አጽዋማት
መካከል አንዱ በዚህ በጳጉሜ ወር የምንጾመው የፈቃድ ጾም
ነው፡፡ ይህም ጾመ ዮዲት በመባል ይታወቃል፡፡ ይህ ግን እንደ
አንደኛው የፈቃድ ጾም /ጽጌ ጾም/ በብዙዋኑ ዘንድ የታወቀ
አይደለም፡፡ የዮዲት ጾም የሚባለውም እርሷ ስለ ጾመችው
ነው፡፡ እዚህ ላይ ዮዲት ተብላ የተጠቀሰችው በቤተክርስቲያን
ታሪክ ትምህርት ላይ በጥፋት ሥራዋ በተደጋጋሚ
የምትጠቀሰው ዮዲት ጉዲት እንዳልሆነች ለማሳወቅ
እንወዳለን፡፡ ወደ ታሪኩ ስንመለስ የፋርስ ንጉስ ናቡከደነጾር
በሠራዊቱ ተመክቶ ሹም ጠላት አጥፋ ድንበር አስፋ ካመነው
እጅ መንሻ እየተቀበልህ ያላመነውን እያሳመንህ ና ብሎ ለጦር
አበጋዙ ለሆሎፎርኒስ ትዕዛዝ ሰጠ፡፡ ዮዲ 2፡-2-7፡፡ እርሱም
እንደታዘዘው በኃይላቸው የታመኑ 12ሺህ እግረኞችንና በፈረስ
የተቀመጡ 12ሺህ ጦረኞችን እየመራ ዘምቶ ካመነው እጅ
መንሻ እየተቀበለ ያላመነውን እያሳመነ ብዙ ሀገሮችን እያጠፋ
ሲሔድ ከአይሁድ ከተማ ደረሰ በዚህም ብዙ ጥፋ በመድረሱ
የእስራኤል ልጆች አለቀሱ፡፡
ዮዲት ባሏ ሞቶባት ከወንድ ርቃ ንጽሕናዋን ጠብቃ በጾም
በቀኖና በሀዘን ተወስና ትኖራለች በተፈጠረው ጥፋት ህዝቡ
ላይ ለመጣው መከራ ማቅ ለብሳ በራስዋ ላይ ትብያ ነስንሳ
ወደ እግዚአብሔር አለቀሰች፡፡ የፍጥረቱን ጥፋት የማይሻ
እግዚአብሔር አምላክም ሕዝቡን የሚያድኑበትን መንገድ
ለመጠየቅ ሱባኤ በገባች በሦስተኛው ቀን ገለፀላት፡፡ ዮዲ
8፡-2 ፡፡ ከዚህ በኋላ ጠላታቸውን በዮዲት ምክንያት
እስራኤላውያን እስከ ዮርዳኖስ እየተከተሉ አጥፍተዋቸዋል፡፡
ዮዲት ጠላቷን ለማጥፋት የቻለችው በጾምና በጸሎት
ከእግዚአብሔር አምላክ ኃይል አግኝታ ነው፡፡ ስለዚህ
ምዕመናን ጥንተ ጠላታችን ሰይጣንን ፈቃደ ሥጋን ለማሸነፍ
በጾም ከፈጣሪያችን ኃይልን መጎናጸፍ አለብን ብለው ጳጉሜን
በፈቃድ ይጾማሉ፡፡
የጳጉሜ ወር ዕለተ ምጽአት የሚታሰብበትም ወር ነው፡፡
ይህም ጳጉሜ የዓመታት መሸጋገሪያ ጨለማው የክረምት
ወቅት ወደ ማብቂያው የምናልፍባት እንደሆነች ሁሉ
ምጽአትም ከጊዜያዊው ወደ ዘላለማዊ ከምድራዊ ወደ
ሰማያዊ ከዚህ ዓለም ወደ ወዲያኛው መሸጋገሪያ ነውና ነው፡፡
ሊቃውንቱ እንደ ሱባኤ ቀን ቀኖና እንዲፈጽምባት ለብቻ
ለይተው አኑረውታል፡፡ “ይህ ዓለም ኑሮ፣ ኑሮ በመጨረሻ
ያልፋል፡፡ ጌታ ዓለምን ለማሳለፍ ይመጣል” ሲሉ የገታ
የመምጣቱ ነገር እንዲነገርባት፣ መሥዋዕት እንዲሠዋባት፣
ጾም እንዲያዝባት፣ ምጽዋት እንዲመጸወትባት ለይተው
መድበዋታል፡፡
ሕዝቡ ሳይቀር “ጳጉሜን ዕድሜ ትሰጠናለች፤ በኋላም
ታድነናለች” ብለው ጾም ይጾሙባታል፡፡ የዚሁም ማስረጃ
በቅዱስ መልከ ጸዴቅ ድርሳን ይገኛል፡፡ ንግሥት ዘውዲቱ
ምኒልክ የጾም ሥርዐት ይፈጽሙባት ነበር፡፡ ሌሎችም
ሽማግሌዎችና ባልቴቶች አክብረው ይጾሙባታል፡፡ ኾኖም
የጳጉሜን አቆጣጠር አንዱ ከወር ጋራ፣ ሌላውም ከዓመት
ጋራ ቢያደርገውም በሀሉም አቆጣጠር ውስጥ ሕያዊት ኾና
መገኘቷ የታወቀ ነው፡፡
የነቢዩ ኄኖክ መጽሐፍም ጳጉሜን ጨርሶ አልዘነጋትም፡፡
ክርስቲያኖች ሁሉ በየዓመቱ በጳጉሜ ወር ሁሉም ተሰብስበው
ከሌሊት ጀምረው በቤተክርስቲያን ተገኝተው ጸበል
ይጠመቃሉ፡፡ ይህንን የምናደገውም እግዚአብሔር የተባረከ
ዓመት እንዲሰጠን፣ ባሳለፍነው ዓመት የሰራነውን ኃጢአት
ይቅር እንዲለን ነው፡፡ የምንጠመቀውም ንስሐ ገብተን
ነው፡፡ በእግዚአብሔር ስም የተቀደሰው ጸበል ደግሞ
ከበሽታችን ያድነናል፣ የተቀደስንም ያደርገናል፣ መጪውንም
ህይወታችን የተባረከ ያደርግልናል፡፡
ወስብሐት ለእግዚአብሔር
መልካም የአዲስ ዓመት ዋዜማ (ጷጉሜ) ይሁንላችሁ፡፡
ተዋሕዶ ሀይማኖታችን ለዘለአለም አለም ፀንታ ትኑርልን!!!
ጸልዩ በእንተ ሰላመ ቤተክርስትያን!!!
=>+*"+<+>††† ጾመ ዮዲት - ጾመ ጳጉሜም †††<+>+"*
<< ጾመ ዮዲት - ጾመ ጳጉሜም >>
በቤተክርስቲያናችን የፈቃድ ጾም ተብለው የሚታወቁት ጾመ
ጽጌ እና ጾመ ዮዲት ናቸው። የዮዲት ጾም የሚባለውም እርሷ
ስለ ጾመችው ነው፡፡ ለፋርስ ንጉሥ ለናቡከደነፆር የጦር አበጋዝ
የነበረው ሆሎፎርኒስ ፈቃድ ተሰጥቶት እስራኤልን ለመውረር
ሲመጣ በሠራዊቱ (ዮዲ2፣2-7) የእሥራኤል ልጆችም
ሆሎፎርኒስ የአሕዛብን አገር እንዳጠፋና ንብረታቸውን
እንደዘረፈ ሰምተው ስለ ቤተ መቅደሱ መፍረስና ሰለ ንዋያተ
ቅድሳት መርከሰ ማቅ ለብሰው አመድ ነስንሰው ከቤተ
መቅደሱ በር ወድቀው አለቀሱ።(ዮዲ4፡2-15)
ሆሎፎርኒስ ግን የሚጠጡትን ምንጫቸውን በመያዙ ፣
የእሥራኤል ልጆች በውኃ ጥም ከመቸገርና ከመሞት ይልቅ
እጃቸውን ለጠላት ለመስጠት ወሰኑ፡፡ ነገር ግን ዖዝያን
የአባቶቻቸው አምላክ መልስ እስኪሰጣቸውና ቸርነቱን
እስኪመልስላቸው መከራውን በትዕግሥት እንዲቀበሉ
ስለመከራቸው ጸኑ፡፡ዮዲ7 ፣10-32)
፨ ፨ ፨ ፨ ፨ ፨ ፨ ፨ ፨
በዚያም ባሏ ምናሴ የሞቶባት፣ ከወንድ ርቃ ንጽሕናዋን
ጠብቃ በጾም፣ በቀኖና፣ በትኅርምት፣ በኀዘን፣ በጸሎት ተወስና
የምትኖር የሜራሪ ልጅ ዮዲት ማቅ ለብሳ በራስዋ ላይ ትቢያ
ነስንሳ፣ ሱባዔ ገባች! አምላክም ሕዝቡን የሚያድንበትን
ዕውቀትና ጥበብ ግብር በገባች በሦስተኛ ቀን ገለጸላት፡፡
(ዮዲ8፡2) ከዚያም “ወዴት ትሔጃለሽ አትበሉኝ አምላክ
እሥራኤል ይከተልሽ ብሉኝ” ብላ የኀዘን ልብሷን ጣለች፡፡
ሰውነቷን ታጠበችና ሽቱ ተቀባች፣ ባሏ በሕይወት ሳለ
የምትለብሰውን የክት ልብሷን ለበሰች፣ የጠላት ሰዎች ሁሉ
እስኪወዷት ድረስ ፈጽማ አጊጣ ሄደች፡፡(ዮዲ.10፡2-3 )
እነርሱም ለእኔ ትገባለች ለእኔ ትገባለች እያሉ ተሻሙባት፡፡
የንጉሥ ጃንደረባ ጋይ የሚባል ይህችስ ለጌታዬ ትገባለች አለ፣
ለምን እንደመጣች ጠይቀዋት ለመልካም ነገር እንደመጣች
ሲረዱ ከጦር አበጋዙ አደረሷት፡፡(ዮዲ10፡12 -22)
፨ ፨ ፨ ፨ ፨ ፨ ፨ ፨ ፨
በአንዲትም ዕለት ሆሎፎርኒስ የአሽከሮች የምሣ ግብዣ
አድርጎ ሲያበላ ሲያጠጣ ያችን እብራዊት ጥሩ ብሎ አስጠርቶ
ከፊቱ አስቀምጦ ሲበላ አብዝቶ ሲጠጣ ውሎ ሰከረ፡፡(ዮዲ12፡
1-20 ) ከዚያም አሽከሮችን ከሁሉ አስወጥቶ ድንኳኑን
ቆልፎ እንደተኛ ከባድ እንቅልፍ ያዘው ዮዲትም ከፀለየች
በኋላ ከራስጌው ያለውን ሰይፍ አንስታ የራስ ጠጉሩን ይዛ
አንገቱን ቆርጣ በድኑን ከመሬት ጥላ ቸብቸቦውን በአቁማዳ
ቋጥራ ለብላቴናዋ አሸክማ ግንዱን በታች ገልብጣ ዙፋኑን
በላይ አድርጋ ወደ ሃገሯ ተመለሰች፡፡ (ዮዲ13፡1-10) ሕዝበ
እሥራኤል በዚህ ድርጊቷ እጅግ ተደነቁ፣ ጠላታቸውን
በእጃቸው የጣለላቸውን አግዚአብሔር አምላካቸውንም
አመሰገኑ፡፡ በኋላም የሆሎፎርኒስን ራስ በተራራው ላይ
ሰቅለው መዋጋት ጀመሩ፡፡ እስከዮርዳኖስም እየተከተሉ
አጥፍተዋቸዋል፡፡ ቅድስት ቤ.ክንም እግዚአብሔር የዮዲት
ጾም ተቀብሎ ከጠላት እጅ እንዳዳናቸው፣ ለእኛም ከሰይጻም
ወጥመድ እናመልስ ዘንድ ይህንን ጾም እንጾመው
ታበረታታለች ( የፈቃድ ጾም ነውና)። ለእኛም ለሃገራችን
ፍቅር ሰላምና አንድነትን፣ የመከፋፈልን አዚም
የምንቆርጥበት ጾም ያድርግልን!
በቤተክርስቲያናችን የፈቃድ ጾም ተብለው የሚታወቁት ጾመ
ጽጌ እና ጾመ ዮዲት ናቸው። የዮዲት ጾም የሚባለውም እርሷ
ስለ ጾመችው ነው፡፡ ለፋርስ ንጉሥ ለናቡከደነፆር የጦር አበጋዝ
የነበረው ሆሎፎርኒስ ፈቃድ ተሰጥቶት እስራኤልን ለመውረር
ሲመጣ በሠራዊቱ (ዮዲ2፣2-7) የእሥራኤል ልጆችም
ሆሎፎርኒስ የአሕዛብን አገር እንዳጠፋና ንብረታቸውን
እንደዘረፈ ሰምተው ስለ ቤተ መቅደሱ መፍረስና ሰለ ንዋያተ
ቅድሳት መርከሰ ማቅ ለብሰው አመድ ነስንሰው ከቤተ
መቅደሱ በር ወድቀው አለቀሱ።(ዮዲ4፡2-15)
ሆሎፎርኒስ ግን የሚጠጡትን ምንጫቸውን በመያዙ ፣
የእሥራኤል ልጆች በውኃ ጥም ከመቸገርና ከመሞት ይልቅ
እጃቸውን ለጠላት ለመስጠት ወሰኑ፡፡ ነገር ግን ዖዝያን
የአባቶቻቸው አምላክ መልስ እስኪሰጣቸውና ቸርነቱን
እስኪመልስላቸው መከራውን በትዕግሥት እንዲቀበሉ
ስለመከራቸው ጸኑ፡፡ዮዲ7 ፣10-32)
፨ ፨ ፨ ፨ ፨ ፨ ፨ ፨ ፨
በዚያም ባሏ ምናሴ የሞቶባት፣ ከወንድ ርቃ ንጽሕናዋን
ጠብቃ በጾም፣ በቀኖና፣ በትኅርምት፣ በኀዘን፣ በጸሎት ተወስና
የምትኖር የሜራሪ ልጅ ዮዲት ማቅ ለብሳ በራስዋ ላይ ትቢያ
ነስንሳ፣ ሱባዔ ገባች! አምላክም ሕዝቡን የሚያድንበትን
ዕውቀትና ጥበብ ግብር በገባች በሦስተኛ ቀን ገለጸላት፡፡
(ዮዲ8፡2) ከዚያም “ወዴት ትሔጃለሽ አትበሉኝ አምላክ
እሥራኤል ይከተልሽ ብሉኝ” ብላ የኀዘን ልብሷን ጣለች፡፡
ሰውነቷን ታጠበችና ሽቱ ተቀባች፣ ባሏ በሕይወት ሳለ
የምትለብሰውን የክት ልብሷን ለበሰች፣ የጠላት ሰዎች ሁሉ
እስኪወዷት ድረስ ፈጽማ አጊጣ ሄደች፡፡(ዮዲ.10፡2-3 )
እነርሱም ለእኔ ትገባለች ለእኔ ትገባለች እያሉ ተሻሙባት፡፡
የንጉሥ ጃንደረባ ጋይ የሚባል ይህችስ ለጌታዬ ትገባለች አለ፣
ለምን እንደመጣች ጠይቀዋት ለመልካም ነገር እንደመጣች
ሲረዱ ከጦር አበጋዙ አደረሷት፡፡(ዮዲ10፡12 -22)
፨ ፨ ፨ ፨ ፨ ፨ ፨ ፨ ፨
በአንዲትም ዕለት ሆሎፎርኒስ የአሽከሮች የምሣ ግብዣ
አድርጎ ሲያበላ ሲያጠጣ ያችን እብራዊት ጥሩ ብሎ አስጠርቶ
ከፊቱ አስቀምጦ ሲበላ አብዝቶ ሲጠጣ ውሎ ሰከረ፡፡(ዮዲ12፡
1-20 ) ከዚያም አሽከሮችን ከሁሉ አስወጥቶ ድንኳኑን
ቆልፎ እንደተኛ ከባድ እንቅልፍ ያዘው ዮዲትም ከፀለየች
በኋላ ከራስጌው ያለውን ሰይፍ አንስታ የራስ ጠጉሩን ይዛ
አንገቱን ቆርጣ በድኑን ከመሬት ጥላ ቸብቸቦውን በአቁማዳ
ቋጥራ ለብላቴናዋ አሸክማ ግንዱን በታች ገልብጣ ዙፋኑን
በላይ አድርጋ ወደ ሃገሯ ተመለሰች፡፡ (ዮዲ13፡1-10) ሕዝበ
እሥራኤል በዚህ ድርጊቷ እጅግ ተደነቁ፣ ጠላታቸውን
በእጃቸው የጣለላቸውን አግዚአብሔር አምላካቸውንም
አመሰገኑ፡፡ በኋላም የሆሎፎርኒስን ራስ በተራራው ላይ
ሰቅለው መዋጋት ጀመሩ፡፡ እስከዮርዳኖስም እየተከተሉ
አጥፍተዋቸዋል፡፡ ቅድስት ቤ.ክንም እግዚአብሔር የዮዲት
ጾም ተቀብሎ ከጠላት እጅ እንዳዳናቸው፣ ለእኛም ከሰይጻም
ወጥመድ እናመልስ ዘንድ ይህንን ጾም እንጾመው
ታበረታታለች ( የፈቃድ ጾም ነውና)። ለእኛም ለሃገራችን
ፍቅር ሰላምና አንድነትን፣ የመከፋፈልን አዚም
የምንቆርጥበት ጾም ያድርግልን!
=>+*"+<+>††† ጳጉሜ፦3 ቅዱስ ሩፋኤል †††<+>+"*
ጳጉሜ፦3
ቅዱስ ሩፋኤል
ሥንክሳር፦
1)የስሙ ትርጉም፦ "የእግዚአብሔር መድኃኒት"
2)ምድብ፦ ከ7ቱ ሊቃነ-መላእክት እንዱ።
3)ትውልድ፦ መላእክት የሥጋ ልደትና ሞት የለባቸውም
(ለመጠቆም ያክል ነው)
4)ዓቢይ ተልእኮ፦ ፈታሄ ማህፀን፣ ሕክምና፣ የቀንና የዓመታዊ
የሰዎችን ሥራ ለእግዚአብሔር ዘገባ ማቅረብ፣ የሌሊት
3ሰዓት ተረኛ ጥበቃ፣ ከአውሬዎች ጥበቃ፣ መንገድ መምራትና
ሌሎችም፤
5)ተኣምር፦"ከከበሩት ከሰባቱ ሊቃነ መላእክት አንዱ እኔ
ሩፋኤል ነኝ" እንዳለ:: ጦቢት 12፥13
እንግዲህ ከባህሪው ቅድስና ፍጥረቱን በጸጋ ቅድስና መርጦ
የሚለይ እግዚአብሔር አክብሮ እንዲህ ያለ ሰማያዊ ፀጋ
ከሰጣቸው ቅዱሳን መላእክት መካከል በስልጣኑ
ሊቀመናብርት (የመናብርት አለቃ) የሆነ በሹመት ፈታሔ
ማኅጸን (ማሕጸን የሚፈታ) ከሳቴ እውራን (የእውራንን ዓይን
የሚያበራ) ሰዳዴ አጋንንት (አጋንንትን የሚያባርር) ፈዋሴ
ዱያን (ድውያንን የሚፈውስ)፣ አቃቤ ኆኅት (የምህረትን ደጁ
የሚጠብቅ) ተብሎ የተገለጠ ከሊቃነ መላእክቱ ቅዱስ
ሚካኤልና ቅዱስ ገብርኤል ተከትሎ የሚነሳ መልአክ ራሱን
እንዲህ በማለት ገለጠ « የቅዱሳንን ጸሎት ከሚያሳርጉ ወደ
ከበረ ወደ ገነነ ወደ እግዚአብሔር ጌትነት ከሚያገቡ ከከበሩ
ከሰባቱ አለቆች አንዱ አለቃ እኔ ሩፋኤል
ነኝ» (ጦቢ.12÷15)
ይህ የከበረ ታላቅ መልአክ ሰሙ ሩፋኤል የሚለው ከአምላክ
ለሰዎች የተሰጠ ፈውስ የሚለውን ይተካል «በሰው ቁስል
የተሾመ ከከበሩ ከመላእክት አንዱ ሩፋኤል ነው፡» (ሄኖ.6÷3)
ይህ መልአክ እንደሌሎቹ ሊቃነ መላእክት ሁሉ የሰው ልጆችን
ይጠብቃቸዋል(ዳን.4÷13 ዘጸ. 23÷20 መዝ.
90÷11-13 )
ያማልዳል፣ ከፈጣሪ ያስታርቃቸዋል፡፡(ዘካ.1 ÷12)
በፈሪሀ እግዚአቤሔር እና በአክብሮተ መላእክት ያሉትን
ያድናቸዋል (ዘፍ.49÷15 መዝ.3÷37)
« እግዚአብሔር ሃይሉን የሚገልጥበትን ቅጣቱን ሊያሳይ
ቢወድ አስቀድሞ መርጦ በወደዳቸው ለይቅርታ የተዘጋጁ
የይቅርታ መላእክትን ያመጣል» (ሮሜ.9÷22)
የወላድ ማኅፀን እንዲፈታ ስለተሸመ ከጌታ አዋላጅ ብትኖርም
ባትኖርም ሐኪም ሩፋኤል አይታጣም በምጥ ጊዜ ሲጨነቁ
ሴቶች ሁሉ የመልአኩን መልክ አንግተው ማርያም ማርያም
ይላሉ ማየጸሎቱን ጠጥተው ቶሎ ፈጥነው ይወልዳሉ እያሉ
ደጅ ጠንተው ይማጸኑታል፡፡
ዜና ግብሩን ሊቁ ዮሐንስ አፈወርቅ ከተናገረለት በመነሳት
በቅዱሳን ላይ ድንቅ የሆነ እግዚአብሔር በመልአኩ አድሮ
ያደረጋቸውን ተግባራት አበው የበረከት ምንጭ በሆነ ድርሳኑ
ላይ አኑረው የበረከቱ ተካፋይ እንድንሆን ሰጥተውናል፡፡
በጉልህ ሠፍረው ከምናገኛቸው ብዙ ድንቅ ሥራዎች መሀል
ጥቂቶቹን እነሆ፦
~> በሥነ-ስዕሉ የተማጸኑ፣ በምልጃው ታምነው የጸኑ
ቴዎዶስዮስንና ዲዮናስዮስን በገሃድ ተገልጾ ለንግስናና ለጵጵስና
ክብር አብቅቷቸዋል፡፡
~> የንጉስ ቴዎዶስዮስ ልጅም ጻድቁ አኖሬዋስም በፈጣሪው
ህግ እየተመራ የሊቀ መናብርቱን መታሰቢያ ቤተ መቅደስ
አሳንጾ ሲያስመርቅ ለበለጠ ክብር ልቡን አነቃቅቶ ለታናሽ
ወንድሙ ለአርቃዴዋስ የነጋሢነት ስልጣኑን ትቶ መንኖ
በስውርና በጽሙና እዲኖር ረድቶታል፡፡
~> በሊቀጳጳሳት ቴዎፍሎስ ዘመን አባቶች ለሊቀመናብርቱ
ክብር በአሣ አንበሪ ጀርባ ላይ ያሳነጹትን መታሰቢያ ቤተ
መቅደስ በወደቡ አጠገብ በእስክንድሪያ ሳለች ጠላት ዲያቢሎስ
አነዋውጾ ለምስጋና የታደሙትን ምዕመናን ሊያጠፉ አሣ
አንበሪውን ቢያውከው ወደ ሊቀመናብርቱ ተማጽነው እርዳን
ቢሉ ፈጥኖ ደርሶ በበትረ መስቀሉ (ዘንጉ) ገሥጾ ከጥፋት
ታድጓቸዋል፡፡
በቅዱስ መጽሐፍም እንደተገለጠው
~> ሣራ ወለተ ራጉኤልን አስማንድዮስ ከተባለው የጭን
ጋንኤን ሲታደጋት የጦቢያን አባት የጦቢትን ዓይን አበራለት
(መጽሐፍ ጦቢት)
ከዚህም አልፎ የይስሐቅን እናት ሣራን፣ የሶምሶንን እናት
(እንትኩይን) ምክነታቸውን የቆረጠ ወልዶ ለመሳም
ያበቃቸው ይኸው ፈታሔማኅጸን የልዑል እግዚአብሔር
መልአክተኛ ቅዱስ ሩፋኤል ነው፡፡
የመልአኩ ጥበቃና የክንፎቹ መጋረድ ከተዋህዶ ምእመናን
ጋር! አሜን!
ለቅዱሳን ክብርን ከማይሰጥ ከተሸወደ ትውልድ ያድነን!
ቅዱስ ሩፋኤል
ሥንክሳር፦
1)የስሙ ትርጉም፦ "የእግዚአብሔር መድኃኒት"
2)ምድብ፦ ከ7ቱ ሊቃነ-መላእክት እንዱ።
3)ትውልድ፦ መላእክት የሥጋ ልደትና ሞት የለባቸውም
(ለመጠቆም ያክል ነው)
4)ዓቢይ ተልእኮ፦ ፈታሄ ማህፀን፣ ሕክምና፣ የቀንና የዓመታዊ
የሰዎችን ሥራ ለእግዚአብሔር ዘገባ ማቅረብ፣ የሌሊት
3ሰዓት ተረኛ ጥበቃ፣ ከአውሬዎች ጥበቃ፣ መንገድ መምራትና
ሌሎችም፤
5)ተኣምር፦"ከከበሩት ከሰባቱ ሊቃነ መላእክት አንዱ እኔ
ሩፋኤል ነኝ" እንዳለ:: ጦቢት 12፥13
እንግዲህ ከባህሪው ቅድስና ፍጥረቱን በጸጋ ቅድስና መርጦ
የሚለይ እግዚአብሔር አክብሮ እንዲህ ያለ ሰማያዊ ፀጋ
ከሰጣቸው ቅዱሳን መላእክት መካከል በስልጣኑ
ሊቀመናብርት (የመናብርት አለቃ) የሆነ በሹመት ፈታሔ
ማኅጸን (ማሕጸን የሚፈታ) ከሳቴ እውራን (የእውራንን ዓይን
የሚያበራ) ሰዳዴ አጋንንት (አጋንንትን የሚያባርር) ፈዋሴ
ዱያን (ድውያንን የሚፈውስ)፣ አቃቤ ኆኅት (የምህረትን ደጁ
የሚጠብቅ) ተብሎ የተገለጠ ከሊቃነ መላእክቱ ቅዱስ
ሚካኤልና ቅዱስ ገብርኤል ተከትሎ የሚነሳ መልአክ ራሱን
እንዲህ በማለት ገለጠ « የቅዱሳንን ጸሎት ከሚያሳርጉ ወደ
ከበረ ወደ ገነነ ወደ እግዚአብሔር ጌትነት ከሚያገቡ ከከበሩ
ከሰባቱ አለቆች አንዱ አለቃ እኔ ሩፋኤል
ነኝ» (ጦቢ.12÷15)
ይህ የከበረ ታላቅ መልአክ ሰሙ ሩፋኤል የሚለው ከአምላክ
ለሰዎች የተሰጠ ፈውስ የሚለውን ይተካል «በሰው ቁስል
የተሾመ ከከበሩ ከመላእክት አንዱ ሩፋኤል ነው፡» (ሄኖ.6÷3)
ይህ መልአክ እንደሌሎቹ ሊቃነ መላእክት ሁሉ የሰው ልጆችን
ይጠብቃቸዋል(ዳን.4÷13 ዘጸ. 23÷20 መዝ.
90÷11-13 )
ያማልዳል፣ ከፈጣሪ ያስታርቃቸዋል፡፡(ዘካ.1 ÷12)
በፈሪሀ እግዚአቤሔር እና በአክብሮተ መላእክት ያሉትን
ያድናቸዋል (ዘፍ.49÷15 መዝ.3÷37)
« እግዚአብሔር ሃይሉን የሚገልጥበትን ቅጣቱን ሊያሳይ
ቢወድ አስቀድሞ መርጦ በወደዳቸው ለይቅርታ የተዘጋጁ
የይቅርታ መላእክትን ያመጣል» (ሮሜ.9÷22)
የወላድ ማኅፀን እንዲፈታ ስለተሸመ ከጌታ አዋላጅ ብትኖርም
ባትኖርም ሐኪም ሩፋኤል አይታጣም በምጥ ጊዜ ሲጨነቁ
ሴቶች ሁሉ የመልአኩን መልክ አንግተው ማርያም ማርያም
ይላሉ ማየጸሎቱን ጠጥተው ቶሎ ፈጥነው ይወልዳሉ እያሉ
ደጅ ጠንተው ይማጸኑታል፡፡
ዜና ግብሩን ሊቁ ዮሐንስ አፈወርቅ ከተናገረለት በመነሳት
በቅዱሳን ላይ ድንቅ የሆነ እግዚአብሔር በመልአኩ አድሮ
ያደረጋቸውን ተግባራት አበው የበረከት ምንጭ በሆነ ድርሳኑ
ላይ አኑረው የበረከቱ ተካፋይ እንድንሆን ሰጥተውናል፡፡
በጉልህ ሠፍረው ከምናገኛቸው ብዙ ድንቅ ሥራዎች መሀል
ጥቂቶቹን እነሆ፦
~> በሥነ-ስዕሉ የተማጸኑ፣ በምልጃው ታምነው የጸኑ
ቴዎዶስዮስንና ዲዮናስዮስን በገሃድ ተገልጾ ለንግስናና ለጵጵስና
ክብር አብቅቷቸዋል፡፡
~> የንጉስ ቴዎዶስዮስ ልጅም ጻድቁ አኖሬዋስም በፈጣሪው
ህግ እየተመራ የሊቀ መናብርቱን መታሰቢያ ቤተ መቅደስ
አሳንጾ ሲያስመርቅ ለበለጠ ክብር ልቡን አነቃቅቶ ለታናሽ
ወንድሙ ለአርቃዴዋስ የነጋሢነት ስልጣኑን ትቶ መንኖ
በስውርና በጽሙና እዲኖር ረድቶታል፡፡
~> በሊቀጳጳሳት ቴዎፍሎስ ዘመን አባቶች ለሊቀመናብርቱ
ክብር በአሣ አንበሪ ጀርባ ላይ ያሳነጹትን መታሰቢያ ቤተ
መቅደስ በወደቡ አጠገብ በእስክንድሪያ ሳለች ጠላት ዲያቢሎስ
አነዋውጾ ለምስጋና የታደሙትን ምዕመናን ሊያጠፉ አሣ
አንበሪውን ቢያውከው ወደ ሊቀመናብርቱ ተማጽነው እርዳን
ቢሉ ፈጥኖ ደርሶ በበትረ መስቀሉ (ዘንጉ) ገሥጾ ከጥፋት
ታድጓቸዋል፡፡
በቅዱስ መጽሐፍም እንደተገለጠው
~> ሣራ ወለተ ራጉኤልን አስማንድዮስ ከተባለው የጭን
ጋንኤን ሲታደጋት የጦቢያን አባት የጦቢትን ዓይን አበራለት
(መጽሐፍ ጦቢት)
ከዚህም አልፎ የይስሐቅን እናት ሣራን፣ የሶምሶንን እናት
(እንትኩይን) ምክነታቸውን የቆረጠ ወልዶ ለመሳም
ያበቃቸው ይኸው ፈታሔማኅጸን የልዑል እግዚአብሔር
መልአክተኛ ቅዱስ ሩፋኤል ነው፡፡
የመልአኩ ጥበቃና የክንፎቹ መጋረድ ከተዋህዶ ምእመናን
ጋር! አሜን!
ለቅዱሳን ክብርን ከማይሰጥ ከተሸወደ ትውልድ ያድነን!
Thursday, August 18, 2016
=>+*"+<+>††† ምሥጢረ ደብረ ታቦር †††<+>+"*
ምሥጢረ ደብረ ታቦር!
(መቅረዝ ዘተዋሕዶ .)፡- ጌታችንና መድኃኒታችን ኢየሱስ
ክርስቶስ በፊሊጶስ ቂሳርያ ለደቀመዛሙርቱ “ሰዎች የሰውን
ልጅ ማን ይሉታል?” ብሎ ጠይቋቸው ነበር፡፡ እነርሱም
“አንዳንዶች ከእናቱ ማኅፀን ጀምሮ ቅዱስ ነውና ኤርሚያስ
ነው ይሉሀል፤ አንዳንዶቹ ድንቅ የሆነ ልደትህንና
የምታጠምቀውን አዲስ ጥምቀት አይተው መጥምቁ ዮሐንስ
ነው ይሉሀል፤ ሌሎች ደግሞ ለአባቶችህ ቤት ያለህን ቅናት
አይተው ኤልያስ ነው ይሉሃል” እያሉ መልሰውለት ነበር፡፡
ጌታችንም መልሶ፡- “እናንተስ ማን ትሉኛላችሁ?” ብሎ
ጠየቃቸው፡፡ የሐዋርያት አፈጉባዔ የሚሆን ሊቀ ሐዋርያት
ቅዱስ ጴጥሮስም “አንተክርስቶስ የሕያው እግዚአብሔር አብ
የባሕርይ ልጅ ነህ” ብሎ መልሷል፡፡ ጌታም “የዮና ልጅ
ስምዖን ሆይ በሰማይ ያለው አባቴ እንጂ ሥጋና ደም
(ምድራዊ መምህር) ይህን አልገለጠልህምና ብፁዕ ነህ”
ብሎታል፡፡
ከዚህ በኋላ ጌታችን በኢየሩሳሌም ካህናት ሊቀካህናት ጸሐፍት
ፈሪሳውያን ስለሚያደርሱበት መከራ ስለሚሞተው ሞት
ይነግራቸው ጀመር፡፡ ሰይጣንም አስቀድሞ በቀዳማይቱ
ሔዋን እንዳደረገው አሁንም በስምዖን ጴጥሮስ አንደበት
ወዳጅ መስሎ “አይሆንም አይደረግም” በማለት መከራከር
ጀመር፡፡ ጌታችን ግን ጴጥሮስን አድርጎ ሰይጣንን ይገስጸው
ጀመር፡- “ጴጥሮስ ሆይ! የእኔ አመመጣጥ ለምን እንደሆነ
አታስተውልምን? የዮና ልጅ ስምዖን ሆይ! በቤተልሔም
ተወልጄ ከሴቶች ለሚወለዱ ሕፃናት ሁሉ ደስታ
እንደሆንኩላቸው አሁንም የእኔን እዚያ መውረድ እየተጠባበቁ
የሚገኙትን ቅዱሳን ወደ ገነት እመልስ ዘንድ ሲዖል መሄድ
አለብኝ፡፡ ብዙዎች ነቢያትና ጻድቃን ይህን ሊያዩ ይመኛሉና፤
አብርሃም ቀኔን ያይ ዘንድ ይናፍቃልና፡፡ ስለዚህ አያቸው ዘንድ
መውረድ አለብኝ፤ እጎበኛቸው ዘንድ ልሞት ልሰቀል
ይገባኛል፡፡ በእውነት ሰይጣን ካልሆነ በቀር የእኔን መሰቀል
የሚቃወም የነፍሳትም ነፃ መውጣት የማይናፍቅ ማን ነው?
አንተ ጴጥሮስ! ይህን ሁሉ የምትለኝ ሰይጣን በአንተ ተመስሎ
አንድም አንተው ራስህ ለእኔ ካለህ ፍቅር የተነሣ መሆኑን
ብረዳም ጀሮህ ትንቢተ ነቢያትን ባይሰማ ይልቁንም ዓሣ
ማጥመድን ብቻ ስለሚያውቅ ነውና ወግድ” አለው፡፡
ይህም በሆነ በሰባተኛው ቀን ሦስቱን ደቀ መዛሙርት
ማለትም ጴጥሮስ፣ ዮሐንስንና ያዕቆብን ይዞ ወደ ታቦር
ተራራ ወጣ፡፡ ክርስቶስ ባይሞት እንዴት ያለ ክብር
እንደሚቀርባቸው ያሳያቸው ዘንድ ምስክርም እንዲሆኑ
እነዚህን ሦስቱ ደቀ መዛሙርት ይዞ ወጣ፡፡ በዚያም እንደ
ዮርዳኖስ ወንዝ መድኃኔዓለም ክብረ መንግሥቱን፣ ብርሃነ
መለኮቱን ገልጠላቸው፡፡ በየዓመቱ ነሐሴ 13 ቀን ቤተ
ክርስቲያናችን ከምታከብራቸው ዘጠኙ ዐበይት የጌታ በዓላት
አንዱ የሆነው በዓለ ደብረታቦር የዚህ ታሪክ መታሰቢያ ነው ፡፡
በዚህ ዕለት ሕፃናት ጅራፋቸውን ገምደው እያስጮኹ
ይጨፍራሉ፡፡ ይኸውም ጅራፍ ሲጮህ እንደሚያስደነግጥ ሁሉ
ከጌታ ጋር የነበሩት ሦስቱ ደቀ መዛሙርትም አብ በደመና
ሆኖ ሲናገር መደንገጣቸውንና መውደቃቸውን የሚያስታውስ
ነው፡፡
ታቦር ተራራ ከገሊላ ባሕር በምዕራራባዊ ደቡብ በኵል 10
ኪሎ ሜትር ርቀት ላይ፣ ከናዝሬት ከተማ በስተምሥራቅ፣
ከዮርዳኖስ ወንዝ በስተምዕራብ አቅጣጫ የሚገኝ ተራራ
ነው፡፡ ተራራው ከባሕር ወለል በላይ 572 ከፍታ አለው፡፡
ብዙ ሰዎች ከላይ ወደታች ሲታይ ታቦር ተራራ ቅርጹ
የተገለበጠ የሻይ ስኒ ይመስላል ይላሉ ፡፡
ምሥጢረ መንግሥቱን ለምን በታቦር ተራራ ገለጸው?
መድኃኔዓለም ሌሎች ተራሮች እያሉ ክብሩን ለመግለጥ
ስለምን ደብረ ታቦርን መረጠ ቢሉ ትንቢቱንና ምሳሌውን
ለመፈጸም ነው፡፡
1. ትንቢቱን ለመፈጸም
“ታቦርና አርሞንኤም በስምህ አምነው በተደረገላቸው ነገር
ደስ ይላቸዋል፣ ስምህን ያመሰግናሉ፣ ለስምህም ምስጋና
ያቀርባሉ” እንዲል /መዝ. 88፡12/፡፡ 2. ምሳሌውን
ለመፈጸም
ይህ ተራራ ባርቅ ሲሳራን ድል አድርጎበታል /መሳ.4፡6/፡፡
ታሪኩም እንዲህ ነው፡፡ “የእስራኤል ልጆች በእግዚአብሔር
ፊት እንደገና ክፉ ሥራ ሠሩ፡፡እግዚአብሔርም በአሶር
በነገሠው በከነዓን ንጉሥ በኢያቡስ እጅ አሳልፎ ሰጣቸው፤
የሠራዊቱም አለቃ በአሕዛብ አሪሶት የተመረጠው ሲሣራ
ነበር፡፡… ዘጠኝ መቶ የብረት ሰረገሎች ነበሩትና
የእስራኤልንም ልጆች ሃያ ዓመት ያስጨንቃቸው ነበር” /
መሳ 4.1-3/፡፡ ሁሌም ቢሆን የሰውን በደል
ዐይቶእንደወጣችሁ ግቡት፣ እንደገባችኋት ውጧት የማይልና
“ከፈተናው ጋር መውጫውን ደግሞ ያደርግላችኋል”
የተባለለት እግዚአብሔር ከዚህ ቀንበርየሚላቀቁበትን መላ
ራሱ አመለከታቸው /1ቆሮ. 10-13/፡፡ እስራኤላውያን ወደ
ፈጣሪያቸው በጮኹ ጊዜ የለፊዶት ሚስት የሆነችውንና
እስራኤልን በነቢይነትና ዳኝነት ታገለግል የነበረችው ነቢይቱን
ዲቦራን ተጠቅሞ የማሸነፊያ መላውን አመለከታቸው፡፡
ነቢይቱ ዲቦራ ትንቢት ከመናገር አልፋ የእስራኤልን ንጉሥ
ባርቅ ከእኔ ጋር ወደ ጦርነቱ ውጪ ብሎ ባስጨነቃት ጊዜ
በጦር አዝማችነትም ተሳተፈች፡፡ እግዚአብሔር በነቢይቱ
በዲቦራ በኩል ለእስራኤል ንጉሥ “ሔደህ ወደ ታቦር ተራራ
ውጡ” ብሎ አዞት ነበርና ንጉሡ ዐሥር ሺሕ ብረት ለበስ
ያልሆነ እግረኛ ሠራዊት ይዞ ደብረ ታቦርን ተማምኖ
በተራራው ላይ መሸገ፤ ጦርነቱም ሳይጀመር አለቀ፡፡
ምክንያቱም “እግዚአብሔርም ሲሣራን ሰረገሎቹንም ሁሉ
ሠራዊቱንም ሁሉ ከባርቅ ፊት በሰይፍ ስለት አስደነገጣቸው፡፡
ሲሣራም ከሰረገላው ወርዶ በእግሩ ሸሸ” /መሳ. 4.15/፡፡
እስራኤል በእግዚአብሔር አጋዥነት በታቦር ተራራ ላይ የሃያ
ዓመት የግፍና የሰቀቀን አገዛዝ ቀንበራቸውን ከትከሻቸው
አሽቀንጥረው በምትኩ የድል ካባን ደረቡ፡፡ “በጦርነት
ኃይለኞች ሆኑ የባዕድ ጭፍሮችንም አባረሩ” ተብሎም
ጀግንነታቸው ተጻፈላቸው፡፡ የታቦር ተራራ ያኔ እንደ
እግዚአብሔር ፈቃድ ባለውለታቸው ነበር /ዕብ.
11.32-34/፡፡ ጌታም በልበ ሐዋርያት ያለ ሰይጣንን ድል
ያደርግበታልና ማለትም በልባቸው ጥርጥርን እና ፍቅረ
ሢመትን( የሥልጣን ፍቅር) ያሳደረ ዲያብሎስን ድል
ነስቶላቸዋል፡፡ ከዚህም በመነሣት ነው “በዓለ ደብረታቦር
የደቀመዛሙርት ተማሪዎች በዓል ነው” የሚባለው ፡፡
ለምን ሦስቱን ሐዋርያት ብቻ ይዞ ወጣ?
1. ጌታ “እሞታለሁ፤ እሰቀላለሁ” ባለው ጊዜ ጴጥሮስ
“ልትሞት አይገባም፤ ይህ ላንተ አይገባም” ብሎ ተቃውሞት
ነበርና በአብ ቃል “እርሱ ያላችሁን ስሙት፤ ይህ ለአንተ
አይገባም አትበሉት፤ አትቃወሙት” ለማለት፡፡
2. ጌታ “እናንተስ ማን ትሉኛላችሁ?” ብሎ ደቀመዛሙርቱን
በጠየቃቸው ጊዜ ጴጥሮስ “አንተ የሕያው የእግዚአብሔር
ልጅ ነህ” ብሎት ነበርና አሁንም አብ “አዎ ልክ ነህ!
እመለክበት ዘንድ ለተዋሕዶ የመረጥኩት የምወደው ልጄ ይህ
ነው” ብሎ ለማረጋገጥ፡፡
3. ለፍቅሩ ስለሚሳሱ ነው፡፡ ይህም በዕብራይስጡ ኬፋ ፤
በግሪኩ ጴጥሮስ ፤ በግዕዙ ኰኲሕ (ዐለት) የተባለው የዮና
ልጅ ስምዖን ጌታችን “እሞታለሁ” እያለ ሲናገር
“አይሁንብህ” ማለቱ አስቀድመን እንደተናገርን “ለጌታ ካለው
ፍጹም ፍቅር የተነሣ ነው” ይላል ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ፡፡
ዮሐንስም በወንጌል “የጌታ ወዳጅ” ተብሎ ተጽፏል፡፡ ያዕቆብ
ደግሞ ጌታን በእጅጉ እንደሚወደው በኋላ ታውቋል፡፡
ይኸውም “እኔ የምጠጣውን ጽዋ ትጠጣላችሁ?” /ማቴ.20፡
20/ ሲባሉ“አዎ” ብሎ መመለሱና በዚህም በሄሮድስ
ዘአግሪጳ ሰማዕት ሆኖ መሞቱ ምስክር ነው፡፡
4. በይሁዳ ምክንያት ነው፡፡ “ኃጥእ ሰው የእግዚአብሔርን
ክብር እንዳያይ ያርቁታል” እንዲል /ኢሳ 26:13/ እርሱን
ጥሎ አሥራ አንዱን ወደ ተራራ ይዞ ቢወጣ ከምሥጢር
ቢለየኝ በሞቱ ገባሁበት እንዳይል፡፡ ያም ባይሆን ስምንቱ ደቀ
መዛሙርት ለምን ይከለከላሉ ቢሉ አልተከለከሉም በርዕሰ
ደብር (በተራራው አናት)ለሦስቱ ደቀ መዛሙርት የተገለጸው
ምስጢር በእግረ ደብር (በተራራው ግርጌ) ለነበሩት ስምንቱ
ደቀ መዛሙርት ተገልጦላቸዋል፡፡ ይህም በደብረሲና
ለሰባውሊቃናት የተገለጠ ምሥጢር በከተማ ለነበሩት
ለኤልዳድና ሙዳድ እንደተገለጠ ማለት ነው /ዘኁ.11፡26/፡፡
ኤልያስና ሙሴን ለምን አመጣቸው?
1. በአንድ ወቅት ሙሴ እግዚአብሔርን ፡- “በአንተ ዘንድ
ባለሟልነትን ማግኘቴ እውነት ከሆነስ ፊት ለፊት ተገልጸህልኝ
ልይህና በአንተ ዘንድ ባለሟልነትን ማግኘቴን ልወቀው” ሲል
ጠይቆት ነበር፡፡ እግዚአብሔርም “ጀርባዬን ታያለህ ፊቴን
ግን አታይም” ብሎት ነበር /ዘጸ. 33.13፣23/፡፡ የዚህ ኃይለ
ቃል ትርጓሜናሐተታ በደብረ ታቦር ተፈጽሟል፡፡ እንዲህ
ማለቱ “አምስት ሺሕ አምስት መቶ ዘመን ሲፈጸም ሰው
ሆኜ ሥጋ ለብሼ ኋላ በደብረ ታቦር እስክገለጽልህ ድረስአንተ
በመቃብር ተወስነህ ትኖራለህ” ማለቱ ነበርና፡፡ ይህን ማለቱ
እንደሆነ የታወቀው ግን በደብረ ታቦር ሙሴን ከብሔረ
ሙታን በአካለ ነፍስ አምጥቶ ባቆመው ጊዜ ነበር፡፡
2. ልዑል እግዚአብሔር ነቢዩ ኤልያስን፡- “አንተ በኋለኛው
ዘመን ምስክር ትሆነኛለህ” ብሎት ነበር፡፡ ይኸውም ኃይለ
ቃል ኤልያስ ከብሔረ ሕያዋን መጥቶ “የእኔን የኤልያስን ጌታ
ማን ኤልያስ ነው ይልሃል? እግዚአ ኤልያስ፤ አምላከ ኤልያስ
ይበሉህ እንጂ” ሲል በደብረ ታቦር ተፈጸመ፡፡ ታያለህ የተባለው
ሙሴም አየ፣ትመሰክራለህ የተባለው ኤልያስም መሰከረ፡፡ 3.
በፊልጶስ ቂሳርያ ጌታ ሐዋርያትን “ሰዎች የሰውን ልጅ ማን
እንደሆነ ይሉታል?” ብሎ በጠየቃቸው ጥያቄ ሲመልሱ
“ሙሴ ነው ይሉሃል ፤ እንዲሁም የኃይልሥራህን ተመልክተው
ኤልያስ ነው ይሉሃል” ብለው ነበርና ሙሴን ከመቃብር ፤
ኤልያስን ከብሔረ ሕያዋን አምጥቶ እግዚአ ሙሴ ፤ አምላከ
ሙሴ ፤ እግዚአኤልያስ ፤ አምላከ ኤልያስ መሆኑን
ለማስመስከር፡፡
4. አይሁድ ፈሪሳውያን ጌታን እንደ ሕግ ተላላፊና
የእግዚአብሔርን ክብር ለራሱ የሚወስድ አድርገው ያስቡት
ስለነበረ /ዮሐ.9፡16፣ 10፡33/ ሕግን የሰጣቸው ሙሴንና
ለሕገ እግዚአብሔር ቀናተኛ የነበረው ኤልያስን አምጥቶ ሕግ
አፍራሽ አለመሆኑን የእግዚአብሔር ተቃዋሚም አለመሆኑን
ለማስረገጥ፡፡
5. ጌታችን በሙታንና በሕያዋን ላይ ሥልጣን ያለው እንደሆነ
ይታወቅ ዘንድ ሞተው ከተቀበሩት ሙሴን ከብሔረ
ሕያዋንም አልያስን አምጥቶ ሲነጋገር ታየ፡፡
6. የሐዋርያቱን የወደፊት አገልግሎት ሲነግራቸው፡፡
ይኸውም ሙሴ እና ኤልያስ ለሕዝበ እስራኤል በጣም ታማኝ
እንደነበሩ ሁሉ እነርሱም ለሚያገለግሉት ሕዝብ ታማኝ
እረኞች እንዲሆኑ፡፡ ሆኖም ግን አገልግሎታቸው ከሙሴና
ከኤልያስ ይልቅ ጠንከር እንደሚልም አሳይቶአቸዋል፡፡
ምክንያቱም ውጊያቸው እንደ ሙሴ ከፎርዖን እንደ ኤልያስም
ከአክዓብ ጋር ሳይሆን ከክፋት መናፍስት ጋር ነውና፡፡
7. ጽድቃቸው ከእነዚህ ከሙሴና ከኤልያስ የበለጠ ሊሆን
እንደሚገባ ለማሳየት /ማቴ.5፡20/፡፡ ምክንያቱም ሙሴ
ሕዝበ እስራኤልን ቢመራ ምድረ ፍልሥጥኤምን ለማውረስ
ነው፡፡ እነዚህ ግን ሕዝቡን መርተው የሚያስገቡት መንግሥተ
ሰማያትን ነው፡፡ ኤልያስ ሰማያትን ቢለጉምም ከጊዜአዊ
ዝናም ነው፡፡ እነዚህ ግን ለዘለዓለም መንግሥተ ሰማያትንም
የመለጎም ሥልጣን አላቸውና፡፡
ከዚህ በኋላ ጴጥሮስ “ጌታ ሆይ በዚህ መሆን ለእኛ መልካም
ነው” ሲል ተደምጧል፡፡ ይህም የተለያየ ትርጉም አለው፡፡
ቃል በቃል (Literaly)ስናየው ቅዱስጴጥሮስ ጌታ ሆይ በዚህ
መኖር ለእኛ መልካም ነው ማለቱ “አንተ እያበላኸን
እየፈወስከን፣ ሙሴ እነዚህ መከራ ያደርሱቡኛል ይገድሉኛል
ያልካቸውን ጸሐፍትና ፈሪሳውያን እንዳይመጡ በደመና
እየጋረደ፣ ቢመጡም አልያስ እሳት እያዘነመ እያባረራቸው
በዚህ መኖር ለእኛ መልካም ነው” ማለቱ ሲሆን
ምሥጢራዊው መልእክቱ ግን “የኢየሱስ ክርስቶስ የባሕርይ
አምላክነት በሚታመንበት፣ ወልድ ዋሕድ በምትለው
ሃይማኖት መኖር ለእኛ መልካም ነው፡፡ ሰይጣን ድል
በተደረገባት በታቦር ተራራ ምሳሌም በምትሆን በወንጌል
ሕይወት፣ አንድም በቤተ ክርስቲያን መኖር ለእኛ መልካም
ነው” ማለቱ ነው፡፡
ታቦር ተራራ የወንጌል ምሳሌ ነው!
ተራራ ሲወጡት ያደክማል፣ ከወጡት በኋላ ግን ጭንጫውን፣
ግጫውን ሲያሳይ ደስ ያሰኛል፡፡ ወንጌልም ሲማሯት
ትከብዳለች በኋላ ግን ጽድቅን እና ኃጢአትን ለይታ ስታሳውቅ
ደስ ታሰኛለች፡፡
ታቦር ተራራ የቤተክርስቲያን ምሳሌ ነው!
ሀ. በታቦር ተራራ ከብሉይ ኪዳን ነቢያት ኤልያስና ሙሴን፣
ከሐዲስ ኪዳን ሦስቱን ሐዋርያት እንደተገኙ በቤተክርስቲያን
ብሉይ ከሐዲስ እንዲነገር ያጠይቃል፤ ሐዋርያት የሰበኩት
ወንጌል አስቀድመው ነቢያት በምሳሌና በትንቢት የተናገሩት
እንደሆነ ያስረዳል፡፡ “ነቢያት በቀየሱ ሐዋርያት ገሰገሱ”
እንዲል ጳውሎስም“በሐዋርያት በነቢያት መሠረት ላይ
ታንጻችኋል” ይላልና /ኤፌ 2፣20/፡፡
ለ. በታቦር ተራራ ከመዓስባን (ባለትዳር) ሙሴን ከደናግል
ደግሞ ኤልያስ እንደተገኙ በቤተክርስቲያን በድንግልና
የሚኖሩ መናንያን መነኮሳት፣ በሕግ በሥርዓትየሚኖሩ
ባለትዳሮችም ይገኛሉና፡፡
ታቦር ተራራ የመንግሥተ ሰማያት ምሳሌ ነው!
1. ተራራ በብዙ ችግር እንዲወጡት ወደ እግዚአብሔር
መንግሥትም በብዙ መከራ እንገባ ዘንድ ያስፈልገናልና /ሐዋ
14፡22/፡፡
2. በታቦር ተራራ የብሉይ ኪዳን ነቢያት ከሐዲስ ኪዳንም
ሐዋርያት እንደተገኙ መንግሥተ ሰማያትን ነቢያትም፣
ሐዋርያትም አንድ ሆነው ይወርሷታልና፡፡
3. በታቦር ተራራ ከመዓስባን ሙሴ ከደናግል ደግሞ ኤልያስ
እንደተገኙ መንግሥተ ሰማያትንም ደናግልም መዓስባንም
በአንድ ላይ ይወርሷታልና፡፡
4. በታቦር ተራራ ሞተው ከተቀበሩት መካከል ሙሴን
በብሔረ ሕያዋን ካሉት ደግሞ ኤልያስን እንደመጡ
መንግሥተ ሰማያትንም ሞተው የተቀበሩትም በብሔረ
ሕያዋን ያሉትም በአንድነት ይወርሷታልና፡፡
በአጠቃላይ ታቦር ተራራ የክርስቶስ የባሕርይ አምላክነት
የተመሠከረበት፣ የምሥጢረ ሥላሴ ትምህርት የተሰጠበት፤
ፈጣሪ ከቅዱሳን ሰዎቹ ጋር የተገኘበት፤ በልበ ሐዋርያት የነበረ
ሰይጣን ድል የተደረገበት፤ የሐዋርያት በተለይም የሦስቱ
ባለሟልነት የተገለጠበት፤ አሉባልታና ተራ ወሬ የከሸፈበት፤
የቅዱሳንን ክብርለሚያናንቁ ተራራም እንኳን “ቅዱስ”
እንደሚባል የተማርንበት፤ የብሔረ ሕያዋን መኖር
የተመሰከበረበት፤ የትንሣኤ ሙታን ዋስትና የተገለጠበት
የክብር ሰገነት፣ የምሥጢር መቅደስ፣ ታላቅ ትምህርት
ቤትም ጭምር ነው፡፡
ፈጣሪያችን እግዚአብሔር እስከ መጨረሻዋ ሕቅታ ድረስ
በታቦር ተራራ በተመሰለች ቤተክርስቲያን በሃይማኖታችን
ጸንተን የመንግሥተ ሰማያት ወራሾች የስሙ ቀዳሾች
እንድንሆን የእግዚአብሔር ቸርነት የድንግል ማርያም
አማላጅነት አይለየን፡፡ አሜን!!
(መቅረዝ ዘተዋሕዶ .)፡- ጌታችንና መድኃኒታችን ኢየሱስ
ክርስቶስ በፊሊጶስ ቂሳርያ ለደቀመዛሙርቱ “ሰዎች የሰውን
ልጅ ማን ይሉታል?” ብሎ ጠይቋቸው ነበር፡፡ እነርሱም
“አንዳንዶች ከእናቱ ማኅፀን ጀምሮ ቅዱስ ነውና ኤርሚያስ
ነው ይሉሀል፤ አንዳንዶቹ ድንቅ የሆነ ልደትህንና
የምታጠምቀውን አዲስ ጥምቀት አይተው መጥምቁ ዮሐንስ
ነው ይሉሀል፤ ሌሎች ደግሞ ለአባቶችህ ቤት ያለህን ቅናት
አይተው ኤልያስ ነው ይሉሃል” እያሉ መልሰውለት ነበር፡፡
ጌታችንም መልሶ፡- “እናንተስ ማን ትሉኛላችሁ?” ብሎ
ጠየቃቸው፡፡ የሐዋርያት አፈጉባዔ የሚሆን ሊቀ ሐዋርያት
ቅዱስ ጴጥሮስም “አንተክርስቶስ የሕያው እግዚአብሔር አብ
የባሕርይ ልጅ ነህ” ብሎ መልሷል፡፡ ጌታም “የዮና ልጅ
ስምዖን ሆይ በሰማይ ያለው አባቴ እንጂ ሥጋና ደም
(ምድራዊ መምህር) ይህን አልገለጠልህምና ብፁዕ ነህ”
ብሎታል፡፡
ከዚህ በኋላ ጌታችን በኢየሩሳሌም ካህናት ሊቀካህናት ጸሐፍት
ፈሪሳውያን ስለሚያደርሱበት መከራ ስለሚሞተው ሞት
ይነግራቸው ጀመር፡፡ ሰይጣንም አስቀድሞ በቀዳማይቱ
ሔዋን እንዳደረገው አሁንም በስምዖን ጴጥሮስ አንደበት
ወዳጅ መስሎ “አይሆንም አይደረግም” በማለት መከራከር
ጀመር፡፡ ጌታችን ግን ጴጥሮስን አድርጎ ሰይጣንን ይገስጸው
ጀመር፡- “ጴጥሮስ ሆይ! የእኔ አመመጣጥ ለምን እንደሆነ
አታስተውልምን? የዮና ልጅ ስምዖን ሆይ! በቤተልሔም
ተወልጄ ከሴቶች ለሚወለዱ ሕፃናት ሁሉ ደስታ
እንደሆንኩላቸው አሁንም የእኔን እዚያ መውረድ እየተጠባበቁ
የሚገኙትን ቅዱሳን ወደ ገነት እመልስ ዘንድ ሲዖል መሄድ
አለብኝ፡፡ ብዙዎች ነቢያትና ጻድቃን ይህን ሊያዩ ይመኛሉና፤
አብርሃም ቀኔን ያይ ዘንድ ይናፍቃልና፡፡ ስለዚህ አያቸው ዘንድ
መውረድ አለብኝ፤ እጎበኛቸው ዘንድ ልሞት ልሰቀል
ይገባኛል፡፡ በእውነት ሰይጣን ካልሆነ በቀር የእኔን መሰቀል
የሚቃወም የነፍሳትም ነፃ መውጣት የማይናፍቅ ማን ነው?
አንተ ጴጥሮስ! ይህን ሁሉ የምትለኝ ሰይጣን በአንተ ተመስሎ
አንድም አንተው ራስህ ለእኔ ካለህ ፍቅር የተነሣ መሆኑን
ብረዳም ጀሮህ ትንቢተ ነቢያትን ባይሰማ ይልቁንም ዓሣ
ማጥመድን ብቻ ስለሚያውቅ ነውና ወግድ” አለው፡፡
ይህም በሆነ በሰባተኛው ቀን ሦስቱን ደቀ መዛሙርት
ማለትም ጴጥሮስ፣ ዮሐንስንና ያዕቆብን ይዞ ወደ ታቦር
ተራራ ወጣ፡፡ ክርስቶስ ባይሞት እንዴት ያለ ክብር
እንደሚቀርባቸው ያሳያቸው ዘንድ ምስክርም እንዲሆኑ
እነዚህን ሦስቱ ደቀ መዛሙርት ይዞ ወጣ፡፡ በዚያም እንደ
ዮርዳኖስ ወንዝ መድኃኔዓለም ክብረ መንግሥቱን፣ ብርሃነ
መለኮቱን ገልጠላቸው፡፡ በየዓመቱ ነሐሴ 13 ቀን ቤተ
ክርስቲያናችን ከምታከብራቸው ዘጠኙ ዐበይት የጌታ በዓላት
አንዱ የሆነው በዓለ ደብረታቦር የዚህ ታሪክ መታሰቢያ ነው ፡፡
በዚህ ዕለት ሕፃናት ጅራፋቸውን ገምደው እያስጮኹ
ይጨፍራሉ፡፡ ይኸውም ጅራፍ ሲጮህ እንደሚያስደነግጥ ሁሉ
ከጌታ ጋር የነበሩት ሦስቱ ደቀ መዛሙርትም አብ በደመና
ሆኖ ሲናገር መደንገጣቸውንና መውደቃቸውን የሚያስታውስ
ነው፡፡
ታቦር ተራራ ከገሊላ ባሕር በምዕራራባዊ ደቡብ በኵል 10
ኪሎ ሜትር ርቀት ላይ፣ ከናዝሬት ከተማ በስተምሥራቅ፣
ከዮርዳኖስ ወንዝ በስተምዕራብ አቅጣጫ የሚገኝ ተራራ
ነው፡፡ ተራራው ከባሕር ወለል በላይ 572 ከፍታ አለው፡፡
ብዙ ሰዎች ከላይ ወደታች ሲታይ ታቦር ተራራ ቅርጹ
የተገለበጠ የሻይ ስኒ ይመስላል ይላሉ ፡፡
ምሥጢረ መንግሥቱን ለምን በታቦር ተራራ ገለጸው?
መድኃኔዓለም ሌሎች ተራሮች እያሉ ክብሩን ለመግለጥ
ስለምን ደብረ ታቦርን መረጠ ቢሉ ትንቢቱንና ምሳሌውን
ለመፈጸም ነው፡፡
1. ትንቢቱን ለመፈጸም
“ታቦርና አርሞንኤም በስምህ አምነው በተደረገላቸው ነገር
ደስ ይላቸዋል፣ ስምህን ያመሰግናሉ፣ ለስምህም ምስጋና
ያቀርባሉ” እንዲል /መዝ. 88፡12/፡፡ 2. ምሳሌውን
ለመፈጸም
ይህ ተራራ ባርቅ ሲሳራን ድል አድርጎበታል /መሳ.4፡6/፡፡
ታሪኩም እንዲህ ነው፡፡ “የእስራኤል ልጆች በእግዚአብሔር
ፊት እንደገና ክፉ ሥራ ሠሩ፡፡እግዚአብሔርም በአሶር
በነገሠው በከነዓን ንጉሥ በኢያቡስ እጅ አሳልፎ ሰጣቸው፤
የሠራዊቱም አለቃ በአሕዛብ አሪሶት የተመረጠው ሲሣራ
ነበር፡፡… ዘጠኝ መቶ የብረት ሰረገሎች ነበሩትና
የእስራኤልንም ልጆች ሃያ ዓመት ያስጨንቃቸው ነበር” /
መሳ 4.1-3/፡፡ ሁሌም ቢሆን የሰውን በደል
ዐይቶእንደወጣችሁ ግቡት፣ እንደገባችኋት ውጧት የማይልና
“ከፈተናው ጋር መውጫውን ደግሞ ያደርግላችኋል”
የተባለለት እግዚአብሔር ከዚህ ቀንበርየሚላቀቁበትን መላ
ራሱ አመለከታቸው /1ቆሮ. 10-13/፡፡ እስራኤላውያን ወደ
ፈጣሪያቸው በጮኹ ጊዜ የለፊዶት ሚስት የሆነችውንና
እስራኤልን በነቢይነትና ዳኝነት ታገለግል የነበረችው ነቢይቱን
ዲቦራን ተጠቅሞ የማሸነፊያ መላውን አመለከታቸው፡፡
ነቢይቱ ዲቦራ ትንቢት ከመናገር አልፋ የእስራኤልን ንጉሥ
ባርቅ ከእኔ ጋር ወደ ጦርነቱ ውጪ ብሎ ባስጨነቃት ጊዜ
በጦር አዝማችነትም ተሳተፈች፡፡ እግዚአብሔር በነቢይቱ
በዲቦራ በኩል ለእስራኤል ንጉሥ “ሔደህ ወደ ታቦር ተራራ
ውጡ” ብሎ አዞት ነበርና ንጉሡ ዐሥር ሺሕ ብረት ለበስ
ያልሆነ እግረኛ ሠራዊት ይዞ ደብረ ታቦርን ተማምኖ
በተራራው ላይ መሸገ፤ ጦርነቱም ሳይጀመር አለቀ፡፡
ምክንያቱም “እግዚአብሔርም ሲሣራን ሰረገሎቹንም ሁሉ
ሠራዊቱንም ሁሉ ከባርቅ ፊት በሰይፍ ስለት አስደነገጣቸው፡፡
ሲሣራም ከሰረገላው ወርዶ በእግሩ ሸሸ” /መሳ. 4.15/፡፡
እስራኤል በእግዚአብሔር አጋዥነት በታቦር ተራራ ላይ የሃያ
ዓመት የግፍና የሰቀቀን አገዛዝ ቀንበራቸውን ከትከሻቸው
አሽቀንጥረው በምትኩ የድል ካባን ደረቡ፡፡ “በጦርነት
ኃይለኞች ሆኑ የባዕድ ጭፍሮችንም አባረሩ” ተብሎም
ጀግንነታቸው ተጻፈላቸው፡፡ የታቦር ተራራ ያኔ እንደ
እግዚአብሔር ፈቃድ ባለውለታቸው ነበር /ዕብ.
11.32-34/፡፡ ጌታም በልበ ሐዋርያት ያለ ሰይጣንን ድል
ያደርግበታልና ማለትም በልባቸው ጥርጥርን እና ፍቅረ
ሢመትን( የሥልጣን ፍቅር) ያሳደረ ዲያብሎስን ድል
ነስቶላቸዋል፡፡ ከዚህም በመነሣት ነው “በዓለ ደብረታቦር
የደቀመዛሙርት ተማሪዎች በዓል ነው” የሚባለው ፡፡
ለምን ሦስቱን ሐዋርያት ብቻ ይዞ ወጣ?
1. ጌታ “እሞታለሁ፤ እሰቀላለሁ” ባለው ጊዜ ጴጥሮስ
“ልትሞት አይገባም፤ ይህ ላንተ አይገባም” ብሎ ተቃውሞት
ነበርና በአብ ቃል “እርሱ ያላችሁን ስሙት፤ ይህ ለአንተ
አይገባም አትበሉት፤ አትቃወሙት” ለማለት፡፡
2. ጌታ “እናንተስ ማን ትሉኛላችሁ?” ብሎ ደቀመዛሙርቱን
በጠየቃቸው ጊዜ ጴጥሮስ “አንተ የሕያው የእግዚአብሔር
ልጅ ነህ” ብሎት ነበርና አሁንም አብ “አዎ ልክ ነህ!
እመለክበት ዘንድ ለተዋሕዶ የመረጥኩት የምወደው ልጄ ይህ
ነው” ብሎ ለማረጋገጥ፡፡
3. ለፍቅሩ ስለሚሳሱ ነው፡፡ ይህም በዕብራይስጡ ኬፋ ፤
በግሪኩ ጴጥሮስ ፤ በግዕዙ ኰኲሕ (ዐለት) የተባለው የዮና
ልጅ ስምዖን ጌታችን “እሞታለሁ” እያለ ሲናገር
“አይሁንብህ” ማለቱ አስቀድመን እንደተናገርን “ለጌታ ካለው
ፍጹም ፍቅር የተነሣ ነው” ይላል ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ፡፡
ዮሐንስም በወንጌል “የጌታ ወዳጅ” ተብሎ ተጽፏል፡፡ ያዕቆብ
ደግሞ ጌታን በእጅጉ እንደሚወደው በኋላ ታውቋል፡፡
ይኸውም “እኔ የምጠጣውን ጽዋ ትጠጣላችሁ?” /ማቴ.20፡
20/ ሲባሉ“አዎ” ብሎ መመለሱና በዚህም በሄሮድስ
ዘአግሪጳ ሰማዕት ሆኖ መሞቱ ምስክር ነው፡፡
4. በይሁዳ ምክንያት ነው፡፡ “ኃጥእ ሰው የእግዚአብሔርን
ክብር እንዳያይ ያርቁታል” እንዲል /ኢሳ 26:13/ እርሱን
ጥሎ አሥራ አንዱን ወደ ተራራ ይዞ ቢወጣ ከምሥጢር
ቢለየኝ በሞቱ ገባሁበት እንዳይል፡፡ ያም ባይሆን ስምንቱ ደቀ
መዛሙርት ለምን ይከለከላሉ ቢሉ አልተከለከሉም በርዕሰ
ደብር (በተራራው አናት)ለሦስቱ ደቀ መዛሙርት የተገለጸው
ምስጢር በእግረ ደብር (በተራራው ግርጌ) ለነበሩት ስምንቱ
ደቀ መዛሙርት ተገልጦላቸዋል፡፡ ይህም በደብረሲና
ለሰባውሊቃናት የተገለጠ ምሥጢር በከተማ ለነበሩት
ለኤልዳድና ሙዳድ እንደተገለጠ ማለት ነው /ዘኁ.11፡26/፡፡
ኤልያስና ሙሴን ለምን አመጣቸው?
1. በአንድ ወቅት ሙሴ እግዚአብሔርን ፡- “በአንተ ዘንድ
ባለሟልነትን ማግኘቴ እውነት ከሆነስ ፊት ለፊት ተገልጸህልኝ
ልይህና በአንተ ዘንድ ባለሟልነትን ማግኘቴን ልወቀው” ሲል
ጠይቆት ነበር፡፡ እግዚአብሔርም “ጀርባዬን ታያለህ ፊቴን
ግን አታይም” ብሎት ነበር /ዘጸ. 33.13፣23/፡፡ የዚህ ኃይለ
ቃል ትርጓሜናሐተታ በደብረ ታቦር ተፈጽሟል፡፡ እንዲህ
ማለቱ “አምስት ሺሕ አምስት መቶ ዘመን ሲፈጸም ሰው
ሆኜ ሥጋ ለብሼ ኋላ በደብረ ታቦር እስክገለጽልህ ድረስአንተ
በመቃብር ተወስነህ ትኖራለህ” ማለቱ ነበርና፡፡ ይህን ማለቱ
እንደሆነ የታወቀው ግን በደብረ ታቦር ሙሴን ከብሔረ
ሙታን በአካለ ነፍስ አምጥቶ ባቆመው ጊዜ ነበር፡፡
2. ልዑል እግዚአብሔር ነቢዩ ኤልያስን፡- “አንተ በኋለኛው
ዘመን ምስክር ትሆነኛለህ” ብሎት ነበር፡፡ ይኸውም ኃይለ
ቃል ኤልያስ ከብሔረ ሕያዋን መጥቶ “የእኔን የኤልያስን ጌታ
ማን ኤልያስ ነው ይልሃል? እግዚአ ኤልያስ፤ አምላከ ኤልያስ
ይበሉህ እንጂ” ሲል በደብረ ታቦር ተፈጸመ፡፡ ታያለህ የተባለው
ሙሴም አየ፣ትመሰክራለህ የተባለው ኤልያስም መሰከረ፡፡ 3.
በፊልጶስ ቂሳርያ ጌታ ሐዋርያትን “ሰዎች የሰውን ልጅ ማን
እንደሆነ ይሉታል?” ብሎ በጠየቃቸው ጥያቄ ሲመልሱ
“ሙሴ ነው ይሉሃል ፤ እንዲሁም የኃይልሥራህን ተመልክተው
ኤልያስ ነው ይሉሃል” ብለው ነበርና ሙሴን ከመቃብር ፤
ኤልያስን ከብሔረ ሕያዋን አምጥቶ እግዚአ ሙሴ ፤ አምላከ
ሙሴ ፤ እግዚአኤልያስ ፤ አምላከ ኤልያስ መሆኑን
ለማስመስከር፡፡
4. አይሁድ ፈሪሳውያን ጌታን እንደ ሕግ ተላላፊና
የእግዚአብሔርን ክብር ለራሱ የሚወስድ አድርገው ያስቡት
ስለነበረ /ዮሐ.9፡16፣ 10፡33/ ሕግን የሰጣቸው ሙሴንና
ለሕገ እግዚአብሔር ቀናተኛ የነበረው ኤልያስን አምጥቶ ሕግ
አፍራሽ አለመሆኑን የእግዚአብሔር ተቃዋሚም አለመሆኑን
ለማስረገጥ፡፡
5. ጌታችን በሙታንና በሕያዋን ላይ ሥልጣን ያለው እንደሆነ
ይታወቅ ዘንድ ሞተው ከተቀበሩት ሙሴን ከብሔረ
ሕያዋንም አልያስን አምጥቶ ሲነጋገር ታየ፡፡
6. የሐዋርያቱን የወደፊት አገልግሎት ሲነግራቸው፡፡
ይኸውም ሙሴ እና ኤልያስ ለሕዝበ እስራኤል በጣም ታማኝ
እንደነበሩ ሁሉ እነርሱም ለሚያገለግሉት ሕዝብ ታማኝ
እረኞች እንዲሆኑ፡፡ ሆኖም ግን አገልግሎታቸው ከሙሴና
ከኤልያስ ይልቅ ጠንከር እንደሚልም አሳይቶአቸዋል፡፡
ምክንያቱም ውጊያቸው እንደ ሙሴ ከፎርዖን እንደ ኤልያስም
ከአክዓብ ጋር ሳይሆን ከክፋት መናፍስት ጋር ነውና፡፡
7. ጽድቃቸው ከእነዚህ ከሙሴና ከኤልያስ የበለጠ ሊሆን
እንደሚገባ ለማሳየት /ማቴ.5፡20/፡፡ ምክንያቱም ሙሴ
ሕዝበ እስራኤልን ቢመራ ምድረ ፍልሥጥኤምን ለማውረስ
ነው፡፡ እነዚህ ግን ሕዝቡን መርተው የሚያስገቡት መንግሥተ
ሰማያትን ነው፡፡ ኤልያስ ሰማያትን ቢለጉምም ከጊዜአዊ
ዝናም ነው፡፡ እነዚህ ግን ለዘለዓለም መንግሥተ ሰማያትንም
የመለጎም ሥልጣን አላቸውና፡፡
ከዚህ በኋላ ጴጥሮስ “ጌታ ሆይ በዚህ መሆን ለእኛ መልካም
ነው” ሲል ተደምጧል፡፡ ይህም የተለያየ ትርጉም አለው፡፡
ቃል በቃል (Literaly)ስናየው ቅዱስጴጥሮስ ጌታ ሆይ በዚህ
መኖር ለእኛ መልካም ነው ማለቱ “አንተ እያበላኸን
እየፈወስከን፣ ሙሴ እነዚህ መከራ ያደርሱቡኛል ይገድሉኛል
ያልካቸውን ጸሐፍትና ፈሪሳውያን እንዳይመጡ በደመና
እየጋረደ፣ ቢመጡም አልያስ እሳት እያዘነመ እያባረራቸው
በዚህ መኖር ለእኛ መልካም ነው” ማለቱ ሲሆን
ምሥጢራዊው መልእክቱ ግን “የኢየሱስ ክርስቶስ የባሕርይ
አምላክነት በሚታመንበት፣ ወልድ ዋሕድ በምትለው
ሃይማኖት መኖር ለእኛ መልካም ነው፡፡ ሰይጣን ድል
በተደረገባት በታቦር ተራራ ምሳሌም በምትሆን በወንጌል
ሕይወት፣ አንድም በቤተ ክርስቲያን መኖር ለእኛ መልካም
ነው” ማለቱ ነው፡፡
ታቦር ተራራ የወንጌል ምሳሌ ነው!
ተራራ ሲወጡት ያደክማል፣ ከወጡት በኋላ ግን ጭንጫውን፣
ግጫውን ሲያሳይ ደስ ያሰኛል፡፡ ወንጌልም ሲማሯት
ትከብዳለች በኋላ ግን ጽድቅን እና ኃጢአትን ለይታ ስታሳውቅ
ደስ ታሰኛለች፡፡
ታቦር ተራራ የቤተክርስቲያን ምሳሌ ነው!
ሀ. በታቦር ተራራ ከብሉይ ኪዳን ነቢያት ኤልያስና ሙሴን፣
ከሐዲስ ኪዳን ሦስቱን ሐዋርያት እንደተገኙ በቤተክርስቲያን
ብሉይ ከሐዲስ እንዲነገር ያጠይቃል፤ ሐዋርያት የሰበኩት
ወንጌል አስቀድመው ነቢያት በምሳሌና በትንቢት የተናገሩት
እንደሆነ ያስረዳል፡፡ “ነቢያት በቀየሱ ሐዋርያት ገሰገሱ”
እንዲል ጳውሎስም“በሐዋርያት በነቢያት መሠረት ላይ
ታንጻችኋል” ይላልና /ኤፌ 2፣20/፡፡
ለ. በታቦር ተራራ ከመዓስባን (ባለትዳር) ሙሴን ከደናግል
ደግሞ ኤልያስ እንደተገኙ በቤተክርስቲያን በድንግልና
የሚኖሩ መናንያን መነኮሳት፣ በሕግ በሥርዓትየሚኖሩ
ባለትዳሮችም ይገኛሉና፡፡
ታቦር ተራራ የመንግሥተ ሰማያት ምሳሌ ነው!
1. ተራራ በብዙ ችግር እንዲወጡት ወደ እግዚአብሔር
መንግሥትም በብዙ መከራ እንገባ ዘንድ ያስፈልገናልና /ሐዋ
14፡22/፡፡
2. በታቦር ተራራ የብሉይ ኪዳን ነቢያት ከሐዲስ ኪዳንም
ሐዋርያት እንደተገኙ መንግሥተ ሰማያትን ነቢያትም፣
ሐዋርያትም አንድ ሆነው ይወርሷታልና፡፡
3. በታቦር ተራራ ከመዓስባን ሙሴ ከደናግል ደግሞ ኤልያስ
እንደተገኙ መንግሥተ ሰማያትንም ደናግልም መዓስባንም
በአንድ ላይ ይወርሷታልና፡፡
4. በታቦር ተራራ ሞተው ከተቀበሩት መካከል ሙሴን
በብሔረ ሕያዋን ካሉት ደግሞ ኤልያስን እንደመጡ
መንግሥተ ሰማያትንም ሞተው የተቀበሩትም በብሔረ
ሕያዋን ያሉትም በአንድነት ይወርሷታልና፡፡
በአጠቃላይ ታቦር ተራራ የክርስቶስ የባሕርይ አምላክነት
የተመሠከረበት፣ የምሥጢረ ሥላሴ ትምህርት የተሰጠበት፤
ፈጣሪ ከቅዱሳን ሰዎቹ ጋር የተገኘበት፤ በልበ ሐዋርያት የነበረ
ሰይጣን ድል የተደረገበት፤ የሐዋርያት በተለይም የሦስቱ
ባለሟልነት የተገለጠበት፤ አሉባልታና ተራ ወሬ የከሸፈበት፤
የቅዱሳንን ክብርለሚያናንቁ ተራራም እንኳን “ቅዱስ”
እንደሚባል የተማርንበት፤ የብሔረ ሕያዋን መኖር
የተመሰከበረበት፤ የትንሣኤ ሙታን ዋስትና የተገለጠበት
የክብር ሰገነት፣ የምሥጢር መቅደስ፣ ታላቅ ትምህርት
ቤትም ጭምር ነው፡፡
ፈጣሪያችን እግዚአብሔር እስከ መጨረሻዋ ሕቅታ ድረስ
በታቦር ተራራ በተመሰለች ቤተክርስቲያን በሃይማኖታችን
ጸንተን የመንግሥተ ሰማያት ወራሾች የስሙ ቀዳሾች
እንድንሆን የእግዚአብሔር ቸርነት የድንግል ማርያም
አማላጅነት አይለየን፡፡ አሜን!!
Tuesday, June 14, 2016
=>+*"+<+>††† ወደ ምስራቅ ተመልከቱ †††<+>+"*...
"ወደ ምስራቅ ተመልከቱ ማለት ምን ማለት ነው"??
በኦርቶዶክስ። ተዋህዶ ሀይማኖታችን ቤተ ክርስቲያን
የምታንፀው ምስራቁን አቅጣጫ ጠብቃ ነው እንድሁም
ከቤተ ክርስቲያኑ ጋር አብሮ የሚሰራው ቤተለሄም። በስተ
ምስራቅ በኩል ይደረጋል በፆለት ሰአትም ወደ ምስራቅ
ዙረን ነው የምንፀልየው በስረአተ ቀብር ላይም የሞተ
ሰው ሲቀበርእራሱ ውደ ምዕራብ እግሩ ወደ ምስራቅ።
ሆኖ ይቀበራል።ሌላው ዳቆኑ በስረአተ ቅዳሴው ላይ ወደ
ምስራቅ ተመልከቱ ይላል ለምን??
፩ የአዳም አባታችን ጥንተ ርስተ ገነት በምስራቅ ናት ዘፍ
2*8 ፪÷፰ ይች እርስታችን በአዳም በደል ምክንያት
በክሩቤል ሰይፍ ተዘግታ ስትኖር ሞትን ድል አድርጎ
በደልን ክሶ ጌታችን መዲሀኒታችን እየሱስ ክርስቶስ በሞቱ
ከፈተልን ሉቃ 23*43። ፳፫*፵፫ ወደ ምስራቅ በዞርን
ቁጥርወደ ገነት ለመግባት የተሰጠን ተስፍፋ ትዝ ይለናል
የተከፈተችውም ቤታችን ገነት በእምነት ውለል ብላ
ትታየናለች በክርስቶስ ያገኘነውን ፀጋ እናስባለን
ምድራዊያን አለመሆናችንንም እናስባለን
፪ ጌታ የተውለደው በምስራቅ ነው
ሰበአሰገል ኮኩቡን ያዩት በምስራቅ ሲሄን ያኮከብ
የምህረት እግዝያብሄር ምሳሌ ነው እርሱን ወደ
እግዝያብሄር እንዳደረሳቸው ሁሉ እኛንም ወደ ለመለመው
መስክ ይመራናል ማቴ ፳፪*፲፬ 22*14 ወደ ምስራቅ
በዞርን ቁጥር። የጌታን መውለድነ ያደረገልንን ውለታ
ይታውሰናል የምህረት ኮከብ እየመራን መሆኑን ትዝ
ይለናል
፫ ምስራቅ የእመቤታችን ምሳሌ ነው
ከምስራቅ ጨለማውን የሚገፈው።ፀሀይ እንደሚውጣ
ሁሉ ከእመቤታችን ከድንግል ማርያምም የአለም
የሀጥያት ጨለማ የሚገፍ ፀሀይ ፅድቅ እየሱስ ክርስቴስ
ውጥቷል። ተገኝቷል ለእናንተ ስሜ የምትፈሩ የፅድቅ
ፀሀይ ትወጣላችሁአለች። ሚል ፬*፩ 4*1 ህዝ ፵፬*፩÷፬
44*1-4 ነብዩ ህዝቀየልም እመቤታችንን ያያት በምስራቅ
ነው ስለዚህ ውደ ምስራቅ በዞርን ቁጥር እመቤታችንን
እናስታውሳለን የፅድቅ ፀሀይ ክርስቶስ ስለተውለደልን
በጨለማ አለመሆናችን ትዝ እያለን ከሀጥያት እንርቃለን
፬ የአለም ድህነት የተገኘው በምስራቅ ነው
ጌታ የተስቀለውና አለምን ያዳነው በምስራቅ ነው እየሩስ
አሌም ምስራቃዊት ከተማ ናት በመሆኑ ውደ ምስራቅ
በዞርን ቁጥር የተሰቀለውን ክርስቴስንና የተከፈለልንን ዋጋ
እናስባለን
፭ ክርስትናና ቤተ ክርስቲያን የተመሰረቱት በምስራቅ ነው
የመጅመሪያው ቤተ ክርስቲያን የተመስረተውበ በእየሩስ
አሌም ሲሆንውንጌል የተሰበከው ከዚህ በመነሳቱ ነው
ስለዚህ ውደ ምስራቅ ስንዞር የቤተ ክርስቲያን ጉዞ
የውንጌል መስፋፋትን የህዝብ ና የአለም መዳን ትዝ
ይለናል
፮ ምስራቅ የእግዝያብሄር ክብር መገለጫ ነው
ኢሳ ፳፰*፲፫ 28*13። እግዝያብሄር በምስራቅ
የእስራኤልንም አምላክ የእግዝያብሄርንም ስም በባህር
ደሴቶች አከበሩ ህዝ ፵፫*፪ 43*2 የእስራኤልንም
አምላክ ክብር ከምስራቅ መንገድ ውጣ ።
፯ የጌታ ዳግም ምፅአትም ከምስራቅ ነው
ዘካ ፲፬*፲፬ 14*14
ውስብሀት ለእግዝያብሄር አሜን
በኦርቶዶክስ። ተዋህዶ ሀይማኖታችን ቤተ ክርስቲያን
የምታንፀው ምስራቁን አቅጣጫ ጠብቃ ነው እንድሁም
ከቤተ ክርስቲያኑ ጋር አብሮ የሚሰራው ቤተለሄም። በስተ
ምስራቅ በኩል ይደረጋል በፆለት ሰአትም ወደ ምስራቅ
ዙረን ነው የምንፀልየው በስረአተ ቀብር ላይም የሞተ
ሰው ሲቀበርእራሱ ውደ ምዕራብ እግሩ ወደ ምስራቅ።
ሆኖ ይቀበራል።ሌላው ዳቆኑ በስረአተ ቅዳሴው ላይ ወደ
ምስራቅ ተመልከቱ ይላል ለምን??
፩ የአዳም አባታችን ጥንተ ርስተ ገነት በምስራቅ ናት ዘፍ
2*8 ፪÷፰ ይች እርስታችን በአዳም በደል ምክንያት
በክሩቤል ሰይፍ ተዘግታ ስትኖር ሞትን ድል አድርጎ
በደልን ክሶ ጌታችን መዲሀኒታችን እየሱስ ክርስቶስ በሞቱ
ከፈተልን ሉቃ 23*43። ፳፫*፵፫ ወደ ምስራቅ በዞርን
ቁጥርወደ ገነት ለመግባት የተሰጠን ተስፍፋ ትዝ ይለናል
የተከፈተችውም ቤታችን ገነት በእምነት ውለል ብላ
ትታየናለች በክርስቶስ ያገኘነውን ፀጋ እናስባለን
ምድራዊያን አለመሆናችንንም እናስባለን
፪ ጌታ የተውለደው በምስራቅ ነው
ሰበአሰገል ኮኩቡን ያዩት በምስራቅ ሲሄን ያኮከብ
የምህረት እግዝያብሄር ምሳሌ ነው እርሱን ወደ
እግዝያብሄር እንዳደረሳቸው ሁሉ እኛንም ወደ ለመለመው
መስክ ይመራናል ማቴ ፳፪*፲፬ 22*14 ወደ ምስራቅ
በዞርን ቁጥር። የጌታን መውለድነ ያደረገልንን ውለታ
ይታውሰናል የምህረት ኮከብ እየመራን መሆኑን ትዝ
ይለናል
፫ ምስራቅ የእመቤታችን ምሳሌ ነው
ከምስራቅ ጨለማውን የሚገፈው።ፀሀይ እንደሚውጣ
ሁሉ ከእመቤታችን ከድንግል ማርያምም የአለም
የሀጥያት ጨለማ የሚገፍ ፀሀይ ፅድቅ እየሱስ ክርስቴስ
ውጥቷል። ተገኝቷል ለእናንተ ስሜ የምትፈሩ የፅድቅ
ፀሀይ ትወጣላችሁአለች። ሚል ፬*፩ 4*1 ህዝ ፵፬*፩÷፬
44*1-4 ነብዩ ህዝቀየልም እመቤታችንን ያያት በምስራቅ
ነው ስለዚህ ውደ ምስራቅ በዞርን ቁጥር እመቤታችንን
እናስታውሳለን የፅድቅ ፀሀይ ክርስቶስ ስለተውለደልን
በጨለማ አለመሆናችን ትዝ እያለን ከሀጥያት እንርቃለን
፬ የአለም ድህነት የተገኘው በምስራቅ ነው
ጌታ የተስቀለውና አለምን ያዳነው በምስራቅ ነው እየሩስ
አሌም ምስራቃዊት ከተማ ናት በመሆኑ ውደ ምስራቅ
በዞርን ቁጥር የተሰቀለውን ክርስቴስንና የተከፈለልንን ዋጋ
እናስባለን
፭ ክርስትናና ቤተ ክርስቲያን የተመሰረቱት በምስራቅ ነው
የመጅመሪያው ቤተ ክርስቲያን የተመስረተውበ በእየሩስ
አሌም ሲሆንውንጌል የተሰበከው ከዚህ በመነሳቱ ነው
ስለዚህ ውደ ምስራቅ ስንዞር የቤተ ክርስቲያን ጉዞ
የውንጌል መስፋፋትን የህዝብ ና የአለም መዳን ትዝ
ይለናል
፮ ምስራቅ የእግዝያብሄር ክብር መገለጫ ነው
ኢሳ ፳፰*፲፫ 28*13። እግዝያብሄር በምስራቅ
የእስራኤልንም አምላክ የእግዝያብሄርንም ስም በባህር
ደሴቶች አከበሩ ህዝ ፵፫*፪ 43*2 የእስራኤልንም
አምላክ ክብር ከምስራቅ መንገድ ውጣ ።
፯ የጌታ ዳግም ምፅአትም ከምስራቅ ነው
ዘካ ፲፬*፲፬ 14*14
ውስብሀት ለእግዝያብሄር አሜን
=>+*"+<+>††† 7 †††<+>+"*...
#ሰባት_ቁጥር_ምስጢራት
በመጽሐፍ ቅዱስና በስርዓተ ቤተ-ክርስቲያን አስተምህሮ ስባት
ቁጥር ብዙ ምሳሌ እንዳለው ይታወቃል፡፡ በዕብራዊያን
ዘንድም
ሰባት ፍጹም ቁጥር ነው፡፡ ምሳሌ 24፡16 እግዚአብሔር
ከሰኞ
እስከ እሑድ ያሉትን ቀናት በሰባት ቁጥሮች ወስኗል ሕዝበ
እስራኤል ከግብጽ ባርነት ወጥተው በሲና በርሀ ሲጓዙ ይመሩት
የነበሩት በ7 ደመና እንደነበረ ይታወቃል፡፡ ዘዳ 13፡21 ከዚህ
ቀጥለንም ለቤተ-ክርስቲያን አስተምህሮ የ7 ቁጥር
ምስጢራትን
ምሉዕነትን የሚያስረዱ ልዩ ልዩ ማስረጃዎችን በዝርዝር
እንመለከታለን፡፤
ሀ/ ሰባቱ አባቶች
1. ሰማያዊ አባታችን እግዚአብሔር
2. የነፍስ አባት
3. ወላጅ አባት
4. የክርስትና አባት
5. የጡት አባት
6. የቆብ አባት
7. የቀለም አባት
ለ ሰባቱ ዲያቆናት
1. ቅዱስ እስጢፋኖስ
2. ቅዱስ ፊልጶስ
3. ቅዱስ ጵሮክሮስ
4. ቅዱስ ጢሞና
5. ቅዱስ ኒቃሮና
6. ቅዱስ ጳርሜና
7. ቅዱስ ኒቆላዎስ
ሐ ሰባት የጌታ ቃላት /እኔ ነኝ
1. የሕይወት እንጅራ እኔ ነኝ
2. የዓለም ብርሃን እኔ ነኝ
3. እኔ የበጎች በር ነኝ
4. መልካም እረኛ እኔ ነኝ
5. ትነሣዔና ሕይወት እኔ ነኝ
6. እኔ መንገድና ሕይወት ነኝ
7. እውነተኛ የወይን ግንድ እኔ ነኝ
መ ሰባቱ ሰማያት
1. ጽርሐ አርያም
2. መንበረ መንግሥት
3. ሰማይ ውዱድ
4. ኢየሩሳሌም ሰማያዊት
5. ኢዮር
6. ራማ
7. ኤረር
ሠ ሰባቱ ሊቃነ መላእክት
1. ቅዱስ ሚካኤል
2. ቅዱስ ገብርኤል
3. ቅዱስ ሩፋኤል
4. ቅዱስ ራጉኤል
5. ቅዱስ ዑራኤል
6. ቅዱስ ፋኑኤል
7. ቅዱስ ሳቁኤል
ረ ሰባቱ አብያተ ክርስቲያናት
1. የኤፌሶን ቤተ ክርስቲያን
2. የሰርምኔስ ቤተ ክርስቲያን
3. የጴርጋሞን ቤተ ክርስቲያን
4. የትያጥሮስ ቤተ ክርስቲያን
5. የሰርዴስ ቤተ ክርስቲያን
6. የፊልድልፍልያ ቤተ ክርስቲያን
7. የሎዶቅያ ቤተ ክርስቲያን
ሰ ሰባቱ ተዐምራት
ጌታ እኛን ለማዳን በመስቀል ላይ በተሰቀለ ጊዜ የተፈጸሙ
ተዐምራት
1. ፀሐይ ጨልሟል
2. ጨረቃ ደም ሆነ
3. ከዋክብት ረገፉ
4. ዐለቶች ተሠነጠቁ
5. መቃብራት ተከፈቱ
6. ሙታን ተነሡ
7. የቤተ መቅደስም መጋረጃ
ሸ ሰባቱ የመስቀሉ ቃላት
1. አምላኬ አምላኬ ለምን ተውከኝ
2. አባት ሆይ የሚያደርጉትን አያውቁምና ይቅር በላቸው
3. ዛሬ ከእኔ ጋራ በገነት ትሆናለህ
4. እነሆ ልጅሸ እናትህ እነሆት
5. ተጠማሁ
6. ተፈጸመ
7. አባት ሆይ ነፍሴን በእጅህ አደራ እስጥሃለሁ
ቀ ሰባቱ ምሥጢራተ ቤተ ክርስቲያን
1. ምሥጢረ ጥምቀት
2. ምሥጢረ ሜሮን
3. ምሥጢረ ቁርባን
4. ምሥጢረ ክህነት
5. ምሥጢረ ተክሊል
6. ምሥጢረ ንስሐ
7. ምሥጢረ ቀንዲል
በ ሰባቱ ዐበይት አጽዋማት
1. ዐቢይ ጾም
2. የሐዋርያት ጾም
3. የፍልሰታ ጾም
4. ጾመ ነቢያት
5. ጾመ ገሀድ
6. ጾመ ነነዌ
7. ጾመ ድኅነት
ተ ሰባቱ በእግዚአብሔር ዘንድ የተጠሉ ነገሮች
1. ትዕቢተኛ ዓይን ምሳ 16፡6-19
2. ሃሰተኛ ምላስ
3. ንፁህን ደም የምታፈስ እጅ
4. ክፉ ሃሳብን የምታፈልቅ ልብ
5. ለክፋት የምትፈጥን እጅ
6. የሐሰት ምስክርነት
7. በወንድሞች መካከል ጠብን የምታፈራ ምላስ
ቸ ሰባቱ ፀሎት ጊዜያት
1. ነግህ የጠዋት ጸሎት
2. ሠለስት (የ3 ሰዓት ጸሎት)
3. ቀትር (የ6 ሰዓት ጸሎት)
4. ተሰአቱ (የ9 ሰዓት ጸሎት)
5. ሰርክ (የ11 ሰዓት ጸሎት)
6. ነዋም (የምኝታ ጸሎት)
7. መንፈቀ ሌሊት (የሌሊት ጸሎት)
ኀ ሰባቱ ራሶች (2ኛ ነገ. 17፡6)
1. ኢራን
2. ኢራቅ
3. ግሪክ
4. ሚዳን
5. ግብጽ
6. ጣሊያን
7. እስራኤል
ወስብሐት ለእግዚአብሔር ለዘበቅዱሳኒሁ
ይሴባሕ ይእዜኒ ወዘልፈኒ ወለዓለም ዓለም አሜን፡፡ ወአሜን
ለይኩን ለይኩን፡፡
በመጽሐፍ ቅዱስና በስርዓተ ቤተ-ክርስቲያን አስተምህሮ ስባት
ቁጥር ብዙ ምሳሌ እንዳለው ይታወቃል፡፡ በዕብራዊያን
ዘንድም
ሰባት ፍጹም ቁጥር ነው፡፡ ምሳሌ 24፡16 እግዚአብሔር
ከሰኞ
እስከ እሑድ ያሉትን ቀናት በሰባት ቁጥሮች ወስኗል ሕዝበ
እስራኤል ከግብጽ ባርነት ወጥተው በሲና በርሀ ሲጓዙ ይመሩት
የነበሩት በ7 ደመና እንደነበረ ይታወቃል፡፡ ዘዳ 13፡21 ከዚህ
ቀጥለንም ለቤተ-ክርስቲያን አስተምህሮ የ7 ቁጥር
ምስጢራትን
ምሉዕነትን የሚያስረዱ ልዩ ልዩ ማስረጃዎችን በዝርዝር
እንመለከታለን፡፤
ሀ/ ሰባቱ አባቶች
1. ሰማያዊ አባታችን እግዚአብሔር
2. የነፍስ አባት
3. ወላጅ አባት
4. የክርስትና አባት
5. የጡት አባት
6. የቆብ አባት
7. የቀለም አባት
ለ ሰባቱ ዲያቆናት
1. ቅዱስ እስጢፋኖስ
2. ቅዱስ ፊልጶስ
3. ቅዱስ ጵሮክሮስ
4. ቅዱስ ጢሞና
5. ቅዱስ ኒቃሮና
6. ቅዱስ ጳርሜና
7. ቅዱስ ኒቆላዎስ
ሐ ሰባት የጌታ ቃላት /እኔ ነኝ
1. የሕይወት እንጅራ እኔ ነኝ
2. የዓለም ብርሃን እኔ ነኝ
3. እኔ የበጎች በር ነኝ
4. መልካም እረኛ እኔ ነኝ
5. ትነሣዔና ሕይወት እኔ ነኝ
6. እኔ መንገድና ሕይወት ነኝ
7. እውነተኛ የወይን ግንድ እኔ ነኝ
መ ሰባቱ ሰማያት
1. ጽርሐ አርያም
2. መንበረ መንግሥት
3. ሰማይ ውዱድ
4. ኢየሩሳሌም ሰማያዊት
5. ኢዮር
6. ራማ
7. ኤረር
ሠ ሰባቱ ሊቃነ መላእክት
1. ቅዱስ ሚካኤል
2. ቅዱስ ገብርኤል
3. ቅዱስ ሩፋኤል
4. ቅዱስ ራጉኤል
5. ቅዱስ ዑራኤል
6. ቅዱስ ፋኑኤል
7. ቅዱስ ሳቁኤል
ረ ሰባቱ አብያተ ክርስቲያናት
1. የኤፌሶን ቤተ ክርስቲያን
2. የሰርምኔስ ቤተ ክርስቲያን
3. የጴርጋሞን ቤተ ክርስቲያን
4. የትያጥሮስ ቤተ ክርስቲያን
5. የሰርዴስ ቤተ ክርስቲያን
6. የፊልድልፍልያ ቤተ ክርስቲያን
7. የሎዶቅያ ቤተ ክርስቲያን
ሰ ሰባቱ ተዐምራት
ጌታ እኛን ለማዳን በመስቀል ላይ በተሰቀለ ጊዜ የተፈጸሙ
ተዐምራት
1. ፀሐይ ጨልሟል
2. ጨረቃ ደም ሆነ
3. ከዋክብት ረገፉ
4. ዐለቶች ተሠነጠቁ
5. መቃብራት ተከፈቱ
6. ሙታን ተነሡ
7. የቤተ መቅደስም መጋረጃ
ሸ ሰባቱ የመስቀሉ ቃላት
1. አምላኬ አምላኬ ለምን ተውከኝ
2. አባት ሆይ የሚያደርጉትን አያውቁምና ይቅር በላቸው
3. ዛሬ ከእኔ ጋራ በገነት ትሆናለህ
4. እነሆ ልጅሸ እናትህ እነሆት
5. ተጠማሁ
6. ተፈጸመ
7. አባት ሆይ ነፍሴን በእጅህ አደራ እስጥሃለሁ
ቀ ሰባቱ ምሥጢራተ ቤተ ክርስቲያን
1. ምሥጢረ ጥምቀት
2. ምሥጢረ ሜሮን
3. ምሥጢረ ቁርባን
4. ምሥጢረ ክህነት
5. ምሥጢረ ተክሊል
6. ምሥጢረ ንስሐ
7. ምሥጢረ ቀንዲል
በ ሰባቱ ዐበይት አጽዋማት
1. ዐቢይ ጾም
2. የሐዋርያት ጾም
3. የፍልሰታ ጾም
4. ጾመ ነቢያት
5. ጾመ ገሀድ
6. ጾመ ነነዌ
7. ጾመ ድኅነት
ተ ሰባቱ በእግዚአብሔር ዘንድ የተጠሉ ነገሮች
1. ትዕቢተኛ ዓይን ምሳ 16፡6-19
2. ሃሰተኛ ምላስ
3. ንፁህን ደም የምታፈስ እጅ
4. ክፉ ሃሳብን የምታፈልቅ ልብ
5. ለክፋት የምትፈጥን እጅ
6. የሐሰት ምስክርነት
7. በወንድሞች መካከል ጠብን የምታፈራ ምላስ
ቸ ሰባቱ ፀሎት ጊዜያት
1. ነግህ የጠዋት ጸሎት
2. ሠለስት (የ3 ሰዓት ጸሎት)
3. ቀትር (የ6 ሰዓት ጸሎት)
4. ተሰአቱ (የ9 ሰዓት ጸሎት)
5. ሰርክ (የ11 ሰዓት ጸሎት)
6. ነዋም (የምኝታ ጸሎት)
7. መንፈቀ ሌሊት (የሌሊት ጸሎት)
ኀ ሰባቱ ራሶች (2ኛ ነገ. 17፡6)
1. ኢራን
2. ኢራቅ
3. ግሪክ
4. ሚዳን
5. ግብጽ
6. ጣሊያን
7. እስራኤል
ወስብሐት ለእግዚአብሔር ለዘበቅዱሳኒሁ
ይሴባሕ ይእዜኒ ወዘልፈኒ ወለዓለም ዓለም አሜን፡፡ ወአሜን
ለይኩን ለይኩን፡፡
Subscribe to:
Posts (Atom)